Get Mystery Box with random crypto!

ሽፈራው የሶማው

የቴሌግራም ቻናል አርማ rasmeried — ሽፈራው የሶማው
የቴሌግራም ቻናል አርማ rasmeried — ሽፈራው የሶማው
የሰርጥ አድራሻ: @rasmeried
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.22K
የሰርጥ መግለጫ

የአማራ ሕዝብ የሕልውና የፍትህ እና ርትዕ ትግል ትክክልና ድል መጎናፀፍ ያለበት ነው።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-16 12:55:00 የብርሃኑ ጁላ ፡ የፋኖ እና ሸኔ ሚዛን

ብርሃኑ "ሁለት ጫፎች " በማለት ፋኖ እና ሸኔ እኩል ጠላቶች አድርጎ ፣ እኩል አጥፊዎች አድርጎ በጥላቻና በሴራ የታጨቀውን ንግግሩን ሲያወርደው አመሸ።
የረባ ትምህርት የሌላቸውን እና የዝቅተኛ ስነልቦና ስሪት የተሠራባቸውን ብዐዴኖች እንጂ አማራን ሊያሳምን የማይችል ድብቅ ጥላቻውን ነው ያጎረፈው።

የፋኖን ኃጥያት ሲዘረዝር ያልጠቀሰው ወንጀል የለም። ሴት ይደፍራል ፣ ታክስ ይሰበስባል፣ ይገድላል፣ መንገድ ይዘጋል፣ የዘርፋል.... ያላለው የለም።

ስለእሱው ሸኔ ሲደናገር ግን ትልቁ የሸኔ ጥፋት ወደ አዲስአበባ እገባለሁ ብሎ አፍንጫችን ስር መምጣቱ ነው አለ። የጅምላ ግድያው ፣ ከወለጋ እስከ አጣዬ ያለው ጭፍጨፋው ፣ ማገቱ ፣ በሰው እገታ ገንዘብ መጠየቁ ፣ ባንክ መዝረፉና ንብረት ማውደሙ ፣ ሚሊዮኖችን ማፈናቀሉ አልጠቀሰውም።
አይጠቅሰውም!!
ትልቁ ድልም ሸኔን ወደኋላ ገፍቶ ጫካ አስቀምጦ "ጉሬላ ኃይል" መደረጉ እንደሆነ ተናገረ።
ያሠማራውን ኃይል እንዴት ብሎ ኃጥያቱን ይጠቅሰዋል?
ብርሃኑ ተገልጦ ነው ያመሸው!!
ዘረኛነቱ ፣ ፀረ-አማራነቱ ፣ ክንብንቡ ተገልጦ ነው ያመሸው።
በዚህ አያያዙ ከአማራ የወጡ ወታደራዊ መኮንኖች ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። ጥቅምት 24ን ያየ በማን ጠባሳ ይቀልዳል?
ሁሉም ነገር ስልጣንን ስለመጠበቅና ባላንጣን ጉልበበት ስለማሳጣት እንጂ ስለህዝብ ሰላም ተብሎ እንደማይሠራ የተገለፀልን ብዙዎች ነን።


ድል ለአማራ

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
474 viewsedited  09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 12:44:22
423 views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 12:44:07 የጃልመሮን ያህል ማስመሰል አልቻለም!

ጃልመሮ የአራጁ "ኦነግ ሸኔ" መሪ ነው። ሚዲያ ላይ ሲቀርብ ግን የሆነ ሲቪክ ተቋም መሪ ይመስላል። ጥላቻውን፣ አረመኔነቱን ለመደበቅ ይጥራል።

ይህኛው ኢታማዡር ሹም ሆኖ ጥላቻውን መደበቅ አልቻለም። በአገር ስም ይህን ሁሉ ኮከብ ደርድሮ ስለ ልዩ ጥቅም ከሚያወሩት ፖለቲከኞች የከፋ ጥላቻና አስተሳሰብ የታጨቀበት ሰው ነው።

