Get Mystery Box with random crypto!

የ ኡስታዝ ሀቢብ ኑሩ የድምፅ ፋይሎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ oustaz_habib_nuru — የ ኡስታዝ ሀቢብ ኑሩ የድምፅ ፋይሎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ oustaz_habib_nuru — የ ኡስታዝ ሀቢብ ኑሩ የድምፅ ፋይሎች
የሰርጥ አድራሻ: @oustaz_habib_nuru
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.17K
የሰርጥ መግለጫ

የኡስታዝ ሀቢብ ኑሩ የድምፅ ፋይሎች
ጠቅላላ የኦዲዮ ደርሶች ማህደር

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-13 08:41:31 አሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱሏሂ ወበረካቱሁ
ወድ የተከበራችሁ የአማኞች ጋሻ ተከታታይዎች ሰላም ሰነበታችሁ።
ለተወሰነ ጊዜ ወደ online መግበት ለማቆም ስለ ወሰንኩኝ ጥያቄም ሆነ ሀሳብ አቅርባችሁ ካልተመለክትኩት ቅሬታ እንዳይኖራችሁ ማሳሰብ እፈልጋለሁ።

ሀቢብ ኑሩ
780 views05:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 11:26:17 የተንዚህ መከታ ተጨባጭ መረጃ
መሰረታዊ ግንዛቤ እና እውነታ፣
ክፍል 6
==========

በዐረብኛ ቋንቋ "ኢስተዋ"
የሚለው ቃል
ትርጉም
"ኢስተዋ" የሚለው ቃል በዐረብኛ ቋንቋ የተለያዩ ትርጉሞችን ይዞ ሊመጣ ይችላል፡፡ የሚገርመው ነገር ግን ገመናቸው የማይወጣ መስሏቸው ወሀቢያዎች ይህ ቃል አንድ ትርጉም ብቻ ነው ያለው እያሉ ሽንጣቸውን ገትረው ሲከራከሩ መስተዋሉ ነው፡፡ እስቲ ይህ አባባላቸው ውድቅ እንደሆነ ለማሳየት ያክል ብቻ ከትርጉሞቹ መካከል የተውሰኑትን ለመመልከት እንሞክር
መመቻቸት ወይም
መደላደል
አሏህ በቁርአን ላይ የነቢዩሏህ ኑህን(ዐለይሂሰላም) መርከብ አስመልክቶ እንዲህ ብሏል
"واستوت على الجودي" سورة هود:٤٤
ትርጉም "(የነቢዩሏህ ኑህ መርከብ) ጁዲይ በሚባል ተራራ ላይ ተደላደለች"(ሱረቱ ሁድ፥44)
የዐረብኛ ቁንቋ ምሁራን እንደተናገሩት አንድ ሰው ከመጓጓዣው ጀርባ ላይ "ኢስዋእ አደረገ" ከተባለ ተደላደለ ማለት ነው
ልብ ይበሉ፡- እንግዲህ ወሀቢያዎች አሏህን ዐርሽ ላይ ተደላደለ እያሉ መግለጻቸው አሏህ በቁርአን ላይ መርከቧን የገለጸበትን ባህሪ ለአሏህ እየሰጡ ነው ታዲያ ይህ እምነት ተሽቢህ(አሏህን ከፍጡራን ጋር ማመሳሰል) ካልሆነ ተሽቢህ(አሏህን ከፍጡራን ጋር ማመሳሰል) ማለት ምን ማለት ሊሆን ነው!?
ታዲያ አሏህ በቁርአን ላይ
ليس كمثله شىء
ትርጉም "እርሱን (አሏህን) የሚመስል ምንም ነገር የለም"(ሱረቱ ሹራ፥11) ብሎ ማንንም ምንንም እንደማይመስል ከመናገር በላይ ምን ብሎ ቢነግራቸው ይሆን አሏህን ከፍጡራን ጋር ከማመሳሰል የሚቆጠቡት አሏህ ይጠብቀን
መስተካከልና ቀጥ ማለት
አሏህ እንዲህ አለ
فاستوى على سوقه سورة الفتح:٢٩
ትርጉም " (አዝርኢቱ) በአገዳው ላይ ቀጥ ባለ እና በተስተካከለ ጊዜ"(ሱረቱ አል-ፈትህ፡29) በዚህ የቁርአን አንቀጽ ላይ "ኢስተዋ" የሚለው ቃል "ቀጥ አለ፥ተስተካከለ" የሚል ትርጉም ይዞ ነው የመጣው!
ታላቁ የተፍሲር ምሁር አቡ ሀያን አል-አንደሉሲይ "አል በህሩል ሙሂጥ" በተሰኘው የተፍሲር ኪታባቸው እንዲህ ብለዋል "(እዚጋ) ኢስተዋ ማለት አዝርኢቱ አገዳው ላይ እድገቱ ሞልቶ በቆመ ጊዜ ማለት ሲሆን 'ሱቅ' የሚለው ደግሞ 'ሳቅ' የሚለው የዐረብኛ ቃል ብዙ ቁጥር አመልካች ሲሆን ስሩ ለማለት ነው"(አል በህሩል ሙሂጥ ክፍል 8/ገጽ 103)
በይዷዊይ የተባሉት የተፍሲር ምሁር ደግሞ "አንዋሩ አል-ተንዚል" በተሰኘው የተፍሲር መጽሀፍቸው እንዲህ ብለዋል "(ኢስተዋ) ማለት አዝርኢቱ አገዳው ላይ ቀጥ ባለ ጊዜ ማለት ነው"(አንዋሩ አል-ተንዚል 5/86)
ነሰፊይ የተባሉት የተፍሲር ምሁርም እንዲሁ በተፍሲር መጽሀፋቸው (4/64) ላይ ተመሳሳይ ነገር አስፍረዋል፡፡
ታዋቂው የተፍሲር ምሁርም ኢማም አል-ቁርጡቢይ በተፍሲር ኪታባቸው 16/295 ላይ ተመሳሳይ ትርጉም አስቀምጠዋል፡፡
ታላቁ የቋንቋ ምሁር ኢብኑ መንዙር ደግሞ "ሊሳኑል ዐረብ" በተሰኘ መጽሀፋቸው እንዲህ ብለዋል "አንድ ነገር ኢስተዋ ከተባለ ተስተካከለ ለማለት ይሆናል"(ሊሳኑል ዐረብ 14/414)
ሱብሀነሏህ! እነዚህ ሁሉ ዑለማኦች እንግዲህ ኢስተዋ የሚለው ቃል ቀጥ ማለትና መስተካከል በሚል ትርጉም እንደሚመጣ እየተናገሩ ወሀቢያዎች ግን አንድ ትርጉም ብቻ ነው ያለው እያሉ አፋቸውን ሞልተው ይናገራሉ፡፡ ለነገሩ ማገናዘብ አለመቻላቸው እንጅ አንድ ኢማም ወደ ሶላት
ከመግባቱ በፊት ሰዎቹ ሶፋቸውን እንዲያስተካክሉ ሲያስታውሳቸው "ኢስተዉ" አይደለም እንዴ የሚለው ጉድ በነሱ አባባል እንግዲህ ኢስተዋ ማለት መደላደል የሚል ትርጉም ብቻ ቢኖረው ሰጋጆች ተስተካክለው በመቆም ፋንታ ተደላድለው ይቀመጡ ነበር አቤት ውርደት
መሙላት
ሌላኛው "ኢስተዋ" የሚልው ቃል ትርጉም "ሞላ" ማለት ነው፡፡አሏህ እንዲህ አለ
ولما بلغ أشده واستوى سورة القصص:١٤
ትርጉም "(ነቢዩሏህ ሙሳ) አካላዊ ጥንካሬያቸው በሞላ ጊዜ"(ሱረቱ አል-ቀሶስ፥14)
ታላቁ የቋንቋ ምሁር ፈይሩዛባዲይ "በሷኢሩ ዘዊ አል-ተምዪዝ" በተሰኘ መጽሀፋቸው እንዲህ ብለዋል
"ولما بلغ أشده استوى"
ማለት ጠነከረ ፥በረታ ማለት ነው"(በሷኢሩ ዘዊ አል-ተምዪዝ 2/106)
ተቆጣጠረ
ታላቁ የቋንቋ ምሁርና 237ተኛው አመተ ሂጅሪያ ያለፉት ዓሊም ዐብዱሏህ ኢብኑ የህያ ኢብኑል ሙባረክ "ገሪቡል ቁርአኒ ወተፍሲሩሁ" በተሰኘ መጽሀፋቸው እንዲህ ብለዋል الرحمن على العرش استوى
" ማለት ተቆጣጠረ ማለት ነው"(ገሪቡል ቁርአኒ ወተፍሲሩሁ ገጽ 113)
በተመሳሳይ 333ተኛው አመተ ሂጅሪያ ያለፉት የአህሉሱና መሪ የሆኑት አቡ መንሱር አል ማቱሪዲይ "ተእዊላቱ አህሊሱና" በተሰኘው መጽሀፋቸው እንዲህ ብለዋል الرحمن على العرش استوى
ማለት ዐርሽን ተቆጣጠረው ማለት ነው" (ተእዊላቱ አህሊሱና 1/85)
ያስተውሉ፡- ወሀቢያዎች እንግዲህ ከነዚህ ታላላቅ ዑለማኦች እንበልጣለን ብለው ነው ማለት ነው ኢስተዋ የሚለው ቃል ኢስተውላ(ተቆጣጠረ) በሚለው ትርጉም ሊመጣ አይችልም እያሉ ሽንጣቸውን ገትረው ሲከራከሩ የሚደመጠው
"ኢስተዋ" የሚለው ቃል "ኢስተውላ(ተቆጣጠረ)" በሚለው ትርጉም እንደሚመጣ የተናገሩትን ዑለማኦች በዚች አጭር ጹሁፍ መጨረስ ቀርቶ ማጋመስ እንኳ አይቻልም፡፡ የተጠቀሰውም ግን በትክክል ማገናዘብ ለሚችል በቂ ነውና አሏህ ሰፊ ግንዛቤን ይስጠን እያልኩ ለዛሬው በዚህ አበቃሁ
ወሰላሙ ዐለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካቱህ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ዒልሙዲን ኢስላማዊ ስቱድዮ
ክፍል 6
https://t.me/elmudinIslamicstudio/13761
3.1K views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 11:26:17 የተንዚህ መከታ ተጨባጭ መረጃ
መሰረታዊ ግንዛቤ እና እውነታ፣
ክፍል 5
==========

