Get Mystery Box with random crypto!

ሽፈራው የሶማው

የቴሌግራም ቻናል አርማ rasmeried — ሽፈራው የሶማው
የቴሌግራም ቻናል አርማ rasmeried — ሽፈራው የሶማው
የሰርጥ አድራሻ: @rasmeried
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.22K
የሰርጥ መግለጫ

የአማራ ሕዝብ የሕልውና የፍትህ እና ርትዕ ትግል ትክክልና ድል መጎናፀፍ ያለበት ነው።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-05-06 22:38:20 ዐቢይ አህመድ እና አገዛዙ፤ ውሸታም እና የውሸታሞች ስብስብ ስለሆነ፤ እውነትን ይጠየፋል፤ ሀቀኞችን ደግሞ አሳዶ ያፍናል፣ ያስራል፣ ያፈናቅላል፣ ይገድላል።

ብትገድሉንም፣ ብታፍኑም ሆነ ብታስሩንም፤ ትግላችን የሀቅ ነውና እናሸንፋችኋለን።

አንበርብር!
472 views19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 21:44:45
ጓዳችን ታጋይ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ በፋሽስታዊው አገዛዝ ታፍኗል።

የፋሽስቱ ኃይል በመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት በኩል ለመንግሥት ሚዲያዎች እና አገዛዙን ለሚደግፉ አፈቀላጤዎቹ "በአሸባሪነት የተጠረጠረው ጎበዜ ሲሳይ ተይዟል" በሚል በሥፋት እንዲያራግቡት ጥብቅ ትዕዛዝ መሥጠቱን ሰምተናል።

አምባገነኖች መለያቸው ነው። የሚታፈኑ ጓዶቻችን ሌሎች ሺህዎችን እያፈሩ ትግሉን ከማቀጣጠል የሚገታ አይደለም!!

ትግላችን ይቀጥላል!!  ሞት ለፋሽስቶች ድል ለአማራ ሕዝብ!!

የምንፈራው ራሱን ፍርሃትን እንጂ አምባገነንን ፈርተን አንቆምም!! ትግላችን እስከቀራኒዮ ነው። የፈራ ይመለስ!

ድል ለአማራ !

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
1.1K views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 21:34:38
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዘር ፍጅት ወንጀልን በገንዘብ እየደገፈ ነው።

"ፕራይም" የተባለው ሚዲያ በፀረ አማራ ቅስቀሳ የተሰማራ ሚዲያ ነው። አማራ ክልል የሚኖርን ህዝብ እርስ በእርስ ለማጋጨት ከሚነዛው ሀሰት በተጨማሪ ሰሞኑን ጉራጌ ዞን የተፈፀመን ግጭት ጠንሳሽ አማራ አስመስሎ አቅርቧል። ዋና ስራው  ፀረ አማራ ቅስቀሳ ነው። የአማራ ህዝብ በሌላው ላይ በደል የፈፀመ አስመስሎ ሲቀሰቅስ ይውላል።

ይህን ሚዲያ በገንዘብ እየደገፈ፣ የዘር ፍጅትን እንዲፈፀም የሚደረግን ቅስቀሳ እያገዘ ያለው የኢትዮጵያ ንግድ ነው። አንድ ተቋም "ስፖርሰር" ከማድረጉ በፊት ሚዲያው ምን እንደሚሰራ ማየትና መገምገም ይጠበቅታል። ነገር ግን በዚህ ሚዲያ ገዥዎቹ የሚፈልጉት ፀረ አማራ ቅስቀሳ ስለሚደረግ አላማውን በኢትዮጵያ ህዝብ ገንዘብ እየደገፉት ይገኛሉ። ይህ ሚዲያ የሚሰራውን ለተመለከተ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአቋም አማራ ጠላቴ ነው ብሎ ፀረ አማራ ቅስቀሳና የዘር ፍጅትን እየደገፈ እንደሆነ አያጣውም።
878 views18:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 21:13:46
875 views18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 21:13:40 "እኛ ተከሳሾች ከዚህ ሥርአት ፍትህን አንጠብቅም ህዝባችን እንዲገነዘበው የምንፈልገው እና በድጋሚ የምናረጋግጠው አማራነትና ፋኖነት እንደወንጀል ተቆጥሮ በሃሠት ተከሠናል ያለ ፍርድ ቤት ውሳኔ በዶክመንተሪ ተፈርዶብናል ወደፊት እውነቱን ህዝብና ታሪክ ይፈርዳል።"

በአዲስ አበባ በእስር ላይ የሚገኙ የአማራ ልጆች

የአማራ ሚዲያ ማዕከል (አሚማ)
   ሚያዚያ 28/2015 ዓ/ም
      አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

        ዳኛው ማነው?