በሁለተኛው ዙር ሰራዊቱ ትግራይ ውስጥ በህዝብ ተከብቦ ሲመታ ብርሃኑ ጁላ ናዝሬት ላይ ለኦህዴድ ስለ ልዩ ጥቅም ይሰበስብ ነበር። ምሳሌ ለመጥቀስ ያህል የጉራጌ ባለሀብቶችን ሰብስቦ "አዲስ አበባ ላይ አማራ እንዳያሸንፈን አግዙን" ብሎ "እኛ እንዲህ አናደርግም" ብለውታል።

ትናንት መጥቶ አንድ ወንበዴ የማያስበውን በሚዲያ ሲናገር ነበር። "ፋኖ ልዩ ኃይሉን ገደለው" ብሎ ሀሰት ሲያወራ ነበር። ሀሰት የለመዱት ነው። ይህኛው ሀሰት ግን አማራ ክልል ላይ መፍጠር የፈለጉት ትርምስ አካል ነው። አማራ እርስ በእርሱ እንዲጋጭ ያላቸውን እቅድ ነው የነገረን። እውነታውማ ልዩ ኃይሉ የተመታው ከሚሴ ላይ ነው። ይህን ትንፍሽ አይልም።

ብርሃኑ ጁላ በዚህ ሀሰቱ እንደ አገር ሰራዊት መሪ ሳይሆን የተገንጣይ ቡድኖች አማራ ክልል ላይ የሚነዙትን ነው የአገር ሰራዊት መሪ ሆኖ እየሰራበት ያለው።

እንዳልኳችሁ! ጃል መሮ የሚባለውን የገዳይ ቡድን መሪ ፀጉሩን ተቆርጦም ሳይቆረጥም ዛሬውኑ በዚህ ሰውዬ ቦታ ቢያስቀምጡት የተሻለ ማስመሰል፣ ጥላቻውን መደበቅ ይችላል።

አስቡት! የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መሪ ተብሎ ጥላቻውን እንዲህ የሚያዘንበው ሰው አንዲት ተገንጣይ ፓርቲ ቢመሰርት! በቀለ ገርባ ማረን ያስብላል!
ሰራዊቱን የትም ትቶ ስለ ልዩ ጥቅም ሲያወራ እየዋለ ለአገር የቆመን ልዩ ኃይል ሊያወግዝ ይሞክራል። ሰውዬው የሚያወራው የግሉን አይደለም። ምሽት በሞቅታ ከልዩ ጥቅም ፖለቲከኞች ጋር ያወሩትን ሳይቀር ነው ሚዲያ ላይ አምጥቶ የሚደፋው። በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማያውቅ መዓረግ አሸክመውት እሱ ግን ቅሌቱ ነው የሚያበዛው። ከእሱ ተራ ወታደሩ ስነ ምግባር አለው። የአሸባሪው መሪ ጃልማሮ ጨፍጭፎም ሚዲያ ላይ ከእሱ የተሻለ ቃላትን ተጠቅሞ ይዋሻል።

(በጌታቸው ሽፈራው)
413 views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 11:14:26 ሕገ መንግሥቱ በመንግሥት እየተጣሰ ነው ስንል ያለምክንያት አለመሆኑን ጥቂት ምሳሌዎችን በመጥቀስ እንዳስረዳ እስኪ፦
[  ] አንቀጽ 10 (2) - “የዜጎች እና የሕዝቦች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ይከበራሉ፡፡” ይላል። እውነታው ግን፤ ሕግ አስከባሪ ፖሊሶች የግለሰቦችን ሰብዓዊ መብት በአደባባይ ይጥሳሉ። ሰዎች በፖለቲካዊ አመለካከታቸው ማኅበራዊ፣ ስነልቦናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ የሚገቡበት አጋጣሚ ተባብሶ ቀጥሏል።

