2023-04-17 12:16:12
በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን መጠነ ሰፊ ግፍ አስመልክቶ ከዓለም አቀፍ አማራ ህብረት የተሰጠ መግለጫ
ዓለም አቀፍ አማራ ህብረት በአብይ አህመድ፣ ሺመልስ አብዲሳና አዳነች አቤቤ የሚመራው የኦሮሞ ብልፅግና ፓርቲ በአማራ ህዝብ ላይ ያወጀውን ፋሺስታዊ ወረራ፣ ግድያ፣ አፈና፣ መጠነ ሰፊ ቤቶች ማፍረስና እና ማፈናቀል እንዲሁም የአማራ ልዩ ኃይልን ትጥቅ ለማስፈታትና ለማፍረስ ያሳለፈውን ዕብሪት የተጠናወተው አገር አፍራሺ የሆነ የሴራ እርምጃ አጥብቆ ያወግዛል።
የአማራ ህዝብ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ከሚደርስበት የማያባራ ግፍ እንዲሁም ከጦርነት እንኳን ገና ሳያገግም በኦሮሞ ብልፅግና የሚዘወረው የብልፅግና ፓርቲ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የአማራን ህዝብ ደህንነት እና ህልውና ሲያስጠብቅ የቆየውን ኃይል ለማፍረስ እና ትጥቅ ለማስፈታት መወሰኑ እና ይህንንም ለማስፈጸም በግልጽ ጦርነት ከህዝቡ ጋር መግባቱ ከአንድ መንግሥት ነኝ ከሚል አካል የሚጠበቅ አይደለም።
የአማራ ልዩ ኃይል የተቋቋመው በክልሉ ምክር ቤት ሲሆን በጀት የሚያገኘውም ከክልሉ ነው። የተቋቋመበት ዋነኛ ምክንያትም የውስጥና የውጭ ታጣቂ ኃይሎች በክልሉ ህዝብ ላይ እያደረሱበት የነበረውን የፀጥታ ችግር በመደበኛ ፓሊስ ሊወጣው ባለመቻሉ መሆኑ ይታወቃል።
ይህ የአማራ ልዩ ኃይል እስካሁን ድረስ በአጣየ እና ሸዋ ሮቢት ከኦነግ ጦር ጋር በመዋጋት፣ በጎንደር ከቅማንት ታጣቂወች ጋር በመፋለም እንዲሁም በቤንሻንጉል ጉምዝ ከክልል መንግሥት በተደረገለት ጥሪ መሰረት ወደ ክልሉ በመግባት የጉምዝና የኦነግ ታጣቂዎች እያደረሱ ከነበረው ጭፍጨፋ ህዝብን ከከፋ እልቂት ታድጓል።
ከዚህም አልፎ ህወሓት በከፈተው ጦርነት ከአገር መከላከያ፣ ከፋኖ ሚሊሻ እና የአፋር ልዩ ኃይል ጋር በመሆን አኩሪ የውጊያ ድሎችን በማስመዝገብ አገርን ከውርደት መንግሥትን ከመፍረስ የታደገ የሃገር ባለዉለታ ነው።
ነገር ግን ለዚህ ላደረገው አስተዋጽዖ እና ለከፈለው መስዋእትነት ምላሹ ትጥቅህን ፍታ የሚል መሆኑ ከማስገረምም አልፎ አደገኛ አካሄድ መሆኑን ተገንዝበናል።
ለመሆኑ የኦሮሞ ብልፅግና ለምን በአሁኑ ወቅት የአማራ ልዩ ኃይል ትጥቅ እንዲፈታ ወሰነ? በእኛ እምነት በአምስት መሰረታዊ ምክንያቶች ነው ብለን እናምናለን፦
