Get Mystery Box with random crypto!

ሽፈራው የሶማው

የቴሌግራም ቻናል አርማ rasmeried — ሽፈራው የሶማው
የቴሌግራም ቻናል አርማ rasmeried — ሽፈራው የሶማው
የሰርጥ አድራሻ: @rasmeried
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.22K
የሰርጥ መግለጫ

የአማራ ሕዝብ የሕልውና የፍትህ እና ርትዕ ትግል ትክክልና ድል መጎናፀፍ ያለበት ነው።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-04-15 13:51:22 አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ስለ ህወሃት የጦር ዝግጅት አገኘሁት ያሉት መረጃ!

ህወሃት አርሚ 44 የተባለው የጦር ክፍል፣ በጎንካ፣ሰበበራ ወጀራት አካባቢ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ወታደራዊ ልምምድ እያደረገ ይገኛል። በቅርቡ ደግሞ በ6 ኤፕሪል 2023 በሃውዜን ፣ ነበለት ፣ወርቃ ኣንባ እንዲሁም በአግበ እሰከ የጭላ ባለው ኣከባቢ ከባለፈው ሰኞ ጀምሮ ከፍተኛ የሆነ ወታደራዊ ሰልጠና መሰጠት ተጀምሯል።

በተጨማሪም ከክፍቶ ፣ጋርጃለ፣ታኦ በሚባሉ በአላማጣ ኣከባቢ በሚገኙ ቦታዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የወኔ  ሰራዊት በእዚሁ እለት ገብቷል። እስከ እዚህ እለት ደረስ የወያኔ ታጣቂዎች የፈቱት ትጥቅ የለም። የተሰጣቸው መምሪያ የለም። መረጃዎች የሚያሳዩት የወያኔ ታጣቂዎች በከፍተኛ የሆነ ወታደራዊ ሰልጠና መጠመዳቸውን ነው። ይህ መረጃ እንደጠቆመው ይህ የወያኔ እንቅስቃሴ በማእከላዊ መንግስት እንደሚታወቅ ነው። ወታደራዊ ስልጠና ለምን እንዳስፈለገ ወያኔዎች ለወታደሮቻቸው የሚሰጡት ማብራሪያ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ባወጣኋቸው ጽሁፎች እንደገለጽኩት በህወሃት ማእከላዊ ኮሚቴ  ስብሰባዎች፣ ከሰላም ስምምነቱ በኋላ በይፋ ሲነገር የነበረው “የሰላም ስምምነቱን ተፈጻሚ ለማድረግ ስምመነቱን ከሚቃወሙ ከአማራና ከኤርትራ ሃይሎች ጋር ለምናደረገው ጦርነት ነው” የሚል ነው።

ከዚህ በተጨማሪ ወያኔ ከተተኳሽ ውጭ ያሉ ወታደራዊ ሎጂስቲክን  ከአዲስ አበባ በወያኔ ደጋፊዎች ባላሃብቶች አስተባባሪነት እየተገዙ በአፋር በኩል በመኪና አስከ 100000 ሽህ ብር ጉቦ እየከፈሉ እያስገቡ ነው። ልብስ፣ የፕላስቲክ ኮዳዎች፣ ጫማዎች የጫኑ በርካታ የጭነት መኪናዎች ትግራይ ይገባሉ። የተተኳሽ እጥረት ለማስወገድ ወያኔ ሰፊ የኮንትሮባንድ ግዥ በማካሄድ ላይ ይገኛል። የክላሽ፣ የብሬን ፣የድሸቃ ተተካሽ በኮንትሮባንድ እየተገዛ በአፋር ጉጉውዶ ዳንደ ወደ ሞኮኒ በግመሎች እንደሚገባ መረጃዎች እየወጡ ነው።

ከዚህ በፊት ወያኔ ከትግራይ ውጭ ለሽብር ስራ የመመለመላቸው በሽዎች የሚቆጠሩ ሰልጣኞች እንዳሉ አሳውቀን ነበር። ከእነዚህ ሰልጣኞች መሃል ይሁኑ አይሁኑ ባይታወቅም በርካታ ቁጥር ያላቸው ግለሰቦች በአዲስ አበባ በኩል ወደ ወለጋ በመሄድ ኦነግ ሸኔ እየተቀላቀሉ እንደሆነ፣ በርካታ የሚታወቁ የወያኔ የልዩ ሃይል ኮማንዶ አባላት አዲስ አበባ ውስጥ  እየገቡ እንደሆነ፣ የወያኔ ከፍተኛ የመረጃ አባላትም አዲስ አበባ ውስጥ እንዳሻቸው የሚንቀሳቅሱበት ሁኔታ ተፈጥሯል።  እነዚህን እና ሌሎች መረጃዎችን መንግስት ቢሰማም ባይሰማም ማድረስ ለሚችሉ አካላት ማስተላለፋችንን አላቆምንም። እነዚህ የወያኔ የሰራዊት አባላት በአዲስ አበባ ወስጥ አንዳንድ እርምጃ እየወሰዱ እንደሆነ የሚያሳዩ መረጃዎች መታየት ጀምረዋል። የበለጠ መጣራት የሚገባቸው መረጃዎች በእጃችን ላይ ይገኛሉ።