የነብያችንን ቀብር በ ፍንዳታ ሙከራ ሥለ ማድረጋ ቸው አልተሳካላቸውም እንጀ!! ።
ቀብሩን በቦምብ የመቱበትም ምክንያት ጣኦት ነው ብለው ነበር።
አላህ ከሸራቸው ይጠብቀንና።
ቂም ቀ·4
የኢስላም ከሊፋት ለመንኮታከት እጅግ ጥቂት በቀረው ግዜ ላይ
የመካ ሙፍቲ የነበሩት ታዋቂው አሊም ሙፍቲ አህመድ ዘይኒ
ደህላን "ፊትነቱል ወሀብያ " በሚለው መፀሃፋቸው ገፅ 77 ላይ
እንዲህ ገልፀዋል
"ወሀብያዎች ከአዛን በሁዋላ ጮክ ብሎ ሰይዳችን ላይ ሰለዋት
ማውረድን ቢድአ ነው ብለው አጥብቀው ከልክለው ነበር። አንድ እውር የነበረ
ለሰለዋት ፍቅር የነበረው ሷሊህ
ሙአዚን ግን ይህን የወሀብያ ህግጋት ከቁብ ሳይቆጥረው ወሀብያዎች
እየሰሙት አዛን
አድርጎ ከጨረሰ በሁዋላ ፣ በጀግንነት ሰይዳችን ላይ ጮክ ብሎ
ሰለዋት አወረደ።
# በዚህ_ግዜ_ወደ_መሐመድ_አብዱልወሀብ_አመጡት
# _እሱም_ሙአዚኑን_እንዲያርዱት_ተከታየቹን_አዞ_አሳረደው ።
እንግዲህ መ/አብዱልወሀብ ከእውሩ ሙአዚን ጋር የቆየ ቂም አልነበረውም!
እንደው ሙአዚኑ የታረደው ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ላይ ሰለዋት
ስላወረደ ብቻ ነበር ። ይህ ማለት መ/አብዱል ወሀብ ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ
ወሰለም ጥላቻ ስለነበረበት ነው እነጂ ሚስኪኑን ሙአዚኑን በማስጠንቀቅያ
ብቻ ማለፍ በቻለ ነበር!
ንቀት ቁ·5
የወሀብያው መሪ ኢብኑ ባዝ እንዲህ ብሎ ፈትዋ ሰጥቶ ነበር።
ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ዋህይ የወረደበትን ሂራ ዋሻን ለመጎብኘት
ከተራራው የወጣ ሰው ከአላህ ሌላ እያመለከ ስለሆነ ሙሽሪክ ነው ብሎ
ፈትዋ ሰጥቷል።
እንደው ሂራ ዋሻ መሄድ ሙሽሪክ ቢያደርግ ኖሮ መቸ ሰይድ ጂብሪል እዛ ዋሻ
መጥቶ ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ላይ ቁርአንን ያወርደላቸው ነበር?

ጥላቻ ቁ·6
ሰለፊ ተብየዎች ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ሚያወድስ ነገር ሲነሳ
አላርጂካቸው አብሮ ይነሳል። ለዚህም ዋና ማሳያው መንዙማ ነው! ።
ባለፈው በለጠፍኩት ፅሁፍ ላይ በሰፊው ስለ መንዙማ አትቼ ነበር።
ወሀብያዋች መሐመድ አወልን ሙሽሪክ ያሉበት ምክንያት ነብያችን ሰለላሁ
አለይሂ ወሰለም ስለሚጠሉ መሆኑን በሰፊው ዘግቤ ነበር።
"አህያውን ፈርቶ ዳውላውን" የሚለውን ተረት በማስደገፍ ጭምር አስረድቼ
ነበር።
ምክንያቱም ቀጥታ ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ማጥቃት ፈርተው
ሙሪዳቸውን ሚያጠቁበት ምክንያት ለሰይሳችን ካላቸው ጥላቫ መሆኑነም
ዘግቤ ነበር።
ጥላቻ ቀ·7
ነጅዲዮች ሰይዳችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንደሚጠሉ ሌላው ማስረጃ
ደግሞ አንድም የሳቸው አሳር ወይም ንብረት ሳውዲውስጥ አለመኖሩ ነው።
ጥምጣማቸው፣ ጋሻቸው፣ ልብሳቸው፣ ጫማቸው፣ቀለበታቸው ፣ለነገስታት
የላኩት ደብዳቤዋቻቸው፣ከዘራቸው፣ኩታቸው፣የውዱእ እቃቸው፣ አንድም ነገር
ሳውዲ ውስጥ ማግኘት አይቻልም።
እንግዲህ ራስህን አንድ ጥያቄ እዚህ ጋር ጠይቅ!! ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ
ወሰለም ሳውዲ ውሰጥ ተልከው ሳለ ለምንድነው አንድም ንብረታቸው እዛ
ያልተገኘው?
መልሱ እጅግ ቀላል ነው!!
ወሀብያዎች ከነጅድ ተነስተው በ1924 ላይ ሳውዲን ሲቆጣጠሩ 90%
የሚጠጋውን የነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ቅርሶች ጣኦት ነው ብለው
አቃጥለው አጥፍተውታል!!!
የቀረው ንብረታቸው በሙስሊሞች ርብርብ ከሳውዲ ወጥቶ ቱርክ፣
ግብፅ፣ሲርያ እና ሌሎች ሀገሮች ላይ ተበትኖ ይገኛል!
ከዚህ በሁዋላ ፣ ከወሀብያ ጋር ያለው ፀባችን በመውሊድ ብቻ እንዳልሆነ
እንደተገነዘብክ ተስፋ አለኝ!
ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቅንቁ ነውና ነገሩ ፣ወሀብያ መውሊድን መቃወሟ የነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ጥላቻ ስላለባት መሆኗን ግልፅ
እንደሆነልህ እገምታላው።
ጥላቻ ባይኖርማ ታድያ ከነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም 11 ሰይፎች
መካከል ቢያንስ አንዱ እንኳን ሳውዲ ውስጥ ታገኘው ነበርና ነው መልካም መውሊድ!