[  ] አንቀጽ 12 (1) - “የመንግሥት አሠራር ለሕዝብ ግልጽ በሆነ መንገድ መከናወን አለበት” ይላል። እውነታው ግን፤  የተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ለየትኛውም የግል መገናኛ ብዙኃን በራቸውን ዘግተው ጥያቄ የሚያስነሱ ጉዳዮች ላይ ሕዝቡ መልስ ከማግኘት ይልቅ በአሉባልታዎች ቅብብል እንዲደናበር ተጨማሪ እንቅፋት እየሆኑ ነው፡፡ 
[  ] አንቀጽ 20 (3) - “[የተከሰሱ ሰዎች] በፍርድ ሒደት ባሉበት ጊዜ በተከሰሱበት ወንጀል እንደጥፋተኛ ያለመቆጠር፣ በምስክርነት እንዲቀርቡ ያለመገደድ መብት አላቸው” ይላል። እውነታው ግን፤ በመንግሥት የሚተዳደሩት ሚዲያዎች እና ባለሥልጣናትም ጭምር፣ በተለያዩ ጊዜ ክስ የተመሰረተባቸውንም ያልተመሰረተባቸውንም ጋዜጠኞች እና ሌሎችም ተቃዋሚዎች ያውም ‹‹በሽብርተኝነት›› የመወንጀላቸው ነገር የማያቋርጥ የእለት ተእለት ድራማ እየሆነ መጥቷል፡፡