እኛ የአማራ ልጆች በመንግስት የሀሠት ክስ ተከሠን በእስር እንገኛለን።

አብዛኞቹ ወጣቶች በህግ ጥላ ስር ሲውሉ በፖሊሶች ተደብድበው በጨለማ ቤት ቆይተው ፍ/ቤት ይቀርባሉ በመንግስት የሀሠት ዶክመንተሪ ተዘጋጅቶብን በእስር  እንድንቆይ በብልፅግና ፖለቲከኞች ተፈርዶብናል።

በዚህም ምክንያት ለምን ፍ/ቤት ታመላልሱናላችሁ ብለን ጠይቀናል ብዙዎቹ በሀሠት የተከሠሡ ምሁራን እና ወጣቶች የፀጥታ አስከባሪዎች ሀገርን ከመፍረስ ህዝብን ከመዋረድ ለመታደግ የመንግስትና የህዝብን ጥሪ ተቀብለው በግንባር ተዋግተው በደረታቸው የጥይት እርሳስ በግንባራቸው የቦንብ ፍንጣሪ ይዘው ነው የተከሠሱት።

ወጣቶቹ ህክምና ሲገባቸው የውንጀላ ዶክመንተሪ ሠለባ ሆነዋል።

በእስር ላይ እያለን በአማራ ክልል መንግስት በፈጠረው ረብሻ ወንጀለኞች ተብለናል።

በኛ እምነት አማራነትን ለማሠርና ለመወንጀል የአማራ መሪዎችን መግደል እና ህዝቡን ማተራመስ አያስፈልግም።

መንግስት አማራነትን ፋኖነትን የሚያጠለሽ ተጨማሪ ዶክመንተሪ እንደሚያዘጋጅ እምነታችን ነው።

ስለሆነም በዚህ የቆርጦ ቀጥል ዶክመንተሪ ህዝባችን እንዳይደናገጥ እንጠይቃለን የተዘጋጁና የሚዘጋጁ ድክመንተሪዎች በፍትህ ሥርአቱና በዳኝነት ስራው ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠርና ህዝብን ለማደናገር እንደሆነ እንድትገነዘቡ እንጠይቃለን።

ሀገራችን ባለፉት አመታት በሀሠት ዶክመንተሪ ፍትህን በአደባባይ ሠቅላለች እነዛ ተከሳሾች ዛሬ የት ናቸው?

እኛ ተከሳሾች ከዚህ ሥርአት ፍትህን አንጠብቅም ህዝባችን እንዲገነዘበው የምንፈልገው እና በድጋሚ የምናረጋግጠው አማራነትና ፋኖነት እንደወንጀል ተቆጥሮ በሃሠት ተከሠናል ያለ ፍርድ ቤት ውሳኔ በዶክመንተሪ ተፈርዶብናል ወደፊት እውነቱን ህዝብና ታሪክ ይፈርዳል።

መንግስት የድሮን ቴክኖሎጂን ጥቅም ላይ በማዋል በሀገራችን የክፍለ ዘመኑን ታላቅ የእርስ በርስ ጦርነት አድርጓል።

ውጤቱም አውዳሚ ነበር እንዲሁም መንግስት ከኦነግ ሸኔ ጋር የከፈተውን የተራዘመ ጦርነት ለመፍታት እየጣረ እንደሆነ እየሠማን ነው። 

ሆኖም በፋኖነት እና በአማራነት ላይ አዲስ ጦርነት ማወጅ አውዳሚ እና ጥፋት እንጂ ውጤት እንደማይኖረው እናሳስባለን።

መንግስት ችግሩን በሠላም መፍታት ካልቻለ ህዝብ ራሱን ከመጥፋት የማዳን የሞራል ግዴታ አለበት።

     ሠላም ለሀገራችን ይሁን!
      የደም ዘመን ይብቃን!!