••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ዒልሙዲን ኢስላማዊ ስቱድዮ
ክፍል 6 ይቀጥላል……
https://t.me/elmudinIslamicstudio/13760
2.3K views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 11:26:16 የተንዚህ መከታ ተጨባጭ መረጃ
መሰረታዊ ግንዛቤ እና እውነታ፣
ክፍል 4
=======
ታላቁ ሶሀብይ ኢብኑ አባስ ረዲየላሁ ዐንህ
إذا إشتبه عليكم شيء من القرآن فاطلوبه من الشعر فإنه ديوان العرب
አንድ ቁርአን አልገባችሁ ካለ ግጥም ውስጥ ፈልጉት… ግጥም የ አረቦች መዝገበ ቃላት ነው ይሉናል ስለዚህ ወደ ግጥም ሄደን የቁርአኑን ትርጉም እንይ
ገጣሚው
قد استوى بشر على العراق
من غير سيف و دم مهراق
ቢሽር ኢራቅን ያለ ምንም ጦርነት እና ደም መፋሰስ ተቆጣጠረ እንጂ ኢራቅ ላይ ከፍ አለ አይባልም… ስለዚህ ኢስተዋ contextual meaning /አገባባዊያዊ ትርጓሜ ነው ያለው ተቀመጠ ሆኖ ይመጣል… ተቆጣጠረ የሚል ትርጉምም አለው… የቁርአኑን ጥበብ መጨረሻ ላይ እመጣበታለሁ አሁን አንድ የ ወሀብያን ቅስም የሚሰብር መረጃ ልንገርህ… በአረብኛ ቋነቋ ህግ መሰረት በላጋ የሚባል የትምህርት ዘርፍ አለ… እዛ ውስጥ ኢንቲሳብ /ሙራአቱ ነዚር የሚል የወሬ ቀመር ቁጭ ብሎልሀል… አንድ ንግግር ነግግር ለመባል ከ ርእስ መውጣት የለበትም ስለ ትምህርት እያወራህ ስለ ቤትህ አስቤዛ ከቀላቀልክ ወሬህ እጅ እጅ ይላል ትባላለህ
ወንድሜዋ አሁን ሱረቱ ጧሀን እንየዉ
تنزيلا ممن خلق الأرض والسموات العلى ٤ الرحمن على العرش استوى ٥ له ما في السموات وما في الأرض وما بينهما وما تحت الثرى ٦
በቀጥታ ከተተረጎመ: _ቁርአን የወረደው ምድርን እና ሰማይን ከፈጠረው ጌታ ነው, ከ አርሽ በላይ ከፍ አለ/ተቀመጠ,በሰማይም ሆነ በምድር ያሉ ነገሮች ሁሉ የ እርሱ ንብረቶች ናቸው…
ጉድ በል ወንድም እውነት አላህ ስለመፍጠር እና የሁሉ ነገር ባለቤት ስለመሆኑ አየነገረን በመሀል አርሽ ላይ ተቀመጥኩ ይላል? ?? መዘባረቅ ከ ፈጣሪ ይጠበቃል ትላለህ… ትክክለኛዉ አተረጓጎም ፈጠረ_ተቆጣጠረ_የግሉ አደረገ አንጂ
ፈጠረ_ቁጭ አለ_የግሉ አደረገ አይደለም
ቁርአን ማለት በውስጡ ብዙ ጥበብ የያዘ ነው አላህ አቡ ለሀብን በ nic name ለምን የጠራው ይመስልሃል? አይዋ ተቀፅላ ስም ከ ዋና ስማችን ያነሰ ክብር ስላለው አላህ በዋና ስሙ አልጠራውም… ቁርአንን እንደ ወሀብያ በቀጥታ አትየው ሊያስተምረን የፈለገው ጉዳይ እኮ አለው… በ 6ቀን ሰማይ እና ምድርን አላህ ለምን ፈጠረ ብትል መረጋጋትን ሊያስተምረን ነው ቁርአኑ ለሁሉ ነገር አትቸኩሉ ሰከን በሉ እኔ ጌታችሁ በ አንዴ መፍጠር እየቻልኩ ለናንተ ትምህርት ነው 6ቀን ማቆየቴ እያለን ነው, አርሽን ተቆጣጥሬያለሁ ሲለንም 7ሰማይ እና 7ምድር ቢጣልበት ሜዳ ላይ የወደቀ ቀለበት የሚያሳክላቸውን ያን ትልቅ አለም የተቆጣጠርኩ ጌታ እናንተን መቆጣጠሬ አያጠራጥራችሁ ነው ጥበቡ አየህ ወንድሜዋ አለል አርሺ ኢስተዋ የ አላህ የ ፈጣሪነት ክብር መገለጫ እንጂ አርሽ ላይ የተቀመጠበት ቃሉ አይደለም… ከፈጠረው ፍጡር ከማንም አይፈልግም ከ 73 በላይ የ ኢስላም አባቶችን መጥቀስ ይቻል ነበር ሰአቱም ቦታውም አይፈቅድም…
በመጨረሻም ኢማሙ አህመድ ሙስነድ ኪታባቸው ላይ እንደዘገቡት ነብዩ ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም "ወደፊት ቱርክን የሚከፍታት መሪ ምርጥ መሪ ነው ወታደሮቹም ምርጥ ናቸው" ብለዋል …ሶሀበቶች ሊከፍቷት ሞከሩ አቡ አዩብ ቱርክ ድንበር ላይ ሞቱ የከፈታት ግን የ 18 አመቱ ወጣት ሙጃሂድ ሙሀመዱል ፋቲህ ነበር, በቦታው የነበረውን ቤት በከራማው በ እጁ ወደ ቂብላ ያዞረ ልጅ ነው ነብዬ የመሰከሩለት ምርጥ ወታደር እምነቱ አላህ ያለ ቦታ እና ያለ አቅጣጫ ነው ያለው የሚሉት የማቱሪዲያ እምነት ነበር… ሁሌም የሚያኮራ እምነት ነው ያለህ ወንድሜዋ ለ ሸይኽ አብዲላህ አል ሀረሪይ ትልቅ ደረጃ አላህ ይስጣቸው ሸይኽ ኡመር እና አሁን ያሉትን ምርጥ ምርጥ ተማሪዏቻቸዉን ከምቀኛ ይጠብቃቸው ወላሂ ቢገባን ትልቅ ዉለታ ነው የ ጀነት ዉለታ
ከስድስቱም ጀሃት ኻሊቃችን ጠራ
ከፊትም ከኃላም ከቀኝም
ከግራ
ጌታ የጠራ ነው ከታችም
ከላይ
ጃሂል ያንጋጥጣል መስሎት
በሰማይ
ጌታ ወርዶ ይፍረድ የሚሉት
ሲጣሉ
ጥርጥርም የለው በውነት
ይከፍራሉ
የጌታ ረህመቱ መፍሰሻው
ከላይ ነው
ለዱዓችን ማንሳት ለረህመት እንጅ ነው
ጌታ ወዴት ይሆን በማለት አትሞኝ
እንደ ነበረ ነው ፍጥረቱ
ሳይገኝ
የኛ መኖርና ሰማይና ምድሩ
ያመላክታሉ ጌታ ለመኖሩ
ጌታ የለም ማለት የለሁም
ማለት ነው
ፍጥረቱን ፈጣር ጌታችን ያለ ነው

ሸይኽ ሙሀመድ ደሴ
ስለ መውሊድ ማክበር የተክፊሮች ጭጋግ ስለጋረደኝ ፣ በዥታየን
አስወግድልኝ! ካልከኝ የሚከተለውን መረጃ ላቀብልህ።
ኢኽዋኖች መውሊድ አታክብር ብለው አስቸገሩኝ ካልከኝ, ራስህን ትከላከል
ዘንድ መሳርያ ላውስህ።