[  ] አንቀጽ 21 (2) - “[የታሰሩ ሰዎች] ከትዳር ጓደኞቻቸው፣ ከቅርብ ዘመዶቻቸው፣ ከጓደኞቻቸው፣ ከሃይማኖት መሪዎቻቸው ጋር ለመገናኘትና እንዲጎበኟቸውም እድል የማግኘት መብት አላቸው” ይላል። እውነታው ግን፤ የማረሚያ ቤት ኃላፊዎች የፈለጉትን ሰው ጠያቂ እንዳይኖረው፣ ወይም የሚጠይቁትን ሰዎች ማንነት የመገደብ ሥራ በገዛ ፍቃዳቸው በየጊዜው እየፈጸሙ ይገኛሉ፡፡ 
[  ] አንቀጽ 29 (2) - “ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሐሳቡን የመግለጽ ነጻነት አለው፡፡ ይህ ነጻነት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ውስን ሳይደረግበት በቃልም ሆነ በጽሑፍ ወይም በሕትመት፣ በሥነ ጥበብ መልክ ወይም በመረጠው በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ፣ ማንኛውንም ዓይነት መረጃና ሐሳብ የመሰብሰብ፣ የመቀበልና የማሰራጨት ነጻነቶቸን ያካትታል፡፡” ይላል። እውነታው ግን ፤ይህ እንቀጽ በአሁኑ ሰዓት በገደል ጫፍ ላይ ቆሟል፡፡ ጋዜጦች ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ እየታገዱ ነው፤ ማተሚያ ቤቶች በተለይ የፖለቲካ ጋዜጦችን እየመረጡ እንዳያትሙ በመንግሥት ባለሥልጣናት ጫና እየደረሰባቸው ነው፣ ድረገጾች እና ጦማሮች ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይነበቡ እየተደረገ ነው፡፡
[  ] አንቀጽ 29 (5) - “በመንግሥት ገንዘብ የሚካሄድ ወይም የመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያለ መገናኛ ብዙኃን የተለያዩ አስተያየቶችን ለማስተናገድ በሚያስችለው ሁኔታ እንዲመራ ያደርጋል፡፡” ይላል። እውነታው ግን፤ የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እና የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በመንግሥት የሚተዳደሩ ድርጅቶች ሆነው ሳሉ የገዢውን ሐሳብ ብቻ የሚያንፀባርቁ፣ በአንድ ወገን ዘመም ይዘቶቻቸውና የሕዝብን እውነታ በማፈን የሚታወቁ መገናኛ ብዙኃን ሆነዋል፡፡
[  ] አንቀጽ 40 (4) - “የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች መሬት በነጻ የማግኘትና ከመሬታቸው ያለመ[ፈ]ነቀል መብታቸው የተከበረ ነው፡፡” ይላል። እውነታው ግን በልማት እንም ዘመናዊ ከተማ ልንገነባ ነው በሚል ሰበብ በተለይም በአዲስ አበባ እና በአዲስ አበባ ዙሪያ ነዋሪዎች ቤት የማፍረስ እና የማፈናቀል ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል።
[  ] አንቀጽ 79 (2) - “በየትኛውም ደረጃ የሚገኝ የዳኝነት አካል ከማንኛውም የመንግሥት አካል፣ ከማንኛውም ባለሥልጣን ሆነ ከማንኛውም ሌላ ተጽእኖ ነጻ ነው፡፡…”  ይላል።እውነታው ግን፤  ፍርድ ቤቶች ነጻነት ላይ ሕዝቡ ያለው እምነት ከእለት እለት እየተሸረሸረ ነው፡፡ ነጻ ፍርድ ቤቶች አሉ ብሎ የሚያምን እየጠፋ ነው፡፡
[  ] አንቀጽ 87 (1) - “የሀገሪቱ የመከላከያ ሠራዊት የብሔሮች፣ የብሔረሰቦች እና የሕዝቦችን ሚዛናዊ ተዋጽኦ ያካተተ ይሆናል፡፡”  ይላል። እውነታው ግን፤ ይሄ እውነት ነው በሚለው ላይ የሚስማሙ ሰዎች ማግኘት ይቸግራል፡፡ ሠራዊቱ በአንድ ብሔር አባላት የበላይነት እንደተያዘ ብዙዎች ይስማማሉ፡፡ ይባስ ብሎ ችግሩን ቀስበቀስ ለመቅረፍ ሲሞከር አይስተዋልም፡፡
[  ] አንቀጽ 89 (2) - “መንግሥት የIትዮጵያውያንን የኢኮኖሚ ሁኔታዎች ለማሻሻል እኩል እድል እንዲኖራቸው ለማድረግና ሀብት ፍትሐዊ በሆነ መንገድ የሚከፋፈልበትን ሁኔታ የማመቻቸት ግዴታ አለበት፡፡”  ይላል። እውነታው ግን፤  ዛሬ ዛሬ በሀብታሞች እና ድሆች መካከል ያለው የኢኮኖሚ ልዩነት እጅግ እየተጋነነ መጥቷል፡፡ ዜጎች ሀብት ለማፍራት እኩል እድል አላቸው ብለው የሚያምኑ እጅግ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ስደተኛ ወጣቶች በድንበር እያሳበሩ ለሞት እስከመጋለጥ የሚደርሱት ድህነት እየገፋቸው ነው፡፡ ጉዳዩ በጣም የከፋ ቢሆንም መንግሥት ይህንን ኃላፊነቱን ለመወጣት የሚሠራው ሥራ አይታይም፡፡
[  ] አንቀጽ 89 (6) - “የሀገር ልማት ፖሊሲዎችና ፕሮግራሞች በሚዘጋጁበት ወቅት መንግሥት ሕዝቡን በየደረጃው ማሳተፍ አለበት፡፡ የሕዝቡንም የልማት እንቅስቃሴዎች መደገፍ አለበት፡፡” ይላል። እውነታው ግን፡- በአገራችን አዋጆች ከወጡ በኋላ ማሳወቅ እንጂ የሚመለከታቸው አካላት ረቂቁን በማውጣት ቀርቶ፣ የወጣው ረቂቅ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ የሚደረግበት ልምድ ፈፅሞ አልተዘረጋም፡፡
[  ] አንቀጽ 89 (8) - “መንግሥት የሠራተኛውን ሕዝብ ጤንነት፣ ደህንነትና የኑሮ ደረጃ ለመጠበቅ መጣር አለበት፡፡”  ይላል። እውነታው ግን፤  ሠራተኛው የሕዝብ ክፍል ወር ጠብቆ በሚያገኛት ምንዳ ለመኖር በሚያደርገው መፍጨርጨር የኑሮ ውድነት መስዋዓት እየሆነ ነው፡፡ መንግሥት በየጊዜው እያሻቀበ የመጣውን የዋጋ ግዥበት ለመቆጣጠር ለማዋል ሥር ነቀል እርምጃ አልወሰደም፡፡ በዚህም የሠራተኛው ሕዝብ ደህንነት አደጋ ላይ ተንጠልጥሏል፡፡
410 views08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 09:47:49
ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ በተነሳባት በዚች ዕለት በግፍ እስር ለምትገኙ ጀግኖች ወንድም እህቶቻችን መልካም የትንሳኤ በዓል!!
447 views06:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 17:31:16
766 views14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 17:30:37 የኦሮሙማ የጥቃት አድማስ እና የአማራው ምርጫዎች፤