  በእስር ላይ የምንገኝ የአማራ ልጆች።

   ሚያዚያ 24-08-2015 ዓ.ም
858 views18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 21:12:48
"እንመራችኋለን"  ባሏቸው ቡድኖች የሚጠሉት እና የሚጠቁት ኢትዮጵያውያን !!

የአብይ አሕመድ ኢትዮጵያ!

የክፋት ዘመን በኢትዮጵያ !!

መታገል ብቻ!!



ድል ለአማራ !

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
1.1K views18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 19:06:22
ብርሃኑ ነገን ጨምሮ አብዛኛው ብልፅግና ውስጥ ያለ የደቡብ ልሒቅ ከኦሮሙማ ጎን ጎን የቆመው ተሸውዶ ነው። የሚፀፀተው ፣ የሚባንነው ፣ የሚደነግጠው ወደፊት ነው።
የኦሮሙማ ሰዎች ለሁሉም የሚፈልገውን እና የሚመጥነውን ይነግራሉ። እንዳሉትም የሚያሳምነውን እና የሚያደናግረውን ያደርጋሉ።
"ኩሽ ናችሁ" በማለት የትብብርና አጋርነት ስሜት የፈጠሩባቸው ወይንም ሊፈጥሩባቸው የሞከሯቸው ነበሩ፣ አሉ። ብዙዎቹ ደቡቦች የዚህ ሰለባ ሲሆኑ ተጨማሪ ማስመጫም ቀርቦላቸዋል።
"ኢትዮጵያን ለ3ሺህ አመታት የበዘበዟት የሰሜን ፖለቲከኞች ይበቃቸዋል፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ጭቁን ሕዝቦች የሚወስኑባት አገር እንድትመጣ አብረን እንቁም" ብለዋቸዋል። "ለደቡቦች ባለን አጋርነት ሁሉንም የደኢሕዴግ አመራር በስልጣን አስቀጥለናል" ይሏቸዋል።
በተለይ የሰሜኖቹ ትግሬና አማራ ፈላጭ ቆራጭነት ማብቃት አለበት የሚለውን ተቀብለው ዝም ጭጭ ያሉት ብዙ ናቸው።

▲ ብርሃኑ ነጋ የፌደራል ስርዓቱን እና ሕገመንግስቱን ለመቀየር የሚታገል የሚመስላቸው ብዙ ነበሩ ፤ በለየለት የዘረኝነት ወቅት አጡት።
▲ ብርሃኑ ነጋና መሠል ሰዎች ለሰብዓዊ መብቶች የሚታገሉ የሚመስላቸው ነበሩ፤ በሰብዓዊ ውድመት ዘመን አጡት።
▲ ብርሃኑ ነጋ እና መሰሎቹን የዲሞክራሲ ታጋዮች አድርገው የሚስሉ ነበሩ፣ በለየለት የአፈና ወቅት የሉም።

ሆኖም፣
ያልተሸወዱት፣ ነገ እነሱን ሊውጣቸው የመጣ ዘንዶ መኖሩን የተረዱት፣ ሐቀኞቹ የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ትግል ላይ ናቸው። አደጋውን እንደአማራው ሕዝብ እያዪትና እየቀመሱት በመሆኑ ትግል ላይ ናቸው።
ያለው ትግል የሴሜቲክ-ኩሽቲክ፣ የሙስሊም-የክርስቲያን፣ የሰሜን-የደቡብ ሳይሆን የኢትዮጵያውያን የፀረ-ጭቆናና ሕልውና መረጋገጥ ትግል ነው !!


ድል ለአማራ !

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
1.1K views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 19:06:00 የአማራ ኃይል ከመከላከያ ጋር እንዲዋጋ አንፈልግም፤ እንዲሁ መወጋትም አንፈልግም፤ ነገር ግን...