እኛ ከ ኸዋሪጆች ጋር እየተጣላን ያለነው በመውሊድ ጉዳይ ብቻ ከመሰለህ፣
እጅጉኑ ተሳስተሀል።
እኛ ከ ኢኽዋኖች ጋር ያለን ፀብ ለምን የነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም
መውሊድ ትቃወማላቹ ሚለው ብቻ አይደለም።
ፀባችን፣ ለምን ነብዩን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ትጠላላቹ? የሚል ነው።
ምናልባት ይህ ጥያቄ አሁን ሊያሰቆጣህ ይችላል!! ። ነገር ግን መጣጥፉን
አንብበህ ከጨረስክ በሁዋላ እውነትም ኸዋሪጆች ነብያችንን ሰለላሁ አለይሂ
ወሰለም እንደሚጠሉ ትረዳለህ።
ነገሩ ምን መሰለህ አንተ የምትወደው ሰው ከሞተ በሁዋላ እንኳን ቅርሱን
ጠብቀህ ታቆያለህ። ያንን ቅረስም ለልጆችህ እያሳየህ የሰውየውን ጀብዱ
ለልጆችህ ትተርካለህ።
ለምሳሌ ያህል እኔ ጋር የቅድመ አያቴ ጦርና ሰይፍ ይገኛል።
ይህ ጦርና ሰይፍ አባቴ በአግባቡ ተንከባክቦ አስረክቦኛል፣ እኔም አላህ ካለ
ለልጄ አስረክባለው እንጂ , ጦርና ሰይፉ ጣኦት ነው ብየ አላቃጥለውም! ።
ነገር ግን ወሀብያዎች ነብያችንን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ቅርስ ለትውልድ
ለማስተላለፍ ፋንታ አብዛኛውን ጣኦት ነው ብለው አጥፍተውታል።
ይህንንም እንደሚከተለው በማስረጃ እገልፅልሀለው
ጥፋትቁ፣
1·1)ነብያችንን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የተወለዱበት ቦታ ወሀብያዎች መካን
በ1920 ዎቹ ሲቆጣጠሩ አፍርሰውታል።
ካፈረሰቱም በሁዋላ ያቦታ እንዲረሳ ለማድረግ በቦታው ትልቅ ላይብረሪ
አሰርተውበታል።
እንግዲህ ከከሊፋዎቻችንም አንዱም ነብያችንን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም
የተወለዱበትን ቦታ ለማፍረስ የሞከረ አልነበረም።
ሁሉም በተረከበው ሁኔታ ነው ለትውልድ ሲያስተላልፍ የነበረው።
አረ እንዴትስ አሚናን መላአካዎች ያባሸሩባት ቦታ እንዴትስ ተደርጎ ይደፈራል??
ወከባ ቀ·2
ነብያችንን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ለረጅም አመታት የኖሩት ከእናታችን ኸዲጃ
ረድየላሁ አንሁ ጋር ነው።
ለ28 አመታት የኖሩትም እሷ ቤት ውስጥ ነው።
በአጭሩ ነብያችንን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምኸድጃን ካገቡ በሁዋላ ቤቷ
የሳቸው ንበረት ነበር።
እንግዲህ ወሀብያዎች ይህን ሰይዳችንን
ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ለ28 አመታት የኖሩበትን ቤታቸውን አፍርሰውታል፣።
አፍርሰው ብቻ አላበቁም፣ በፈረሰው ቦታ ላይ የህዝብ ሽንት ቤት
አሰርተውበታል ።
እንግዲህ የመለስ ቀብር ላይ ሽንት ቤት ቢሰራ ምን አይነት ንቀት እንደሆነ
ይገባሀል።
ነገሩ ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ ነው!
እንግዲህ ቁጠርልኝ ፣ ወሀብያ መጀመርያ ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም
የተወለዱበትን ቤት አፈረሰች፣ ከዛም የኖሩበትን ቤት ሽንት ቤት አደረገችው።
•••••••••••••••••••••••••••••••
ዒልሙዲን ኢስላማዊ ስቱድዮ
ክፍል 5 ይቀጥላል……
https://t.me/elmudinIslamicstudio/13759
2.0K views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 11:26:16 የተንዚህ መከታ ተጨባጭ መረጃ
መሰረታዊ ግንዛቤ እና እውነታ፣
ክፍል 3
=================__
"_አር _ ረህማኑ አለል _ዐርሺ ኢስተዋ
ጤነኞች ብቻ የሚረዱት የአሏህ ተዓምራዊ ቃል "
"የሰው ልጅ አእምሮ ማለት ባዶ ብርጭቆ ነው የተሞላበትን ይቀበላል " ሀጂ ሸይኽ ኡመር ኢማም ሀፊዞሁሏህ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ የ አኼራ ወንድሜ እንደምን ነህልኝ? የ አላህ መሺኣ ሆኖ ዛሬ ከበድ የሚል ወሬ ይዤብህ መጥቻለሁ እና ከ ልብህ ይቅር ብለህ አድምጠኝ… ከ አላህ አገኝበታለሁ ብለህ ጆሮህን ስጠኝ ስራችን ሊላህ እስካልሆነ ትርፉ ወንጀል ብቻ ነው ።ሞት እና ቀብር እንዳለ አትርሳ …አሁን የፃፍኩልህን ሳላነብልህ አጀሌ ደርሶ ብለይህ አደራ ፋቲሃ ቅራልኝ,አኼራን እያሰብክ, የሲሯጡን መንገድ, ጣረ ሞት ላይ ያለውን የውሀ ጥም አትዘንጋው ኺታሜን እና ኺታምህን አላህ ያሳምርልን ።ዛሬ በጣም ፈልጌሃለሁ በጤናማ አስተሳሰብ ስማኝ,ካንተ ማገናዘብ እና ማመዛዘንን እሻለሁ የማወራህ ለቀብሩ ቤትህ የሚጠቅም ወሳኝ ጉዳይ ነው አደራ ወንድም ጋሼ ትህትናህ አይለየኝ ።

【NO MAN IS AN ISLAND】

።።።።።።።።።።
ዛሬ አንድ እኔንም አንተንም የሚያግባባ ሀሳብ ይዤልህ ቀርቤያለሁ ባለመስማማታችን ተስማምተን አብረን አንቀጥልም… ልብ ለልብ መገናኘታችን የግድ ነው ካሎነማ ወንድምነትህ ምኑ ላይ ነው? ??
አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ የፍጥረታቱ ጌታ ከማንም በላይ ሊከበር እና ሊፈራ, ሊወደድ የግድ ነው, ፀጋው ቢቆጠር አያልቅም ከሁሉ በላይ ግን ሙስሊም ስላደረገን አልሀምዱሊላህ… እና ይህ ጌታችን ለመኖሩ ጅማሬም ሆነ ፍፃሜ የለውም ሁሉ ሲጠፋ ብቻውን ቀሪ ነው… ሰው ፈጥሯል, ጅን ሰማይ,መለኢካ ሁሉንም አይመስልም, እንከን እና ጎዶሎ የሌለበት ባሪያዏቹን የማይበድል ፍትሃዊ ጌታ
።።።።።።።።።።።።።።።
አላህ በ ሱረቱ ሹራ ١١
ليس كمثله شيء
ይለናል, እኔን የሚመስል ማንም የለም, ነው ትርጉሙ አላህ እኛ በምንገለፅበት በ 1 ባህሪ እንኳን አይገለፅም እኛ ደካማ, ከጃይ ፍጡሮቹ ነን እሱ ደሞ ፈጣሪ ።
በሱረቱ ነህል ٦٠
ولله المثل الأعلى
እኔ የምገለፅባቸው ባህሪያቶች ከሁሉም ፍጡራን የተለዩ እና የተሟሉ ናቸው ይለናል
አሁንም እዛው ሱረቱ ነህል ٧٤ ላይ
فلا تضربوا لله الأمثال
ለኔ አንድም አምሳያ አታድርጉ… ማንኛችሁንም አልመስልም ይለናል…
በሱረቱል ኢኽላስ ٤
ولم يكن له كفوا أحد
ለኔ አንድም አቻ እና ወደር የለኝም ብሎ ራሱን አስተዋውቆናል… ስለዚህ አላህ በ አንድ እንኳን የፍጡር ባህሪ አይገለፅም ጌታችን እንጂ ጓደኛችን አይደለም… በመቀመጥ,ከላይ በመሆን ከታች በመሆን አይገለፅም ምክንያቱም ሁሌም እኛን አይመስልም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ወንድሜዋ ጌታችን አላህ ምንም ነገር ሳይኖር ነበረ አርሽን ሳይፈጥር ያለ አርሽ ነበረ, አቅጣጫን ሳይፈጥር ያለ አቅጣጫ ነበረ… ከፍጥረታቱ ቅንጣት ታክል የማይፈልግ ከሁሉ የተብቃቃ ጌታ ነው ለዚህም በቁርአን ሱረቱል ኢምራን ٩٧
إن الله لغني عن العالمين
እኔ ከፈጠርኳቸው ፍጡሮች ሁሉ ምንም ነገር አልፈልግም ብሎናል አርሽም አልከው ሰማይ የርሱ ናቸው ከነሱ ትፈልጋለህ ብሎ መናገር የእናት ጡት ነካሽነት ይመስለኛል… ከማንም አልፈልግም እያለን…
።።።።።።።።።።።።።።።።
【ALLAH EXISTS WITH OUT A PLACE 】