ከአማራ ልዩ ሃይል መፍረስ ጋር በተያያዘ የአማራ ክልል ሲተራመስ በነበረባቸው ቀናት ውስጥ ወያኔ በሌላ በኩል የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ይህን ይመስላሉ።  በሱዳን ግንባር ኣርሚ 27 አርሚ 31 እን አርሚ 70 በስየ አብርሃ እና ሳምሬ ብዱን፣  በበረከት እና በማይካድራ በኩል በረሀውን ይዘዉ ወልቃይት ለመቆጣጠር እቅድ አውጥተው እየተንቀሳቀሱ ነው። የወያኔ የምእራብ እዝ፣ 5ክ/ጦር ማይጠብሪ ለመያዝ በቀኝ እና በግራ እቅድ አውጥቷል።  የአማራ ልዩ ሃይል ግን በዚህ ወቅት ተበትኗል።

በሰሜን ጎንደር  የሚገኙትን የማይፀምሪ ግንባር  3ቱ ወረዳዎችን እና የወልቃይት ቀጠናዋችን ለመቆጣጠር በማሰብ ጁንታው እራሱ የአደራጃቸውን የወረዳዋችን  አመራሮች ሽሬ ላይ አዘጋጅቶ በአሁኑ ሰአት እየተጠባበቀ ይገኛል። በወያኔዎች ካምፕ እየተነገረ ያለው የፌደራል መንግስት በእነዚህ ማይፀብሪ እና ወልቃይት ግንባር አካባቢዎች በቅድሚያ መከላከያ አስገብቷል፣ ቀጣይ የፌደራል ፖሊስ ያስገባል። ከላይ የተጠቀሱት ቦታዎች በ2ቱ ሰራዊት ከተሸፈነ በኋላ የአማራ ልዩ ሃይል ጠቅሎ እንደወጣ በቀጥታ ትገባላችሁ የሚል ቃል በፌደራል መንግስቱ ተሰጥቶናል የሚል ነው። ጁንታ ተዋጊዎቹን በእዚህ አባባል  ተስፋ እንዲሰንቁ አድርጎ በመጪው 3ቀናት ውስጥ ለመግባት ተዘጋጅቶ እየተጠባበቀ ነው።

እንዲህ አይነት ቃል በፌደራል መንግስቱ ይገባላቸው ወይም አይገባላቸው የሚታወቅ ነገር የለም። ሆኖም ጁንታው ለታጣቂዎች “መንግስት በገባው ቃል መሰረት እማይፈፅም ከሆነ በሃይል እንገባለን” የሚል አማራጭ  እቅድ እንዳለው ለሰራዊቱ ገልጿል።

ከመንግስት የደህንነት ሰዎች የሚመጣው መረጃ፣ “ይህ የጁንታ ታጣቂ የጥፋት ቡድን እስከ አሁኑ ሰአት ድረስ ትጥቅ አልፈታም። እንደ ጁንታ፣ የመጨረሻ ውሳኔው የወልቃይት፣ ጠለምት*፣ራያ ቦታዋች ካልተመለሱ ትጥቅ አንፈታም በማለት ለጥፋት ተዘጋጅተው ጥፋት ለማድረስ እየተንቀሳቀሱ እንዳሉ ይታወቅ” የሚል ነው። ቦታዎችን መጥቀስ አስፈላጊ ባይሆንም፣ ልዩ ሃይሉ ለቆ በመሄዱ በመከላከያ ሆነ በሌላ ሃይል ያልተሸፈኑ፣  ወያኔዎች ጦራቸውን ያለምንም ከልካይ ማስገባት የሚችሉባቸው ግንባሮች እየተፈጠሩ ነው።