የምንቃወመው መንግስት፣ እኛን ለመውጋት የላከው ሌላ አካል ሳይሆን የመከላከያ ሰራዊት ወታደሮችን ነው። የተፈለገው ህግ የማስከበር ዘመቻ ቢሆን መከላከያ የሚሰማራበት አግባብ አልነበረም። ሆኖም የአብይ አስተዳደር የአቶ ግርማን ሞት ተከትሎ የወሰደው ከመጠን ያለፈ ውሳኔ [blown out of proportion] የሚባል ነው። ይህ ግን በስህተት የተፈጸመ ሳይሆን በዓላማ የተደረገ ነው።

ሁላችንም እንደምንረዳው በአማራ ክልል የተከፈተው ጦርነት አንዱ እና ዋነኛ አላማው አማራን በጉልበት በማንበርከክ ለብሔራዊ መብት እና ጥቅሙ መታገል የማይችል ደካማ እና ተለጣፊ ኃይል የማድረግ ነው። ሆኖም ጦርነቱ ካሉት ዘርፈ ብዙ መልኮች አንዱ በአማራ እና በመከላከያ ሰራዊት መካከል የተፈጠረውን የወዳጅነት ትምምን ማበላሸት ነው። ይህ ደግሞ መከላከያ በሀገራዊ ተቋምነቱ የሁሉ ጠባቂነቱ ቀርቶ ከሌላው ቀምቶ ለአገዛዙ ብቻ የሚቆም የማድረጉ ፕሮግራም አካል ነው።

መከላከያ በኦሮሚያ እና በትግራይ ክልል አሁን ደግሞ በአማራ እና ሶማሊያ ክልል በተለያዬ መልኩ ከሕዝብ ጋር ቀጥተኛ ግጭት ውስጥ እንዲገባ በማድረግ ሕዝባዊነቱን የመሸርሸሩ ተግባር ብዙ ርቀት ሄዷል።
ይህ ለእኔ ብቻ የሚለው ኬኛ ኃይል በአማራ ክልል ጦርነት ሲያውጅ በዚህ አግባብ የታሰበ እንደሆነ መረዳት ተችሏል። በዚህም ዕቅድ ምክንያት የአብይ አስተዳደርም ሆነ ጀሌዎቹ በህዝብ ሀይሎች እየቀረበ ያለውን የሰላም እና የውይይት ጥሪ ለማዳመጥ ፈቃደኞች አልሆኑም። አይሆኑም'ም።

በዚህ ጦርነት የአማራው ፍላጎት የአማራን ብሔራዊ መብት እና ፍትሃዊ ጥያቄ ማስከበር ነው። የዚህ ፍላጎት አንኳር ማጠንጠኛ ደግሞ የተጋረጠብን የህልውና አደጋ ነው። ይህ አደጋ ደግሞ ዛሬ በአማራ ክልል በተከፈተው ጦርነት የመጣ ሳይሆን ለአስርት ዓመታት የቆዬ ግን ደግሞ ባለፉት 5 ዓመታት በአስደንጋጭ ፍጥነት አድጎ እጅግ ከፍተኛ ጉዳት ያስከተለ ነው። ይህ ጦርነት የሁሉም ጥያቄዎች መልስ አይደለም፤ ሆኖም በከፋ ሁኔታ ተመትቶ ከመጥፋት ለመዳን የሚደረግ ተጋድሎ ነው። ስለዚህም ራስን ከጥቃት ከመከላከል ውጭ አማራጭ የለም።

ይህ ከመደበኛ የመንግስት ተቃውሞ የተለዬ ነው፣ ይህ ተራ ሕዝባዊ አመጽ አይደለም፣ ከዘወትራዊው የአማራ ጥቃት ከፍ ያለ አደጋን ያዘለ ነው። ስለዚህም ከማስቆም አለያም ከመመከት ውጭ አማራጭ የለም። ሆኖም ለማስቆምም ሆነ ለመመከት ሕዝቡ የመረጠው ለጥቃቱ አጸፋ ምላሽ ሰጥቶ ባለበት የማስቆም መንገድ ትክክለኛ እና የአብይ / ብልጽግና አስተዳደርን የማጥቃት ፍላጎት ሊከለክል የሚችል [ deterrence ] ስትራቴጂ ነው። ይህን ስትራቴጂ መደገፍ እና ለስኬቱ አጋዥ ሆነን መገኘት ይገባናል።

መከላከያ ጋር የተፈጠረውን የወዳጅነት ትምምን ሳይበላሽ እንዲቀጥል የቀውስ ኢንተርፕሩነሩን አስተዳደር መግታት ይገባል። አስተዳደሩ ሰላማዊም ሆነ ለአመጽ ፖለቲካ ትክክለኛ ምላሽ እንደማይሰጥ ታይቷል፤ ሆኖም ከሰላማዊ እንቅስቃሴ ይልቅ ለጉልበት የተሻለ መልስ እንደሚሰጥም ታይቷል። እናም መግባባት በሚቻልበት ቋንቋ መነጋገር ተገቢ ነውና በዚህ መንገድ መቀጠሉ አማራጭ የሌለው አካሄድ ነው።

ድል ለአማራ !