።።።።።

ኢማሙል ቡኻሪይ በዘገቡት ሀዲስ ነብዪ ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም
كان الله ولم يكن شيء غيره
አላህ ምንም ነገር ሳይኖር ነበር ብለውናል… ይህ ማለት ቦታም አቅጣጫም ሳይኖር ጀሊሉ ያለ ቦታ ያለ አቅጣጫ ነበር እሱ ምን ይሳነዋል እኛንስ ሰው ይሆናል ተብሎ ከማይታሰብ ልብሳችንን ሊነካን ከማንፈልገው sperm መፍጠሩን ችሎበት የለ
…ኢማሙ ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ ነብዩ ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም
اللهم أنت الظاهر فليس فوقك شيء وأنت الباطن فليس دونك شيء
አንተ ጌታዬ አላህ ከ በላይህም ከ በታችህም ምንም ነገር የለም ብለውታል ታዳ ነቢን ነው የምትሰማው ወሀብይን? ??
እነሱ እንደሚሉት አላህ አርሽ ላይ ከሆነ በነቢ አባባል ሰማይም የለም, እኔ እና አንተም የለንም ማለት ነው ። ኧረ ወንድሜዋ ዘይንዬ ዋሽተው አያውቁም ጌታችን አላህ ከፈጠረው ነገር ሁሉ አይፈልግም ሳይፈጥራቸውም ያለነሱ የነበረ ነው ።
_አሁንም ኢማሙ ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ ነብዩ ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም
أقرب ما يكون العبد من ربه وهو ساجد، فأكثروا الدعاء
ከናንተ አንዳችሁ ለ ጌታው ቅርብ የሚሆነው ሱጁድ ሲያደርግ ነው እና ሱጁድ ላይ ዱኣ አብዙ ብለውናል እንደ ወሀብያ አስተሳሰብ አላህ አርሽ ላይ ቢሆን ቆመን ነው የሚቀርበን ወይንስ ግንባራችን መሬት ሲነካ? ??
ስለዚህ ጌታችንን አላህ በቦታም ሆነ በአቅጣጫ ነቢ ገልፀውት አያውቁም ።
።።።።።
【SHORT & PRECISE EXPLANATION ABOUT
AR_REHMANU ALEL _ARSHI ISTEWA】

ወንድሜዋ አሁን ቁርአን ላይ ብዙ ቦታ ስለተጠቀሰው
الرحمن على العرش استوى
አር _ረህማኑ አለል አርሺ ኢስተዋ ላወራህ ወደድኩ… ከዚህ በፊት ቁርአን በቀጥታ እንደማይተረጎም በደንብ ያወራን ይመስለኛል… አዏ አማረኛ ራሱ ብዙ በቀጥታ የማይተረጎሙ ቃሎች አሉት አልጋ _ወራሽ, ሆደ ሰፊ, አይነ ደረቅ, እና ሌሎችም… ይህም ቁርአን ቀጥታ ተወስዶ አላህ አርሽ ላይ ተቀመጠ ወይንም ከፍ አለ አይባልም… በአጭሩ ወደ አረብኛው አለም ልውሰድህ እና እውነታውን ላስቃኝህ

ታላቁ ሰሀብይ ኢማሙ አሊይ ረዲየሏሁ አንሁ
إن الله خلق العرش إظهارا لقدرته ولم يتخذه مكانا لذاته
አላህ አርሽን የፈጠረው ችሎታውን ሊያሳይ እንጂ ቦታ አድርጎ ሊይዘው አይደለም ። ይሉናል አቡ መንሱሪል በግዳዲይ አል ፈርቁ በይነል ፊረቅ ላይ ዘግበውታል ነቢ ሶሀቦቻቸውን ያስተማሩት ይሄንን ነው እንግዲህ አላህ ከ አርሽ አለመፈለጉን ስለዚህ ይህ ቁርአን አላህ አርሽ ላይ ተቀመጠ ተብሎ በቀጥታ አይወሰድም አሏህ አይሁዶችን የረገማቸው በምን መሰለህ በ 6ቀን ሰማይ እና ምድርን ፈጥሮ በ 7ኛው ቀን ደክሞት#አርሽ ላይ ተኛ…ተቀመጠ ወይም ከፍ አለ የሚሉት ወሀብዬች ከ እርግማን እና ቁጣው ይተርፋሉ ትላለህ? ??
ሀፊዝ አቡ በክር ኢብኑል አረቢይ ኢስተዋ 15 ትርጉም አለው ብለውናል, መቀመጥ,ከፍ ማለት, መቆጣጠር, መብሰል,ማሰብ, እኩል መሆን ወ·ዘ,ተ ስለዚህ ከነዚህ ትርጉሞች ውስጥ ለ አላህ ተስማሚ የሆነውን መምረጡ የ ግድ ነው ከፍ አለ እንዳትል ጎደሎ ባህሪ ነው በፊት አላህ ዝቅ ያለ ነበር እንዴ??? መቀመጥም ለፈጣሪ ስድብ ነው ስለዚህ ተቆጣጣረ የሚለው ተስማሚ ነው…።
ታላቁ ሰሀብይ ኢብኑ አባስ ረዲየላሁ አንህ
إذا إشتبه عليكم شيء من القرآن فاطلوبه من الشعر فإنه ديوان العرب
አንድ ቁርአን አልገባችሁ ካለ ግጥም ውስጥ ፈልጉት… ግጥም የ አረቦች መዝገበ ቃላት ነው ይሉናል ስለዚህ ወደ ግጥም ሄደን የቁርአኑን ትርጉም እንይ
ገጣሚው
••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ዒልሙዲን ኢስላማዊ ስቱድዮ
ክፍል 4 ይቀጥላል……
https://t.me/elmudinIslamicstudio/13758
1.9K views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 11:26:16 የተንዚህ መከታ ተጨባጭ መረጃ
መሰረታዊ ግንዛቤ እና እውነታ፣
ክፍል 2
==========