በአንደኛው ግንባር ከዚህ ቀደም የህወሓት ወታደሮች የነበሩትን በጦርነቱ ያልተሳተፉትን በጀሌ ያለ ትጥቅ በምህረት ስም አስገብቷል። ጁንታው በማይጠብሪ ወረዳ  አዲማይዳጉሳ፤ ማይተክሊት ና ሀይዳ የሚባሉ ቦታዋችን፣ በአካሉ አብርሃና ሀጎስ መስፍን በሚባሉ የጁንታው አመራሮች በቁጥጥር ስር አድርጎቸዋል። ይህ ቦታ ማለት የተከዜ ወንዝን ተሻግሮ በግራ ክንፍ፣ ወርቅ ማውጫው ይዞ ለማይጠብሪ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው።

ከዚህ በተጨማሪ የህወሓት 40 ክ/ጦር የአንገረብ መደማምር ወይም ለሁመራ በቅርብ ርቀት ሸረሪና የሚባለው ቦታ ላይ ተጠግቶ ይገኛል። በተጨማሪም በአዲጎሹ፣ በቁራሪትና ማይጋባ የተከዜ ወንዝን ተፋሰስ ይዞ የተጠጋ ሀይል አላቸው። ይህን መረጃ ለአማራ ክልል መሪዎች በራሳቸው የደህንነት መዋቅር እንዲደርስ የተደረገ ቢሆንም በጠቅላላ በሃገርና በክልሉ የደህንነት መስሪያ ቤት ዙሪያ የሚታየው መዝረክረክ የሚያሳስባቸው አካላት በኛ በኩል ለክልሉና ለፌደራሉ መንግስት ከፍተኛ መሪዎች እንዲደርሳቸው ይሉኩልናል። ደርሶናል የሚል ምላሽ ባናገኝም ተመሳሳይ መረጃዎችን ባላፉት ሁለት አመታት ስናደርስ ቆይተናል።

ሌላው ከአማራ ልዩ ሃይል ጋር በተያያዘ ችግር የፈጠረው ጉዳይ፣ የፌደራል መንግስቱ የወልቃይትና የራያን ጉዳይ እንዴት ሊፈታው እንዳሰበ ግልጽ አለማድረጉ ነው። በወያኔ በኩል በተደጋሚ በውስጥ በስብሰባዎቻቸው ሆነ በአደባባይ የሚናገሩት ግልጽ ሆኗል። የእነዚህ ሁለት ቦታዎች ጉዳይ በህገ መንግስቱ መሰረት እንደሚፈታ ከመንግስት ጋር ተግባብተናል እያሉ ነው። በወያኔ በኩል በህገ መንግስቱ መሰረት ማለት ቦታዎቹ መጀመሪያ በቅድሚያ ወደነበሩበት የትግራይ አሰተዳደር ተመልሰው ከዛ በኋላ በነዚህ ቦታዎች ላይ የሚነሳ የማንነትና የይገባኛል ጥያቄ ካለ በህገ መንግስቱ ይፈታል ማለት ነው።

ወያኔዎች ለሰራዊት አባላቶቻቸው ለደጋፊዎቻቸው ደጋግመው ይህን እየተናገሩ ነው። የኢትዮጵያ መንግስትም ከፕሪቶሪያው ስምምነት መሃል ብዙ ተግባራት ቢያከናውንም ካልፈጸማቸው ተግባራት መሃላ የአማራን ሃይሎች ከወቃይትና ከራያ አሰውጥቶ ለትግራይ ማስረከብ እንደሆነ ጌታቸው ረዳ በሌላ ሚድያ ሳይሆን በኢትዮጵያ ቴለቪዥን ላይ ቀርቦ ተናግሯል።
603 views10:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 13:11:43 "ከእርቁ በፊት አማራን ማፅዳት "