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
1.3K views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 13:39:51 ከዚህ በታች የሰፈረው ሃሳብ በአጤ ኃይለሥላሴ የሥልጣን ዘመን ስለአማራ ቀጣይ እጣ ፈንታ ለመወያየት ጉምቱ የኃይለሥላሴ ባለስልጣናት በድብቅ ተሰባስበው ነበር፤ በስብሰባቸውም ደጃዝማች ፀሐዬ የተናገሩት ሀሳብ እንደ ነብይ ያስቆጥራቸዋል። ዛሬም ድረስ በዛውን ወቅት ለተነሳው ሀሳብ መፍትሔ የሚያበጅ የአማራ ሊህቅ አልተገኘም።

ሀሳቡ ይሄ ነው፦

"የዐፄ ኃይለሥላሴ ዙፋን መዝመሙ በብዙኃኑ እየታወቀ የመጣው ፲፱፻፷ ዓ.ም ጀምሮ ነው። ለዚህ ዋና ምክንያቱ ደግሞ የጸሐፌ ትእዛዝ ወልደጊዮርጊስን አይነት በውስጥ አስተዳደር የተካነ፣ ችግር አስቀድሞ አነፍንፎ ብልሃት የሚያበጅ ባለመገኘቱ ነበር። ጸሐፌ ትእዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የተለመደውን የጎንዮሽ አሠራር አያውቁበትም፣ የሚፈልጉትም አልነበሩ።

ስለዚህ ከባህሉ ጋር የሚሄድ ዘዴ በመፍጠር ለችግሮች መፍትሔ ማቅረብ አልቻሉም። በዚህ ምክንያት የኢትዮጵያን ችግር አንድ አድርጎ የሚሰፋ አንድ ብልህ መሪ ታጣ። ይህ ሁኔታ ያሳሳባቸው የመንግሥት ባለሥልጣኖች ችግሩን ለመፍታት የሰው ለውጥ እንደሚያስፈልግ ማሰብ ያዙ። እየተባባሰ የሄደውን የፖለቲካ ትኩሳት ለማብረድም ለጊዜው አክሊሉ ሀብተ ወልድን በይልማ ደሬሳ ለመተካት ዐቀዱ፡፡ ጃንሆይ ግን ፈቃደኛ ባለመሆናቸው አክሊሉን በይልማ ደሬሳ የመተካቱ ሐሳብ ቀረ፡፡ በዚህ ዓይነት መፍትሔ ለማምጣት የሚደረገው ጥረት የማይሳካ መሆኑ እየታየ በመሔዱ ቀስ በቀስ የባለሥልጣኖቹ ስብስብ (መንዜ፣ መራ ቤቴ፣ ቡልጋ እየተባባለ) እየተቧደነ
መከፋፈል ጀመረ፡:

በዚሁ ወቅት የአክሊሉ ሀብተ ወልድ ሥልጣን አሠራር መንግሥትን አደጋ ላይ ይጥላል ብለው ይሠጉ ከነበሩት መካከል አንዱ ደጃዝማች ፀሐዩ ዕንቁ ሥላሴ በተለይ አንዳንድ አስተያየታቸውም ይታወቅ ነበርና እንደ አፈንጋጭ ይታዩ ነበር፡፡ ለዚህ ይመስላል በ፲፱፻፷፭ ዓ.ም. መጀመሪያ አካባቢ የጎንደር ተወላጅ የነበርነውን አቶ ዳኘው (ኋላ አምባሳደርና የጐንደር ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳሪ፣ ኮሎኔል ሞላልኝ በላይ ኋላ የጐጃም ክፍለ ሀገር አስተዳዳሪን እና እኔን (የኦጋዴን ልማት ዋና ሥራ አስኪያጅ) አዲስ አበባ ቀጨኔ መድኃኔ ዓለም መንገድ ላይ ካለው ቤታቸው ከተመረጡ አስተናጋጆች ውጪ ማንም በሌለበት ጋበዙን፡፡

