2022-08-31 08:53:10
ጳጉሜን በመደመር!!
ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃድ ቀን!!
- የተመረጠበት ምክንያት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ባህል እየሆነ የመጣዉንና ከፍተኛ ዉጤት የተገኘበት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እሴትን ይበልጥ ለማጠናከር ነዉ፡፡
• እለቱ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮጀክት እንዲሳካ ያደረገ፣ በዙ አቅመ ደካሞችን የቤት ባለቤት ያደረገ፣ በደም ዕጦት ሲያልፍ የነበረዉን ህይወት ለመታደግ ያስቻለ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራን ይበልጥ ባህል በሚያደርጉ ተግባራት ይከበራል፡፡
• እለቱ ት/ቤቶችንና መኖሪያ አካባቢዎችን በማፅዳት፣ ደም በመለገስ፣ አቅመ ደካሞችን በማጋዝና በመሳሰሉት ተግባት ይከበራል፡፡
ጳጉሜ 2 የአምራችነት ቀን!!
ዓላማዉም በግብርና፣ በኢንደስትሪ፣ በትራንስፖርና ሎጂስቲክስ ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችና ተግዳሮቶችን በመለየት ለቀጣይ ዓመት በቂ ዝግጅት ለማድረግ ነዉ፡፡
ጳጉሜ 3 የሠላም ቀን!!
"ሠላም ለኢትዮጵያ"በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡
• ዓላማዉም ለሰዉ ልጅም ሆነ ለአገራችን ሠላም እጅግ አስፈላጊ ሆነ ጉዳይ መሆኑን ለማስገንዘብና የሠላም እሴት ለማድረግ ነዉ፡፡
• እለቱ በማህበረሰብ ደረጃ እርቅ በማዉረድ፣ የሠላም እሴቶችን በማስተዋወቅና በመሰል መርሃ-ግብሮች ይከበራል፡፡
ጳጉሜ 4 የአገልጋይነት ቀን!!
"አገልጋይነት ከእኔ ይጀምራል" በሚል መሪ ቃል የሚከበር ይሆናል፡፡
• የአገልጋይነት ቀን መከበር ዓላማዉ በሁሉም የግልና የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ተገልጋይ የተሳለጠ አገልግሎት እንዲያገኝና ሁሉም ሠራተኛና አመራር የማገልገል ቃልክዳኑን የሚያድስበትና በአዲሱ ዓመት ሁሉም አካላት ለተሻለ አገልግሎት አሰጣጥ እንዲዘጋጅ፣ ለበለጠ አገልግሎት ቃል የሚገቡበት ዕለት እንዲሆን ነዉ፡፡
• ዕለቱ ሁሉም ሠራተኛና አመራር ከደረጃዉ ዝቅ ብሎ አገልግሎት በመስጠት፣ የፅዳት ሥራን በማከናወን፣ ነፃ አገልግሎት በመስጠትና በተያያዝ ተግባራት ይከበራል፡፡
ጳጉሜ 5 የአንድነት ቀን!!
• የአንድነት ቀን መከበር ዓላማዉ ለዘመናት የቆየዉ የኢትዮጵያ እንድነትና ሉዓላዊነትን ለማስከበር የተከፈለዉን መስዋዕትነት በመዘከር ፤ አሁንም አገራችን ፈተናዎችን እየተሻገረች አንድነቷን ጠብቃ እየተጓዘች እንዳለች እና ቀጣይም በልጇቿ መስዋዕትነትና ጥረት አንድ ሁና እንደምትቀጥል ለማሳየት ነዉ፡፡
• የአንድነት ቀን መከበር አስፈላጊነቱ እንደ ሕዝብና አገር ህልዉናችን የሚረጋገጠዉ፣ ክብራችንና ነጻነታችን ዘላቂ የሚሆነዉ አንድ ሆነን ስንቆም ብቻ መሆኑን ለማስገንዘብና የአንድነታችን እሴቶችን ለማጎልበት ነዉ፡፡
• የጥንካሬያችን ምንጭ አንድነታችን መሆኑን፣ ጠላቶቻችንን ከጥንት እስከ ዛሬ እያሸነፍን የመጣነዉ አንድ ሆነን በመቆማችን እንደ ሆነ ለማስገንዘብ ጭምር ነዉ፡፡
• ዛሬም በብዙ ፈተናዎች ዉስጥ እንገኛለን፣ ለታሪካዊ ጠላቶቻችን የሚላላኩ በአሸባሪዉ ወያኔ ለ3ኛ ጊዜ የተወረርነበት ጊዜ ዉስጥ እንገኛለን፡፡
• ይህንን ወረራ በድል የሚኛጠናቅቀዉና ዘላቂ ሠላማችንን የምናረጋግጠዉ አንድ ስንሆን ብቻ ነዉ፡፡
• ጠላቶቻችን በብሔር፣ በኃይማኖትና በሰፈር ከፋፍሎን ሊያንበረክኩን ብዙ ለፍቷል፣
• የዉጭ ጠላቶችና የዉስጥ ባንዳዎች ግንባር ፈጥሮ ዘምቶብናል፣ ዘመቻዎቻቸዉን በድል የምንወጣዉ አንደነታችንን በማጠናከርና በአንድነታችን የተጎናፀፍናቸዉን ድል ለመዘከር ዕለቱ ዓይነተኛ ሚና ይጫወታል፡፡
1.4K views05:53