በወለጋ አማራው ላይ የተቀናጀ ጦርነት ተከፍቷል። ብርሐኑ ጁላ የሚመራው ሠራዊትም ዋና ተሰላፊ ሆኗል። በወለጋ አማራን የማፅዳት ፕሮጀክት ሸኔ በሚል ሽፋን መዋቅራዊ አላማ ተይዞበት ለአምስት አመታት ተፈፅሟል። ወደ አንድ ሚሊዮን አማራ ሲፈናቀል በሺህ የሚቆጠሩት ተገድለዋል።
ስለሆነም አማራን ትጥቅ ለማስፈታት ያሤረው ፋሽስተዊ አገዛዝ ሸኔም ወደእርቅ ይገባል የሚል ፕሮፖጋንዳ ጀመሯል።
ሸኔ የሚለው የዳቦ ስም እርቅና ተሃድሶ ወደሚል ድራማ ከተሸጋገረ አማራን የማፅዳት ሥራው ሽፋን ሰለሚያጣበት አሁን በይፋ ጦርነት ከፍቷል።
ለኦነግ ሸኔ የትጥቅና ስንቅ አቅርቦት በማስሳለጥ ሲሰሩ የኖሩት ብርሃኑ ጁላ ፣ ደመላሽ ገብረሚካኤል እና ሲሳይ ቶላ አሁን የመጨረሻውን አማራን የማፅዳት ኦፖሬሽን ቆመው እያስፈፀሙ ነው። ከአቋራጭ የዲግሪ ቅሸባ ባለፈ የረባ ትምህርት የሌላቸው አበባው ታደሰ እና ተመስገን ጥሩነህ አድርጉ የሚባሉትን ከመፈፀም አድር-ባይነት ያለፈ ሚና የሌላቸው የአማራ አጥቂዎች ሆነዋል።
"የክልሎች ልዩ ኃይል ፈርሷል" የሚለው ብርሃኑ ጁላ አሁ፡ በይፋ ከኦነግ ሸኔ ሠራዊት ጋር ሠራዊት አሰልፎ አማራን በወለጋ እያስጨፈጨፈ ይገኛል። በምስራቅ ሸዋ አስተዳደር የሚደገፈው "የእነሽመልስ ሸኔ" ደግሞ በምስራቅ አማራ ጦርነት ከከፈተ ሰንብቷል።

ድል ለአማራ !

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
531 views10:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 13:06:41
ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ተከትሎ ቢያንስ ስምንት ጋዜጠኞች መታሰራቸውን ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ጥብቃ ተሟጋቹ ኮሚቴ - ሲፒጄ አስታወቀ።

በአገሪቱ ፖለቲካዊ ውጥረት በሚከሰትበት ጊዜ ከሕግ ውጪ ጋዜጠኞችን ማሰር እንዲያቆሙ እና የፀጥታ ኃይሎች በጋዜጠኞች ላይ ፈጽመውታል የተባሉ ጥቃቶችንም እንዲመረምሩ ሲፒጄ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናትን ጠይቋል።

ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!
https://t.me/Gionamhara
449 views10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 12:46:04 ለጀኔራሉ ይህን መልዕክት አድርሱልኝ!
የርስዎ ጎልያድነት ዛሬ ከናቁት እና ከደነፉበት ህዝብ በታች ነው
******
ትላንት ምሽት በብሄራዊ ጣቢያዎች ላይ የተላለፈው የጀኔራል አበባው ሃይል የተቀላቀለበትን ቃለ መጠይቅ አይቼ እጅግ አዘንኩ፤ አፈርኩም። ከብዙ ጥያቄና መልስ በኋላ የቃለመጠይቁን መዝጊያ "እኔ ሰው ነኝ ፤ ሲቀጥል የኢትዮጵያ ጀኔራል ነኝ ። እኔ የአንድ ብሄር አገልጋይ ልሆን አልችልም" እኔ የህዝብ ልጅ ነኝ ሲሉ ቃለመጠይቃቸውን ደምድመዋል።

መደምደሚያቸውን ተቀብለን እንደ ሰውም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ጀኔራል ሰውኛ የሆኑ የሞራል ጥያቄዎችን ልናነሳላቸው ተገደናል።

እንዴው ለመሆኑ እርስዎ ከተሾሙበት ጊዜ ጀምሮ ዘብ የቆሙለት ውሽልሽሉ መንግስት ጥገናዊ ለውጥ አደረኩ ባለበት ማግስት በቤኒሻንጉል እና በወለጋ ለተከታታይ 5 አመታት የአማራ ህዝብ ታርዶ በጅምላ ሲቀበርና ሲፈናቀል እርስዎ የሚመሩት ተቋም ምን እየሰራ ነበር?

በኦሮሚያ ክልል እና በአዲስ አበባ የሚኖረው የአማራ ህዝብ በብሄሩ ተለይቶ ለዘመናት ያካበተው ሃብት በአንድ ጀንበር ሲወድምበትና ሲፈናቀል በርስዎ የሚመራው የማህበራዊ ፍትህ አስጠባቂ የበላይ ተቋም ምን ሰራ?

እርስዎስ ቢሆኑ እንደ አንድ ትልቅ ተቋም መሪ እንዲሁም ኢትዮጵያዊ ዜጋ የህዝብ ልጅ በሚዲያ ወጥተው ስለምን ድርጊቱን አላወገዙም? ነው ወይስ በርስዎ ስሌት የአማራ ህዝብ ኢትዮጵያዊ ዜጋ አይደለም ማለት ነው?