የኢማም ማሊክ አቋም የመዲና ዓሊም እና ኢማም፤ እንደሌሎቹ የሀቅ ኢማሞች አሏህ ከቦታና አቅጣጫ ያጠሩ ነበር። . እማም አል ሙፈሲር ናሲሩዲን ኢብን አልሙኒር (አል ሙቅተፋ ፊሸረፊል ሙስጠፋ) ስለ አቅጣጫ ተናገሩና ለአሏህ ማስጠጋቱ ተገቢ አለመሆኑን ካረጋገጡ በኋላ አሉ፦ ለዚህም ትርጉም ነው ኢማም ማሊክ ያመላከቱት በዚህ የነቢዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ንግግር እሱም {ከዩኑስ ኢብኑ መታ አታስበልጡኝ} \ቡኻሪይ ዘግበውታል\ ኢማም ማሊክ እንዲህ ብለዋል “ከዩኑስ ልዩ አድርጋቹ (አታስበልጡኝ) ያሉት ተንዚህን ለማመላከት ነው ምክኒያቱም ነቢዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ወደ ዐርሽ ከፍ ብለዋል፤ ዩኑስ ደግሞ በህር ውስጥ ወደ ታች ጠልቀዋል፤ ነገር ግን ይህ ቢሆንም በአቅጣጫ በኩል ሁለቱም አሏህ ዘንድ እኩል ናቸው፤ ብልጫ በቦታ ቢሆን ኖሮ ነቢዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከዩኑስ ቅርብ እና በላጭ ቦታ ላይ የሆኑ በሆነ ነበር (አታስበልጡኝ) ብለውም ባልከለከሉ ነበር።” ይህን ንግግር ከኢማም ማሊክ ኢማም ተቂዩዲን አሱብኪይም አስተላልፈዋል በመጽሃፋቸው (አሰይፉ አሰሰቂል/137) . እንዲሁም አልሓፊዝ ሙርተዳ ዘቢዲይ በ(ኢትሓፉ-ሳደቲል ሙተቂን/105/2)ብለዋል፦ ነገር ግን ሰሪጅ ኢብኑ-ኑእማን የዘገበው ከ አብዱላህ ኢብኑ ናፊእ ከ ኢማም ማሊክ እንዲህ ብለዋል በማለት “አሏህ በሰማይ ነው እውቀቱ በሁሉም ቦታ ነው” የሚለው ንግግር ከሳቸው ያልተረጋገጠ ነው። ይህን ንግግር ያስተላለፈ ሰው ኢማም አሕመድ ስለሱ እንዲህ ይላሉ “አብዱሏህ ኢብኑ ናፊእ አሳኢግ የሐዲስ ሰው አልነበረም በዛም ደካማ ነበር” ኢብኑ ፈርሑን ደግሞ እንዲህ አሉ “መጽሃፍም መስማትም አይችልም ነበር” ኢብኑ ዐዲይም እንዲህ አሉ “ወደ ማሊክ 'ጔራኢቦችን' ያስጠጋ ነበር” በተጫማሪም ስለ ሰሪጅ አል ኑዕማን እን ኢብኑ ናፊእ በሐዲሥ ደዒፍ የሆኑና ዘገባቸው አስተማማኝ ያልሆኑት የሚገልፅ መፅሃፎች ላይ ተቀምጧል። . ስለዚህ በንዲህ አይነት ሰነድ (ዘጋቢዎች) ይህ አይነት ንግግርን ወደሳቸው አናስጠጋም፤ ስለዚህ የኢማም ማሊክ አቋም ከላይ ከተጠቀሰልን በኋላ ሙሸቢሃዎች ወደ እሳቸው የሚያስጠጉት እሳቸው ያላሉት እንደሆነ ይረጋገጥልናል ማለት ነው። 〉
አራቱ የመዝሀብ ዑለማኦች ስለ ኢስቲዋእ አንቀፅ ያነበራቸው አቋም፦ [ ክፍል - ሁለት - 2 ] -------------- -------- ----- --- 2- «ኢማም አቡ-ሐኒፈ» ፦ → ኢማም አቡሐኒፈ አሏህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና ሰለ ኢስቲዋእ ሲጠየቁ (አልፊቅህ አል-አብሰጥ/49) በሚል መጽሃፋቸው እንዲህ አሉ፦
« ﻣﻦ ﻗﺎﻝ ﻻ ﺃﻋﺮﻑ ﺭﺑﻰ ﺃﻓﻰ ﺍﻟﺴﻤﺎﺀ ﺃﻡ ﻓﻰ ﺍﻷﺭﺽ ﻓﻬﻮ ﻛﺎﻓﺮ ‏» ﻷﻧﻪ ﺃﺛﺒﺖ ﻟﻠﺤﻖ ﻣﻜﺎﻧﺎ
«ጌታዬ ሰማይ ላይ ይሁን ወስይ ምድር ላይ አላውቅም ያለ ካፊር ነው» ኢማም ዒዙዲን ኢብኑ ዐብዲሰላም (የኡለማኦች ልዑል) ተብለው ሚሰየሙት የአቡ ሐኒፋን ንግግር ጠቅሰው እንዲህ ኣሉ፦“ይህ ንግግር ለአሏህ ቦታ አለው ማለትን የሚያመላክት ስለሆነ፤ ለአሏህ ቦታ ኣለው ብሎ የሚያስብ ደግሞ ሙሸቢህ ነው (አሏህን ከፍጡር ጋር ያመሳሰለ ነው)። → ይህን ደግሞ የአቡሐኒፋ ንግግር እንደሆነ ብዙ ዓሊሞች አረጋግጠዋል። እንደ አሕመዱ ሪፋዒ፣ እንደ ተቂይ አል ሑስኒይ እና ሌሎችም። ከዚህ የተለየ ወደሳቸው ያሚያስጠጋ ካለ እንደሆነ ውሸት የተነገረ ይሆናል። ምክኒያቱም አቡ ሐኒፋ አሏህን ከተሽቢህ እና ከቦታ ያጠሩ እንደነበረ በመፅሃፎቻቸው፤ እንደ «አል-ፊቅሁል አክበር» ፣ «አል-ወሲያ» ፣ «አል-ፊቅሁል አብሰጥ» ላይ በግልፅ አስቀምጠዋል። ለምሳሌ ያህል ("አልወሲያ"/70) በሚል መጽሃፋቸው እንዲህ ይላሉ፦ “አሏህ በአርሹ ኢስቲዋእ ማድረጉን እናረጋግጣለን፤ በአርሽ ፈላጊ ሳይሆን እንዲሁም ሳይደላደልበት፤ እርሱ አርሽንም ከአርሽ ውጭ ላለውም ጠባቂ ነው፤ ከሌላው ፈላጊ ቢሆን ኖሮ እንደ ፍጡራን አለምን ማስገኘትና ማስተዳደር ባልቻለ ነበር፤ በመቀመጥና በመደላደል ከጃይ ቢሆን ኖሮ ዐርሽን ከመፍጠሩ በፊት ዬት የነበረ ሊሆን ነው?! አሏህ ከዚሁ የላቀና የጠራ ነው።» → የሚገርመው ነገር ወሃቢያዎች ይህ ንግግራቸውንም ለመበረዝ ሞክረዋል። ኢማም አቡሐኒፋ
ﻣﻦ ﻏﻴﺮ ﺃﻥ ﻳﻜﻮﻥ ﻟﻪ ﺣﺎﺟﺔ ﺇﻟﻴﻪ ﻭﺍﺳﺘﻘﺮﺍﺭ ﻋﻠﻴﻪ " «በአርሽ ፈላጊ ሳይሆን እንዲሁም ሳይደላደልበት» ያሉትን፦ ﻭﺍﺳﺘﻘﺮ ﻋﻠﻴﻪ በማለት፣ ሁለት ፊደል በማውጣት ተደላደለበት የሚለውን ትርጉም ወደሚሰጥ ቀይረውታል። ነገር ግን ንግግሩ ራሱ ያዋርዳቸዋል። እርስ በርስ የሚጋጭና የቀየሩት እንደሆነ ግልፅ ነው። ንግግሩስ እንዴት ይሄዳል? «በአርሽ ፈላጊ ሳይሆን» ብለው ተመልሰው "እንዲሁም ተደላደለበት" ማለታቸው፤ እንዲሁም የንግግራቸው መጨራሻን ካየነው አሏህ ከመደላደል ማጥራታቸውን ግልፅ ያደርግልናል «...ከሌላው ፈላጊ ቢሆን ኖሮ እንደ ፍጡራን አለምን ማስገኘትና ማስተዳደር ባልቻለ ነበር፤ በመቀመጥና በመደላደል ከጃይ ቢሆን ኖሮ አርሽን ሳይፈጥረው ዬት የነበረ ሊሆን ነው?! አሏህ ከዚሁ የላቀና የጠራ ነው» ። → እንዲሁም ("አልፊቅህ አል አብሰጥ"/57) እንዲህ ብለዋል፦ «አሏህ ቦታ ሳይኖር የነበረ ነው፤ ፍጡራንንም እንደዛው ሳይፈጥር ነበረ፤ እርሱ የነበረ ነው ዬት (ቦታ) በፊት ፍጡራንም እንዲሁም ምንም ነገር ሳይኖር በፊት የነበረ ነው እሱም ነው የሁሉም ነገር ፈጣሪ። »... → ኢማም አቡ ሐኒፋ አቋማቸው አሏህን ከቦታ እንዲሁም ከፍጡር በህሪ ማጥራት ቢሆንም ሙሸቢሃዎች ጥሜታቸውን ለማሰራጨት እሳቸው ያላሉትን በውሸት ወደሳቸው ሚያስጠጉት አይጠፋም። ከነዚህም አንዱ፦ «በአቡ ሙጢዕ አልበለኺይ የሚወራው! እሱም አቡ ሐኒፋ እንዲህ ብለዋል የሚለው ነው «ጌታዬ ሰማይ ላይ ይሁን ወስይ ምድር ላይ ይሁን አላውቅም ያለ ካፊር ነው» እስካሁን ያለው ትክክል ነው፤ ግን ከዚህ አስከትሎ እንዲህ ይላል “ምክኒያቱም 'አርረሕማኑ ዐለል ዐርሺስተዋ' ሰለሚል, ዐርሹ ደግሞ ከሰባት ሰማያት በላይ ነው” ይህ እሳቸው ያላሉት ንግግር ነው) አሁንም አስከትሎ ይላል፦ “እንዲህ ተብለው ሲጠየቁ ዐርሹ ላይ ነው ብሎ ዐርሹ ግን ሰማይ ይሁን ምድር አላውቅም የሚል ይከፍራል” [ምክኒያቱም አሏህ በቦታ ስለማይፈልግ ነው ዐርሽ ላይ ነው ማለቱ ቦታን ስለሚያመላክት ሰማይ ላይ ነው ማለት ክህደት እንደሆነ ምድር ላይ ነው ማለትም ክህደት ነው።] ዘጋቢው ግን ቀጥሎ እንዲህ ይላል “ምክኒያቱም አሏህ ሰማይ ላይ ስለሆነ...” አዑዙቢላህ አቡ-ሐኒፋ ከዚህ የፀዱ ናቸው። ሼኽ ሙላ ዐሊል ቃሪእ አልሐነፊይ አሉ፦ “ አቡ ሙጢዕ አልበለኺይ (የዚህ ንግግር ዘጋቢ) የሀዲስ ባልተቤቶች ዘንድ ወዳእ ነው (ሀዲስ ላይ ውሸትን የሚጨምር ነው)” እንዲሁም ሼኽ ሙስጠፋ አልሐማሚይ ዘገባው ተቀባይነት እንደሌለው እና “ወዳእ” መሆኑን ተናግረዋል። እንዲሁም ሙሸቢሃዎች ሚያወሩት አቡ ሐኒፋ "አሏህ ሰማይ ነው ብለዋል የሚሉት ትክክል አይደለም የራሣቸው ጭማሬ ነው።