የኦሮሙማ ፕሮጀክት አስፈፃሚዎች አማራውን አስጨፍጭፈውትም፣ አፈናቅለውትም፣ በአገሩ ስደተኛና ተፈናቃይ አድርገው በየድንኳኑ አስፈርውትም አልረኩም።
ጭፍጭፈውና አፈናቅለው በየጎዳናው ለማኝና ተመፅዋች አድርገውትም ፣ በሰሜኑ ጦርነት ውድመቶች ተጨፍጭፎ እና ወድሞላቸውም አልረኩም።
አማራውን በማፈን ፣ የመንቀሳቀስ እና ሠርቶ የማደር መብቶቹን ሁሉ ነፍገውትም ፣ የኢትዮጵያን እሥርቤቶች በአማራ ልጆች ሞልተውትም አልረኩም።
ዛሬም በወለጋ እያስጨፈጨፉት ነው፣ በዚህ ወቅት በምስራቅ አማራ እያስገደሉት ነው፣ ልክ በዚህ ወቅት በአዲስአበባ ዙሪያ ቤቱን እያፈረሱ እያፈናቀሉት ነው።

በዚህ ወቅት አገረ- መንግስቱን ከውድቀት የታደገውን የአማራ ልዩ ኃይል እያሳደዱት ነው፣ እየገደሉት ነው። በዚህ ወቅት በአዲስአበባ እንዳይመቸውና እንዳይረጋጋ የሚያደርጉ የጥቃት መስኮች ከመንገድ ላይ ትራፊክ እስከ ቢሮክራሲ እያሰቃዩት ነው።

ይሔ ሁሉ ግን ሊያደርጉት ከሚፈልጉት አንፃር ፣ ገና እረፍት የሠጣቸው አይደለም። ኦሮሚያ ላይ ትርጉም በሌለው መልኩ ሀብትና ንብረቱን ጥሎ እስከሚወጣ ፣ የኦሮሞ ከተሞችን ከአማራ እስከሚያፀዱ ፣ አዲስአበባን የኦሮሞ ንብረት የማድረግ ሕልምን ለማሳካት እና ኦሮሞ የሚዘውራትን አገር እውን ለማድረግ አማራን ቋሚ ተሸናፊ ለማድረግ የሚያስችሉ ቋሚ ቀውሶች እና ጥቃቶች ገና ይቀጥላሉ !!

▸ ትግራይን ቀጥቅጠን ወያኔ የፈለግነውን ስምምነት እንዲፈፅም፣ የምንለውን እሺ ብሎ የሚቀበል ፣ የሾምንለትን አሜን የሚል እንዳደረግነው ፤ አማራም አሜን ብሎ እንዲገዛ በሚያደርግ መልኩ እንደቁሰዋለን ብለው ተነስተዋል። ወያኔ 27 ዓመት በገዛበት አገር ፣ አማራው የኦሮሞን በ5 አመት የስልጣን ተቀናቃኝ በመሆኑ መስበር አለብን ብሎ ተነስቷል።

▸ ወያኔን ከአማራና ኤርትራ ጋር ሆነን እንደሰበርነው ፣ አማራን ከትግራይና ከሱዳን ጋር ሆነን እንሰብረዋለን የሚል ስሌት ይዞ ፡ ነገሮችን እያስተባበረ ይገኛል።

▸ የአማራን ወታደራዊ አቅሞች ሁሉ አሟጦ የማጥፋት ጥረት ልዩ ኃይልን በመቀተን ፣ ፋኖን በማጥፋት ፣ መሣሪያ በመንጠቅ አያበቃም። በጦርነቱ ሰበብ በከፍተኛ መጠን ወደመከላከያ የገባውን አማራ በፅንፈኛነት ፣ ከብዛት ይልቅ ጥራት በሚሉ ሰበቦች ፣ በጡረታ እና በልዩ ልዩ ሰበቦች ጠርጎ ያስወጣዋል። ለኦሮሙማ ፍላጎት ያደረ ታዛዥ ከመሆን ያለፈ ሚና አይሰጥም።