1. በፕሪቶሪያ ድብቅ ስምምነት መሰረት አብይ አህመድ ወልቃይትና ራያን ለትግራይ ለማስረከብ ስለተስማማ እንዲሁም ለአሜሪካኖች ቃል ስለገባ ይህንን ለማስፈፀም ልዩ ኃይሉ እንቅፋት ይሆናል ብሎ በማሰብ ለማፈራረስ ማሰቡ፣ ለዚህ ማረጋገጫ የሚሆነወ የአማራ ልዩ ኃይል ከመከላከያ ጋር በተፈጠረው ግጭት ቦታዎችን መልቀቁን ተከትሎ የህወሓት ጦር ወደ ጠለምትና ራያ እየገባ መሆኑ እየተዘገበ መሆኑ ነው።
2. ፋኖን ትጥቅ ለማስፈታት ያደረገው ሙከራ ስላልተሳካ በቅድሚያ ልዩ ኃይሉን ትጥቅ አስፈትቶ በቀጣይ የፋኖንን፣ የሚሊሻውን እና የህዝቡን የግል ትጥቅ በቀላሉ ለማስፈታት እንዲችል በማቀድ፣
3. በወለጋ በአማራው ላይ የኦነግ ጦር ከኦሮሚያ ልዩ ኃይል ጋር በመጣመር እያካሄዱ ያሉትን የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ፣ በአዲስ አበባ ዙሪያ መጠነ ሰፊ የቤት ማፍረስና አማራውን የማፈናቀል ዘመቻ እንዲሁም አማራወች ወደ አዲስ አበባ አትገቡም የሚለው ክልከላና እንግልት አማራውን እንዲያመር ስላደረገው ለትግል መነሳቱ የማይቀር መሆኑን በመረዳት መሳሪያ አልባ ለማድረግ፣
4. የአማራ ብልፅግና አንዳንድ የበላይ አመራሮች በተለይም የዞንና የወረዳ አመራሮች የህዝቡን ብሶት ማንፀባረቅ በመጀመራቸው ክልሉ በራሱ የመወሰን አቅም ሊያመጣ ስለሚችል ለመቅጨትና የስልጣናቸው ተገዳዳሪ ኃይል ሆኖ እንዳይወጣ ለማድረግ፣
5. የኦሮሞ ብልፅግና የኦነግን የዘመናት ጥያቄ በማንገብ ኢትዮጵያን በማፍረስ አዲስ አገር ለመፍጠር ወይም የኦሮሞን የበላይነት የምትቀበልና ኦሮማዊት የሆነች ኢትዮጵያን ለመፍጠር ካለው እቅድ አንፃር ግዛት ማስፋቱ ዋናው አጀንዳ በመሆኑ አዲስ አበባን ከመሰልቀጥ፣ ቤንሻንጉልን ጋምቤላን ከመዋጥ ብሎም በሶማሊያ፣ በሲዳማ በደቡብ ክልል ዙሪያ ያለውን የመስፋፋት እቅዱን ተግባራዊ ከማድረግ የአማራ ልዩ ኃይልና ፋኖ ይገዳደረኛል ብሎ ከማሰብ የተነሳ ነው።
በመንግሥት ባለስልጣናት በኩል የሚናገረውና ልዩ ኃይሎችን ወደ መከላከያ ለማዞር የበለጠ አገራዊ ኃይል አቅም ለመፍጠር ነው እንጂ ለማፍረስ አይደለም የሚለው አባባል ፍፁም ውሸት ነው። የታሰበው የአማራ ልዩ ኃይልን ለማፍረስ ነው። ለምን የአማራ ክልል ብቻ የሚል ጥያቄ ሲነሳ ሌሎችንም ያጠቃልላል በሚል ህዝብን ለማሞኘት እየጣሩ ይገኛሉ። ነገር ግን ህዝቡ ስለነቃ ሰሚ አላገኙም። ዋናው እቅዳቸውን በአምባሰደር ተሾመ ቶጋ በኩልና ከአማራ ክልል የፓሊስ ኮሚሺነር በኩል ትጥቅ ፍቱ የሚለው ትዕዛዝ በግልፅ እንዲታወቅ ሆኗል።