ተጋባዦች የተመረጥነው ከኋላችን የአካባቢዎቻችን ድጋፍ እንዳለን ግምት ውስጥ በማስገባት ነበር፡፡ ድግሡ የተሟላ ሆኖ ግብዣው የተደረገበት ዋና ጉዳይም የአማራውን ሕዝብ ለማስተባበር እንድንሠራ ነበር፡፡
ደጃዝማች ፀሐዩ ‹‹ከእንግዲህ ወዲህ ማንም ቢመጣ ተነሳሁ የሚለው አማራው ሕዝብ ላይ እንጂ ለይቶ የሸዋ፣ የጐንደር፣ የጐጃም አይልም፡፡ እኛም ወደድንም ጠላንም የአማራው አንገት አንድ መሆኑን ማወቅ አለብን፡፡ ስለዚህ አማራው መተባበር አለበት›› አሉን፡፡ በዕለቱ በጉዳዩ ላይ ከተነጋገርን በኋላ እኛም የምንችለውን እንደምናደርግ ተስማምተን ተለያየን፡፡ መቼም በዚያ ወቅት ስለጉዳዩ በቀጥታ ያነጋገሩን ደጃዝማች ፀሐዩ ዕንቆሥላሴ ይሑኑ እንጂ ሌሎች ጎላ ጎላ ያሉ የሸዋ መኳንንቶችም በተገናኘንበት ጊዜ ሁሉ በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ያሻርቱን (ያባብሉን፣ ያግባቡን) ነበር። ለማንኛውም ይሄም ሐሳብ የትም የደረሰ አልነበረም፡፡"

ከገጽ 366 - 67
ማን ይናገር የነበረ...
የታህሣሡ ግርግር እና መዘዙ
ደራሲ፤ ብርሃኑ አሥረስ
አሳታሚ፦ አአዩ ፕሬስ
1.8K viewsedited  10:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 07:20:59
ከሲሳይ አየለ የምንማረው ምንድን ነው

ድሬዳዋ ላይ ሲሳይ አየለን የማያውቅ የለም። አምባገነኖችን የሚታገለው፣ ጭቆናና መድሎን እምቢ የሚለውና የሚጠየፈው ሲሳይ ሳተናው !!

ሲሳይ በድሬዳዋ የተተከለውን አፓርታይድ የታገለ እና ወጣቱን ለማታገል የአቅሙን የሠራ ጀግና ነው። እነሲሳይ ተደራጅተው መብታቸውን ለማስከበር የወጣቶች አደረጃጀት ፈጥረው ሕጋዊ ሆነው ለመብታቸው ታግለዋል። አምባገነኑ ስርዓት ግን አልፈቀደላቸውም።
እንግዳያውስ ፖለቲካ ፓርቲ ሆነን እንታገል ብለው ፓርቲም መስርተዋል። ሆኖም የነሲሳይ ውሎና አዳር እሥርቤት ሆነ። ተስፋ የሚደረግበት ለውጥም የነሲሳይን የኢሕአዴግ ዘመን ያባሰ የግፍ መንገድ ሆነ።
አሁን እነሲሳይ የምስራቅ አማራ ፋኖን በመቀላቀል ትግላቸውን በሌላ አማራጭ ጀምረዋል መባሉን ሰማን።
ታዲያ በየክልሉ ያለን አማራዎች ከዚህ ምርጥ የአማራ ልጅ የምንማረው ምንድን ነው
የሐረር ልጆች ምን እንማራለን ? የናዝሬት ልጆች ከሲሳይ ምን እንማራለን? የሐዋሳ ልጆች ከሲሳይ ምን እንማራለን!? የጅማ ልጆች ምን እንማራለን!?
ጭቆና እና ጨቋኝ ብትሸሸውም ፣ ዝም ብትለውም አይተውህም!!
ማሰብ፣ መደራጀት፣ መሰልጠን፣ መመራመር፣ መታገል የዘመናችን ግዴታ ነው!! የእኛ ትውልድ እንዲህ እንዲኖር የታሪክ አንጓ ወስኖብናል ከመታገል በቀር አማራጭ የለንም!!

ድል ለአማራ !!

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
1.8K views04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