••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ዒልሙዲን ኢስላማዊ ስቱድዮ
ክፍል 3 ይቀጥላል……
https://t.me/elmudinIslamicstudio/13756
1.8K views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 11:26:16 የተንዚህ መከታ ተጨባጭ መረጃ
መሰረታዊ ግንዛቤ እና እውነታ፣
ክፍል 1
==========
አዛኝ እና ሩህሩህ በሆነው ጌታዬሥም እጀምራለሁ፣

ከአባታችን አደም እስከ መጨረሻው ነብይ የሆኑት ረሱል አለይሂ ሶላቱ ወሰላም ድረስ ያሉት ሁሉም አንብያዎች አሏሁ ተዐላ ፍጡራንን እንደማይመስል እና ከቦታ እና በአቅጣጫ የተጥራራ ነው ብለው ነው የሚያምኑት።

ሁሉም ፍጡር የሆነ ነገር ቦታ እና አቅጣጫ ይይዛል።ፍጡር ደግሞ ከሁለት ነገር አያልፍም
[ ، ﺇِﻣَّﺎ ﺟِﺴْﻢٌ ﻟَﻄِﻴﻒٌ ﺃَﻭْ ﺟِﺴْﻢٌ ﻛَﺜِﻴﻒٌ .
1ኛው የማይዳሰስ አካል ወይም
2ኛው የሚዳሰስ አካል
ﭐﻟْﺠِﺴْﻢُ ﭐﻟﻠَّﻄِﻴﻒُ ﻛَﺎﻟﻨُّﻮﺭِ ﻭَﭐﻟﺮِّﻳﺢِ ﻭَﭐﻟﻈَّﻼﻡِ ،
1)የማይዳሰሱ አካል፦ ብርሃን፣ጨለማ፣ሩህ......
ﻭَﭐﻟْﺠِﺴْﻢُ ﭐﻟْﻜَﺜِﻴﻒُ ﻛَﺎﻟﻨَّﺠْﻢِ ﻭَﭐﻟﺸَّﻤْﺲِ ﻭَﭐﻟْﻘَﻤَﺮِ
2)የሚዳስሱ አካላት፦ከዋክብት፣ፀሀይ ፣ጨረቃ፣ሰው ፣ድንጋይ......
አሏሁ ተዐላ ደግሞ ከሚዳሰስ አካል እንዲሁም ከማይዳሰሱት አካል አይደለም(የተጥራራ) ነው።
በቦታ እንዲሁም በአቅጣጫዎች መካከል ክፍተት ወይም በዛ ክፍተት የሞላው ነገር ያስፈልገዋል።
ለምሳሌ፦በአንደኛው ሰማይ እና በምድር መካከል የ500 ዓመት ያክል ክፍተት አለው።
በዚህም በሚዳሰሱት አካል እና በማይዳሰሱት አካል የተሞላ ነው ማለትም በ2ቱ መካከል ብርሃን፣ጨለማ አሉ እንዲሁም ሰው፣ድንጋይ.... በተለያዩ ነገራቶች የተሞላ ነው።አሏህ ደግሞ በሚዳሰሱትም አካል ይሁን በማይዳሰሱት አካል አይገለፅም። የተጥራራው ጌታችን አሏሁ ተዐላ አምሳያ የለውም።ለዚህም አሏህ በቁርዓኑ እንዲህ ይለናል
قال الله تعالى"فلا تضربوا لله الأمثال"

ትርጉሙም፦ለአሏህ አምሳያ አታድርጉለት
አሏሁ ተዐላ በተለያየ የቁርዓን ዐያ ራሱን ያጥራራል።ከዚህ በተቃራኒ የሚያምን ማለትም ለአሏህ አምሳያ እንዲሁም በአቅጣጫ የሚገልፅ ሰው ከእስልምና የወጣ ነው።አሏህ ይጠብቀን

ለዚህም ሰለፍ የሆኑት ትልቅ አሊም የሆኑት ኢማም አቡ ጀዕፈር አጦሀውይ እንዲህ ብለዋል
" ﻭﻣﻦ ﻭﺻﻒ ﺍﻟﻠﻪ ﺑﻤﻌﻨﻰ ﻣﻦ ﻣﻌﺎﻧﻲ ﺍﻟﺒﺸﺮ ﻓﻘﺪ ﻛﻔﺮ"
ትርጉሙም፦አሏህን በፍጡር ባህሪ በአንዱ ባህሪ የገለፀ በርግጥ ከፍሯል ማለትም ከእስልምና ይወጣል። አሏህ ይጠብቀን