ለመሆኑ የአማራ ክልል በአሁኑ ሰዓት የህልውና ስጋት የለበትም? በትክክል ከህወሓት፣ ከኦነግና ከኦሮሚያ ልዩ ኃይል እንዲሁም ከሱዳን ወራሪ ጦር ከፍተኛ የህልውና ስጋት አለበት። በአሁኑ ሰዓት ኦነግ በአጣየና አካባቢው ጦርነት በአማራው ላይ ከፍቷል።
የኦሮሚያ ልዩ ኃይል በብዙ የአማራ ከተሞች በመከላከያ ስም በመግባት በህዝቡ ላይ ግልፅ ጦርነት እያካሄደ ንፁሀንን እየጨፈጨፈ ይገኛል። ህወሓት በፌደራል መንግስት በመታገዝ ወልቃይትና ራያን በጦርነት አሸንፎ ለመያዝ ሰራዊቱን እያስጠጋ ይገኛል።
መንግሥትም ታስረው የነበሩ የትግራይ የጦር መኮንኖችን በመፍታት ወደ ትግራይ እየሸኛቸው ይገኛል። ሱዳን የአማራ ልዩ ኃይል ይዞት የንበረውን ካምፕ መልቀቅ ተከትሎ ጦሯን አስገብታ የኢትዮጵያን መሬት በስፋት እየተቆጣጠረች ትገኛለች። እንግዲህ ይህ ከሁሉም አቅጣጫወች የጦርነት ስጋት ባለበት ሁኔታ ነው አማራው ትጥቁን እንዲፈታ የተወሰነበት። ለምንድን ነው ይህ የሚሆነው ቢባል የተፈለገው አማራው ያሉትን ጥያቄዎች ሁሉ ትቶ በባርነት ታዛዥ ሆኖ እንዲኖር ብሎም የኦነጉ መንግሥት አዲስ አገር የመፍጠሩን ወይም የኦሮሞን የበላይነት ለማረጋገጥ የወጠነውን ፕሮጀክት እውን ለማድረግ እንቅፋት እንዳይፈጥርበት ለማድረግ ነው። ይህን በመረዳት ልዩ ኃይሉም ሆነ ህዝቡ ውሳኔውን እንቃወማለን ብሎ ለሰላማዊ ሰልፍ ሲወጣ ጨፍጫፊ ኃይል ተልኮበታል። በብዙ ሚዲያወች እንደተዘገበው አብዛኛው ወደ አማራ ክልል ለወረራ የገባው የመከላከያ ልብስ የለበሰ የኦሮሞ ልዩ ኃይል መሆኑ ተረጋግጧል። ይህ ወራሪ ኃይል በፍፁም ጭካኔ ህዝቡን በከባድ መሳሪያ እየጨረሰው ይገኛል። ብዙወች ተገድለዋል እንዲሁም ቆስለዋል። ህዝቡ ግን ለህልውናው በመዋደቅ ላይ ይገኛል። መሆንም ያለበት ይኸው ነው። የዓለም አቀፍ የአማራ ሕብረት ከተገፋው የአማራ ህዝብ ጎን መቆሙን ያሳውቃል።
የአማራ ክልል መንግሥት በዚህ ወሳኝ የትግል ምዕራፍ ወቅት ህዝቡን ክዶ ከወራሪው ኃይል ጋር ወግኖ መቆሙ እጅግ አሳዛኝና አሳፋሪ ተግባር ነው። አሁንም የበለጠ ደም መፋሰስ ሳይፈጠር ከህዝቡ ጎን በመሆን የትግሉ አካል እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን።
ኢትዮጵያ አገራችን ከዚህ የበለጠ ትርምስ ውስጥ እንዳትገባ ለመንግሥትና ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የሚከተሉትን ጥያቄዎች እናቀርባለን፦
1. በአማራ ህዝብ ላይ የተደቀነው የህልውና ስጋት እስኪቀረፍና አስተማማኝ ሰላም እስኪገኝ ድረስ ልዩ ኃይሉ በፊት በነበረው ሁኔታ እንዲቀጥል፣
600 views09:16