▸ በአገሪቱ ብቻ ሳይሆን በቀጠናውም ከአማራው ጎን የሚቆሙ አካላት እንዳይኖሩ ለማድረግ ሁሉንም ክልል ስጋትና ፍርሃት ውስጥ መክተት ላይ እየተሠራ ነው። ከአማራው ጋር አብረው የሚቆሙ እንዳይኖሩ ብቻ ሳይሆን አማራውም በራሱ አብሮ እንዳይቆም ለማድረግ የሚያስችሉ ከፋፎሎ የመቆጣጠር (Divide and conquer) ፣ ከፋፍሎ የመግዛት (devide and rule) እና መርጦ የማስተናገድ (selective accomodation) ስልቶችን በመከተል መከፋፈል ላይ በስፋት ተሠማርተዋል።

▸ በቀጣይ የሚመጣውን የቤትና ሕዝብና ቤት ቆጠራ የእነሱን ታላቅነት የአማራን ትንሽነት አረጋግጦ እንዲጠናቀቅ ለማድረግ የሚያስችለው ሥራ የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ መሥሪያቤትን የያዘው የበከር ሻሌ ቡድን እጅግ ከፍተኛ ሥራ እየተሠራ ነው። በኦሮሚያ ያለ አማራ ፡ ማንነቱን ክዶ በእነሱ ማንነት የመቆጠር አሊያም የመባረር አማራጭ ይደርሰዋል። እነሱን ነኝ ብሎ ባይቆጠርም ስሌቱ ከወዲሁ እያለቀ ነው። እነሱን ነኝ ማለትም በቀጣይ ምዕራፍ ዘሩ ተቆጥሮ ከመባረር አይድንም። ቋንቋ መናገር እንኳ እንደማያስጥል በተደጋጋሚ ታይቷል።

▸ የአማራ ባለሀብቶች በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ገንዘብ እንዲያወጡ ማድረግ ፣ የኦሮሞ ባለሀብቶችን ግን ከፍተኛ የገንዘብ ድጎማ በመስጠት ኢኮኖሚውን እንዲቆጣጠሩ ለማድረግ የሚያስችሉ ለእነሱ አመቺ የሕግና የአሠራር ማሻሻያ ማድረግ፣ እንደኮንስትራክሽን ያሉ ዘርፎችን እንዲቆጣጠሩ ማስቻል ፣ የአገሪቱን ግዢዎች ወይ ከኦሮሞዎች ወይ በኦሮሞዎች እንዲፈፀሙ ማስቻል የመሠሉ ሥራዎች እየተሠሩ ነው።

▸ በዚህ ሒደት ውስጥ በሚድያ የሚተቹትን ፣ የሚያጋልጡትን እና ሕዝቡን የሚቀሰቅሱትን አክቲቪስቶች ፣ የሚድያ ሙያተኞች ፣ ፖለቲካዊ አስተያየት ሰጪዎች ሁሉ እያደኑና እያዋረዱ ማገት እና ማሠር የማስፈፀሚያ ስልት ተደርጓል። ከአማራው ወግኖ የሚናገር የሌላ ብሔር ተወላጅ ደግሞ አፉን እንዲዘጋ የሚያደርግ እርምጃ እንዲወሰድበት በተወሰነው መሠረት ሲደበደቡና ሲታፈኑ ቆይተዋል፣ ይቀጥላል። ይሔንን አላማ ለማሳካት ደግሞ ልክ እንደ ኢ-መደበኛ ታጣቂው ፣ በኢ-መደበኛነት የሚያፍን፣ የሚደበድብ እና የሚዘርፍ ቡድን ተደራጅቷል።

▸ በፌደራል እና የአዲስአበባ ተቋማት ያለውን አማራ መቀነስና ማባረር፣ ቀኑን የሚጠብቅ የማይቀር አላማ ነው። አዲስአበባን አላስፈላጊ ማድረግ የሚለውም በኑሮ ውድነት ጠብሶ ማስወጣትን ጨምሮ፣ ድሆች የሚሠማሩባቸውን የንግድ ሥራዎች ከማወሳሰብና ከማገድ ጋር ተያይዞ የሚቀጥል ነው። በአድር-ባይነት የወገኑን ጥቃት የካደ የአማራ ሲቪል ሠርቫንት፡ ወገኑን መካዱ አያስቀረውም።