አሏህ ያለ ቦታ እና ያለ አቅጣጫ ያለ ጌታ ነው

ሁላችንም ማወቅና ትርጉማቸውን በሚገባ ማወቅ መሀፈዝ የሚገባን የቁርኣን አያ አሏህን ከቦታም ሆነ ከአቅጣጫ በአጠቃላይ ከፈጠረው ነገር የማይፈልግ ጌታ መሆኑን የሚገልጽ አያዎች(ءاية) ናቸው ለሁላችንም ይጠቅመናል አንድ ሙጀሲም አላህ ያለቦታ ያለ ለመሆኑ ማስረጃ ከቁርኣንና ከሀዲስ ጥቀሱልን ካለ ሁላችንም ይህንን መመለስ እንችላለን ከሀፈዝነው አሏህ ያግራልን
قال الله تعالى{ليس كمثله شىء وهو السميع البصير}سورة الشورى11] አሏህ በተከበረው ቁርኣን እንዲህ ይለናል እርሱን የሚመስል ምንም ነገር የለም እሱም ሰሚና ተመልካች የሆነ ጌታ ነው
قال الله تعالى{ولم يكن له كغوا أحد}سورة اﻹخﻻص4] አሏህ ሱብሀነ ወተአላ በቁርኣን እንዲህ ይለናል አሏህ አንድም ቢጤና አምሳያ የለውም
قال الله تعالى{فﻻ تضربوا لله اﻷمثال}سورة النحل74]
አሏህ ሱብሀነ ወተአላ በቁርኣን እንዲህ ይለናል ለአሏህ ምሳሌ አትጥቀሱለት አምሳያ የለውምና
قال الله تعالى{ولله المثل اﻷعلى}سورة النحل60
አሏህ ሱብሀነ ወተአላ እንዲህ ይለናል አሏህ ባህሪያቶች አሉት የሌሎችን የፍጡራን ባህሪይ የማይመስሉ

قال الله تعالى{هل تعلم له سميا} سورة مريم65]
አሏህ ሱብሀነ ወተአላ በቁርኣኑ።እንዲህ ይለናል አሏህን የሚመስል ምንም ነገር የለም
ከሀዲስ ማስረጃ ካሉን ደግሞ
قال رسول الله صلى الله عليه وسلم
كان الله ولم يكن شيء غيره {رواه البخاري وغيره}
የአሏህ መልእክተኝ እንዲ ብለዋል
አሏህ ከርሱ ሌላ ምንም ነገር ሳይኖር በፊት ነበረ ቡኻሪና ሌሎች ዘግበውታል

اللهم أنت الظاهر فليس فوقك شىء وأنت الباطن فليس دونك شىء
የአሏህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል አንተ ጌታዩ ሆይ አንተ ነህ አዝዛሂር ከአንተ በላይ ምንም ነገር የለም። አንተው ነህ አልባጢን ካንተ በታች ምንም ነገር የለም
قال اﻻمام علي بن أبى طالب رضي الله عنه كان الله وﻻ مكان وهو اﻻن على ما عليه كان}رواه ابو منصور البغدادي في كتابه الفرق بين الفرق ኢማሙ አሊይ እንዲህ አሉ አሏህ ነበረ ነገር ግን ቦታ አልነበረም ቦታ ሳይኖር ያለቦታ ነበር አሁንም ቦታን ከፈጠረ በኃላ ያለ ቦታ ያለ ጌታ ነው{ይህንን ንግግር አቡ መንሱር በግዳዲይ አልፈርቅ በይነ ፈርቅ በተሰኝው ኪታብ ላይ ገልጽውታል
አንብበው አዳምጠው ከተጠቃሚዋች ያርገን ሂፋዙንም አሏህ ያግራልን
የአራቱ መዝሀብ ዑለማኦች ስለ ኢስቲዋእ አንቀፅ ያላቸው አቋም - 1- «ኢማም ማሊክ» ----------- -------- ------ ---
ኢማም ማሊክ በተረጋገጠና ትክክል በሆነ ሰነድ አብዱሏህ ኢብኑ ወህብ ባስተላለፉት እንዲህ ብለዋል፡ ﺛﺒﺖ ﻋﻦ ﺍﻹﻣﺎﻡ ﻣﺎﻟﻚ ﻓﻲ ﻣﺎ ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺒﻴﻬﻘﻲ ﺑﺈﺳﻨﺎﺩ ﺟﻴﺪ ﻣﻦ ﻃﺮﻳﻖ ﻋﺒﺪ ﺍﻟﻠﻪ ﺑﻦ ﻭﻫﺐ ﻗﺎﻝ : ﻛﻨﺎ ﻋﻨﺪ ﻣﺎﻟﻚ ﺑﻦ ﺃﻧﺲ ﻓﺪﺧﻞ ﺭﺟﻞ ﻓﻘﺎﻝ : ﻳﺎ ﺃﺑﺎ ﻋﺒﺪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻌﺮﺵ ﺍﺳﺘﻮﻯ ﻛﻴﻒ ﺍﺳﺘﻮﺍﺀﻩ ؟ ﻓﺄﻃﺮﻕ ﻣﺎﻟﻚ ﺭﺃﺳﻪ ﻓﺄﺻﺎﺑﺘﻪ ﺍﻟﺮﺣﻀﺎﺀ ﺛﻢ ﺭﻓﻊ ﺭﺃﺳﻪ ﻓﻘﺎﻝ : ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻌﺮﺵ ﺍﺳﺘﻮﻯ ﻛﻤﺎ ﻭﺻﻒ ﻧﻔﺴﻪ ﻭﻻ ﻳﻘﺎﻝ ﻛﻴﻒ ﻭﻛﻴﻒ ﻋﻨﻪ ﻣﺮﻓﻮﻉ ﻭﺃﻧﺖ ﺭﺟﻞ ﺳﻮﺀ ﺻﺎﺣﺐ ﺑﺪﻋﺔ ﺃﺧﺮﺟﻮﻩ ﻗﺎﻝ : ﻓﺄﺧﺮﺝ ﺍﻟﺮﺟﻞ " ﺍﻩ

{ማሊክ ኢብኒ አነስ ዘንድ እያለን አንድ ሰውዬ
ገባና እንዲህ ኣለቸው፦ የአብዱላህ አባት ሆይ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻌﺮﺵ ﺍﺳﺘﻮﻯ ﻛﻴﻒ ﺍﺳﺘﻮﻯ
አሏህ በዐርሽ ኢስቲዋእ አደረገ ኢስቲዋኡ እንዴት ነው? በማለት ሲጠይቅ ኢማም ማሊክ ኣጎንብሰው (ከባድ በሆነ ላብ) ተውጠው ከዚያም ቀና ብለው እንዲህ ኣሉት «ረሕማን አርሽ ላይ ኢስቲዋእ ማድረጉ እሱ እንደ ገለፀው ነው ለርሱ እንዴት አይባልም እንዴታነት በሱ ላይ የተነሳ ነው (እንዴታ ለርሱ ተገቢ አይደለም) እንተ ደሞ መጥፎ እና የቢድዓ ሰው ነህ አስወጡት» ከዚያም ሰውዬውን አስወጡት። ኢማም ማሊክ እንዴታነት በሱ ላይ የተነሳ ነው (እንዴታ ለርሱ ተገቢ አይደለም) ማለታቸው፤ የአሏህ ኢስቲዋእ በእንዴታነት ሁናቴ አይደለም እንደፍጡራኑ እንደ መቀመጥና ከዛም በላይ ከፍ አለ በመሳሰሉት አይደለም
••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ዒልሙዲን ኢስላማዊ ስቱድዮ
ክፍል 2 ይቀጥላል……
https://t.me/elmudinIslamicstudio/13755
2.1K views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 10:19:25 የኡድሒያ እርድ ህግጋት ክፍል 1
ማታ ከተሰጠው ደርስ
2.7K views07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 11:19:44 ወቅታዊ ጉዳይ ክፍል 1
ኡስታዝ ሀቢብ ኑሩ
2.5K views08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 21:49:46 *እጅግ ወሳኝ እና አገብጋቢ ወቅታዊ ጉዳይ*

ተበዳዮቹ በዳዮች ይከሷቸዋል ብሎም ያስሯቸዋል ከቶ በየትኛው ህግ

*ሸይኽ ኡመር ኢማም አይታሰሩም።!!*

*የሙስሊሙ መሪ አሚራችን አባታችን ሙፍቲም አልወረዱም ነገም አይወርዱም!!!*

የየትኛው ሀገር ህግ ነው ተበዳይን እሰር የሚል

ያጀመአ ሁላችሁም ይሄንን ወቅታዊ ጉዳይ ችላ ሳትሉ ላይክ ሼር በማድረግ ድምፅ ሁኑ አላፊነታችሁን ተወጡ አማና ግደታችን ነው



822 views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