ሌላው ይቅር ለሃገርና ለህዝብ ደህንነት ስጋት የሆነው የኦሮሚያ ክልል መንግስት ሃይሎች ከመከላከያ ሰራዊቱ በላይ ዘመናዊ መሳሪያዎችንና ወታደራዊ ኮንቮዮችን ታጥቆ ሳለ እርሶም ሆኑ ተቋምዎ አንድም ቀን ጉዳዩን ሊያስተባብል አልቻል። ለምን?

ዛሬ የአገር ህልውና አስጠባቂው፣ የመከላከያ ሰራዊቱ መከታና ደጀን የሆነው የአማራ ልዩ ሃይል እና ፋኖ በታጠቀው ክላሽ ስለምን አይንዎ ቀላ? ለምንስ በዚህ ልክ ሚዲያ ላይ ወጥተው በዕብሪት ሊደነፉ ቻሉ? ከህወሃት ጋር በነበረው ጦርነት እንኳ ይሄን ያህል አልደነፉም ነበር እኮ ክቡር ጄኔራል? ለማንኛውም ሃይል በተሞላበት ቃለ መጠይቅዎ ውስጥ አድር ባይነትዎ ጎልቶ ታይቷል።

እንደው ለመሆኑ ኢትዮጵያዊ ጀኔራልነትዎ እርስዎ የወጡበትን ህዝብ እንዲጠየፉ ያደረገዎት መንፈስ ምን ይሆን?

በአንድ ወቅት የእርስዎ አለቃ ጀኔራል ብርሃኑ ጁላ በስረአቱ ውስጥ ስለሚታየው የተረኝነት ድርጊት ተጠይቀው በድፍረትና በልበ ሙሉነት "አዎ ተራው የኛ ነው፤ ተረኞች ነን" ብለው እንደነበር ክቡር ጀኔራል አበባው ሊረሱት አይችሉም ብለን እናምናለን።

ሲጠቃለል:- ክቡር ጄኔራል ሆይ የሞራል ሚዛንዎን ስተዋል። ምናልባት የእርስዎን አላውቅም እንጂ በርስዎ የሚመራው ሰራዊት ከህዝብ ነው የወጣው። ዛሬ እርስዎ የተማመኑበት ሃይል ሁሉ ከህዝብ በታች ነው።

አዎ የርስዎ ጎልያድነትም ዛሬ ከናቁት እና ከደነፉበት ህዝብ በታች ነው
522 views09:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 12:40:55
'ፅንፈኛውን የአማራ ፋኖ ሙሉ በሙሉ እናጠፋዋለን'- ብርሐኑ ጁላ።

ብርሃኑ ጁላ ዛሬ ከፀጥታ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር በነበረው ስብሰባ "ከዛሬ ጀምሮ የክልል ልዩ ኃይል አደረጃጀትና መዋቅር የለም፣ በይፋ ፈርሷል" ብሏል።

ከእንግዲህ በአማራ ልዩ ኃይል ስያሜ ተልዕኮና ግዳጅ የሚቀበል ኃይል የለም። ትጥቅ የፈቱ ልዩ ኃይሎች ወደ ስልጠና እያጓጓዝን ነው ሲል ተናግሯል።

ፋኖ እና የአማራ ልዩ ኃይልን ለመከፋፈልም ፋኖ ልዩ ኃይሉን እያጠቃ መሳሪያ ለመንጠቅ ሞክሯል የሚል አደገኛ ሀሰተኛ መረጃ ሲነዛ ተደምጧል።
"ፅንፈኛውን ፋኖ ን እያጠፋነው ነው። ትንሽ ብቻ ይቀረናል"ም ብሏል።
ፋኖነት የሁሉም አማራ እሴት ሆኖ ሳለ ፋኖን እናጠፋለን ማለት አማራን እናጠፋለን ከማለት ተለይቶ የሚታይ አይደለም።

ድል ለአማራ !

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
535 viewsedited  09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 12:36:50
ጄነራል አበባው ታደሠ መለስ ዜናዊን ያንቆለጷጰሰበት ንግግር ነው።

ትናንት ጄነራሉ ምን ያክል አሸርጋጅና አሸብሻቢ እንደሆነ፤ የወያኔ ቅምጥል ጄኔራል መሆኑን ይታወቃል። አሁን ያለው የኛ ትውልድ ደግሞ አብይ ሲመጣ ወደ ፖለቲካው ጠጋ ያለው ማህበረሰብ አበባውን ጀግና ጀግና አለው። እሱን ራሱ ያገነነው እኛ አማራ ብሄርተኞች ነን፤ ሰርቆ ሲካፈል የተጣላ ጀኔራል በማንነቱ ተባረረ ብለን አገነነው እሱ ያን ተጠቀመበት።

https://t.me/Mulugetaanberberr
348 views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