▸ በኦሮሚያ ከተሞች እና ዞኖች የሚኖረው አማራ፣ እስከዚያው የሚፈፀምበት ጥቃትና ማሸማቀቅ እንዳለ ሆኖ፡ የአዲስአበባ ጉዳይ ሲጠናቀቅ የሚመለሱበት አጀንዳ ነው። በአዲስአበባ ዙሪያ እንዳደረጉት፣ "ፌስታልህን ይዘህ እንደመጣህ፡ ከእነፌስታልህ ባዶ እጅህን ነፍስህን ይዘህ ከተመለስክ ይበቃሃል" ተብሎ ፣ ያፈራው ሀብትና ንብረት የሚወረስበት ወይም የሚገደልበት ጊዜ ሩቅ አይደለም። የኦሮሙማ ፕሮጀክት ያስገድዳልና ።

▸ በወገናቸው ላይ ሊመጣ የሚችልን አደጋ ለመተንበይና ለመከላከል ይቅርና እየተፈፀመ ያለውን ጥቃት እና ጥፋት ለመቀነስም ለማስቀረትም ያልፈቀዱ እና የማይችሉ፣ ይልቁንም የቀደሙትን ሁሉ በሚያስመሰግን ግፍ እና ክሕደት ወገናቸውን በማጥቃት ላይ የተሠማሩ አድር-ባይ የአማራ ወኪል አመራሮች እንደትናንትናዎቹ የለውጥ አወዳሽ ተባራሪዎች፣ አሁን ያሉትም ቀንበሩ እንደከበዳቸው ምልክት ያሳዩ ቀን በሌሎች መሠል አድርባዮች ይተካሉ። በሕዝባቸው ውርደት ለማጌጥ የተሰለፉ እና አማራን የሚያሳድዱ ሁሉ እንደአገዳ ተላምጠው የሚሸኙበት ቀን ይመጣል።

▸ እነዚህ ሁሉ ሒደቶች ፡ ጠላት ድልን ከተጎናፀፈ አማራ የሚባለውን ግዛት እንኳ ጠብቆ መቀጠል ወደማይችልበት መቀመቅ ማውረድ የጠላት አላማ ነው።
አልደበቁንም!!
አማራ የሚባል ሕዝብም ክልልም የለም ብለዋል!!
የዛሬ 500 ዓመት የረገጥነውን ሁሉ በዚህ ዘመን እንጠቀልላለን ብለዋል።


የአማራ አማራጮቹ ሁለት ብቻ ናቸው!!

1) በቋሚ ተሸናፊነት ጠላት የሚወስንልህን እየተቀበሉ የባርነትና ተንበርካኪነት ኑሮ መኖር፤

2) አማራዊ ሕልውናን ለመታደግ በሚያስችል ሁሉንአቀፍ ትግል ተሠማርቶ ታሪኩን እና ማንነቱን የሚመጥን ልዕልናውን ማረጋገጥ!!


ድል ለአማራ !

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
563 views14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 15:29:07
‹‹በሚዲያ የአማራ ሕዝብ ግፍ ደርሶበታል ብለህ ሕዝቡን አነሳስተሀል›› ሲል ፖሊስ ወነጀለ!

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርቧል። ጋዜጠኛው የአማራ ሕዝብ ግፍ ደርሶበታል በማለት መንግስትን አስገድዶ ከስልጣን ለማውረድ በሚዲያ ሲንቀሳቀስ ነበር። ተከባብሮ የሚኖርን ሕዝብ ለመለያት ሲሰራ ነበር የሚል ክስ የቀረበበት ሲሆን፤ ለተጨማሪ ማጣራት 14 የምርመራ ተን ታስሮ ይቆይልን ሲል ፖሊስ ጠይቋል።

የጋዜጠኛው ጠበቆች በበኩላቸው ፤ የሚዲያ ባለሙያ ታስሮ የሚጣራበት የሕግ አግባብ የለም ስለዚህ የዋስትና መብቱ ተከብሮ በዋስ ይለቀቅ›› ሲሉ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል። አክለውም -ደንበኛችን ከሕግ አግባብ ውጪ ፍርድ ቤት ሳይቀርብ 48 ሰዓት አልፎታል፤ የመብት ጥሰት ተከናውኖበታል ሲሉ ፖሊስን ከሰዋል። ፖሊስም ‹‹ከባህርዳር መከላከያ ነው የያዘው፤ ከነሱ እስክንረከብ ነው ጊዜ የሄደብን›› የሚል ምላሽ ለፍርድ ቤቱ ሰጥተዋል።

በመጨረሻ፣ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ በጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ላይ የ10 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል። በተያያዘ ዜና የኢትዮ ሰላም ሚዲያ ባለቤት የሆነውና ከጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ጋር በአንድ መዝገብ የተከሰሰው ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው፤ በተመሳሳይ ክስ የተከሰሰ ሲሆን፤ የአስር ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶበታል። ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በአሁኑ ሰዓት ከሌሎች ጋዜጠኞች ጋር በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ጊዜያዊ እስረኛ ማቆያ በእስር ላይ ይገኛል፡

ተጨማሪ መረጃዎችን ከኢትዮ 251 የተለያዩ የመረጃ መረቦች ያግኙ፦

ዩቱዩብ https://youtube.com/c/ETHIO251MEDIA
በቴሌግራም https://t.me/ethio251media
በፌስቡክ https: https://www.facebook.com/ethio251media/
493 views12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 15:27:56
የችሎት  ዜና!

ዛሬ በቀን 7/ 08 /2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው አለም እና ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው የቀረቡ ሲሆን  የሚዲያ ፈቃድ ሳይኖራቸው ህገወጥ ሚዲያ በመክፈት ሁከት እና ብጥብጥ በመፍጠር ተጠርጥራችኋል በሚል የቀረቡ ሲሆን በ1ኛ ተከሳሽ ቴዎድሮስ አስፋው እንዲሁም በ2ኛ ተከሳሽ ዳዊት በጋሻው የ10 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

ምንጭ : ግዮን አማራ


ድል ለአማራ !

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
631 views12:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 13:51:23 በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የእነዚህን ሁለት ቦታዎች ችግር በህገ መንግስቱ መሰረት ይፈታሉ ከማለት አልፎ ይህ ማለት ቦታዎቹን ለትግራይ ጊዜያዊ አሰተዳደር ማስረከበ መሆኑን ወይም ሌላ መንገድ እንዳለው ግልጽ አላደረገም። ይህ ግልጽነት የሌለው አቋም ከላይ ከተጠቀሰው የወያኔዎች ትጥቅ አለመፍታት ጋር ተደመሮ የአማራ ልዩ ሃይል እንዲበተን የተደረገው እነዚህ ቦታዎች ለትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አሳልፎ ለመስጠት ነው ከሚል መደምደሚያ ላይ በመድረሱ ህዝብ ስጋት  ውስጥ ገብቷል።

በትናንትናው ዕለት ብቻ 05/08/2015 ዓ/ም  ከምሽቱ 12.25 ጀምሮ ሰአት ከኦረሞ ብሄረሰብ ዞን ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ  ጓዳ ፣በጤ፣ገርቢ ባልጪ እና ኤፍራታ ግድም ወረዳ ጀውሀ ቀበሌዎች የኦሮሞ ታጣቂዎች አማራ ሲቪል  እና የልዩ ሃይል አባላትን ተሳፋሪዎችን ከመኪና  እያስወረዱ እጅግ አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ እየገደሉ ነበር። ወያኔ ትጥቁን ባልፈታበት ከእነዚህ አካላት ጋር እጅና ጓንት ሆኖ እየሰራ ባለበት፣ ትግራይ ውስጥ ለእነዚህ ሃይሎች ማሰልጠኛ ይሆን ዘንድ የከፈታቸውን ካምፖች ባልዘጋበት፣ ስልጠና መስጠት ባላቆመበት ወቅት፣ የአማራን ህዝብ በዚህ መንገድ እስከ ጥርሳቸው ከታጠቁ ሃይሎች ጋር የሚያደርገውን የራስ መከላከል ስራ የሚሰራለት ልዩ ሃይል ይፍረስ ማለት የአማራን ህዝብ መናቅ ነው።




ድል ለአማራ !

#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
629 views10:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