Get Mystery Box with random crypto!

New Life Ministry

የቴሌግራም ቻናል አርማ new_life_ministry — New Life Ministry N
የቴሌግራም ቻናል አርማ new_life_ministry — New Life Ministry
የሰርጥ አድራሻ: @new_life_ministry
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.07K
የሰርጥ መግለጫ

በክርስቶስ አዲስ ሕይወት አገኘን!
እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን።
ወደ ሮሜ ሰዎች 6 : 4
@newlifeministrybot
2013 የከፍታ ዓመታችን ነው!!
@NEW_LIFE_MINISTRY
@AMBASSADORLIFE

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-25 11:09:23
445 views08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 23:10:08 Watch ""ጊዜዉ ደርሷል " New Amazing song singer biruk gebretsadik #2022" on YouTube


729 views20:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 23:43:58 Watch "#ሰበር ዜና -ዮኒ ወጣቶቹን እራት እየበሉ ሰርፕራይዝ አደረጋቸዉ መልካም ወጣት ወደተለወጠ ህይወት #2014" on YouTube


749 views20:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 23:23:35 Watch ""እንደ ዛሬ ተደስቼ አላዉቅም" መልካም ወጣት ወደ ተለወጠ ህይወት 2014 #youtube #yonatan_aklilu" on YouTube


649 views20:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 08:08:48 ተወደናል!

የማቴዎስ ወንጌል 3
17፤ እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፡ አለ።

ክርስቶስ፣ አብ እርሱን በወደደበት ፍቅር እንደወደደን ነግሮናልና ሰማይ ተከፍቶ፣ ''በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው'' ተብሎ የመጣው ድምጽ በአዲስ ኪዳን የእኛ ቃል ሆኗል!

ከእግዚአብሔር ፍቅር ማለትም እርሱ ለእኛ ካለው ፍቅር ሊለየን የሚችል አንዳች የለም! ዮሐንስ በወንጌሉ ውስጥ እራሱን ሲጠራ፣ ''ክርስቶስም ይወደው የነበረው ደቀመዝሙር'' ብሎ ነው! ይህ ግን ክርስቶስ ከሁሉም የበለጠ ዮሐንስን መውደዱን ሳይሆን ዮሐንስ ከሌሎቹ በተሻለ መልኩ ስለተወደደበት ፍቅር መገለጡ እንዳለው ነው የሚያሳየው! ለእግዚአብሔር ባለህ ፍቅር በመደገፍ እንደ ጴጥሮስ በራስህ ሥራ አትመካ! ይልቁን የተወደድክበትን ፍቅር በማወቅ ስር ስደድ! ምክንያቱም መጽሐፍ፣ '' እርሱ አስቀድሞ ወድዶናልና እንወደዋለን'' ብሎ ስለሚል!

ሁልጊዜ በእግዚአብሔር ዘንድ ተወዳጆችና ደስ የተሰኘብን ውድ ልጆቹ ነን! ዋጋችን ክርስቶስ ነውና!

ወንድም ቢንያም ተስፋዬ

@ye_adis_kidan_hiwot
686 views05:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 08:48:11 ሁሉን እንችላለን!

ወደ ፊልጵስዩስ 4
13፤ ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።

ክርስቶስ፣ አብን ለእኛ የተረከ ትክክለኛ የእግዚአብሔር ነጸብራቅ ብቻ ሳይሆን እውነተኛ ማንነታችንን ገልጦ ያሳየን መስታወታችን ነው! በዚህም፣ በእርሱ የእግዚአብሔርን ሁሉን ቻይነት ብቻ ሳይሆን ለእኛ ለአማኞች ሁሉ መቻሉን አየን!

''ይህ ለእግዚአብሔር ቀላል ነው'' አትበል! የተፈለገው ለእግዚአብሔር መቅለሉ ሳይሆን የአንተ ቀሎክ መኖር ነው! በመሰረቱ፣ አንድ ወንድማችን እንዳለው፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ከባድም ቀላልም ነገር የለም! ከባድና ቀላል የሰው ቋንቋ ናቸውና!

ወዳጄ፣ ሁሉን መቻል ምንጫችን ከሆነው ከእግዚአብሔር የተካፈልነው ማንነት ነው እንጂ በአነቃቂ ንግግር የሚመጣ የአዕምሮ ውጤት አይደለም! ሁሉን መቻል ተሰቶኛል!

ወንድም ቢንያም ተስፋዬ

@ye_adis_kidan_hiwot
964 views05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 15:26:56
> **heavenly youth fire** ** conference**
#መቅረት_አይቻልም።
##ነሐሴ_11_እና_12_እሮብ_እና_ሐሙስ_ከ_8_ሰአት_ጀምሮ
##መንፈስቅዱስ_ሊሰራ_ባለበት_በዚህ_ጊዜ_ወጣቶችን_በመንፈስ_በእሳት_እና_በሀይል_ቀብቶ_ለማስነሳት_መንፈስቅዱስ_በብርቱ_ይፈልጋል። ስለዚህ ወጣቶች ዘመኑ ስለደረሰ እንነቃ ዘንድ ይገባል።**
910 views12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 22:24:43 መንፈስ ቅዱስ

በብሉይ ኪዳን አንድ ሊቀ ካህናት በመቅደስ ሲያገለግል፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ያውቅ ዘንድ፣ ኡሪምና ቱሚም የተባሉትን ሁለት ድንጋዮች በደረት ኪሱ ውስጥ በማድረግ ወደ እግዚአብሔር ይቀርባል።

ክርስቶስ፣ ''እርሱ ለእኔ ካለው ወስዶ ይነግራችኋል፣ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል'' በማለት ስለ መንፈስ ቅዱስ ነገረን! በዚህም፣ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መንፈስ ለሆነው ትክክለኛ ማንነታችን የሚመሰክርልን የአዲሱ ኪዳን ኡሪምና ቱሚም ሆነ!

ወንድም ቢንያም ተስፋዬ

@ye_adis_kidan_hiwot
874 views19:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 07:20:27 ብልጥግና!

1ኛ ቆሮንቶስ 1
4፤ በክርስቶስ ኢየሱስ ስላመናችሁ በተሰጣችሁ በእግዚአብሔር ጸጋ ምክንያት ሁልጊዜ ስለ እናንተ አምላክን አመሰግናለሁ፤

5-6፤ ለክርስቶስ መመስከሬ በእናንተ ዘንድ እንደ ጸና፥ በነገር ሁሉ በቃልም ሁሉ በእውቀትም ሁሉ በእርሱ ባለ ጠጎች እንድትሆኑ ተደርጋችኋልና።

ጳውሎስ፣ በቆሮንጦስ ላለችው ለእግዚአብሔር ቤተክርስትያን፣ ''በክርስቶስ ኢየሱስ ከማመናችሁ የተነሣ በነገር ሁሉ፣ በቃልም ሁሉ በእውቀትም ሁሉ ባለጠጋ ተደርጋችኋል!'' ብሎ አለ!

ወንጌል ያበለጥጋል! ወንጌል አያበለጥግም ብሎ ማለት ዉኃ ውስጥ ገብተህ ሳትረጥብ እንደ መቅረት ነው!

ብዙ ሰው በገንዘብ አቅጣጫ ያለውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ መንካት ስለማይፈልግ፣ አዲስ ኪዳንን የመንፈሳዊ በረከት(ጽድቅ፣ ቅድስና፣ ክብር፣ ልጅነት) ብቻ አድርጎ ለማስቀመጥ ይሞክራል። በአዲስ ኪዳን፣ ከሰማያዊ ጥሪ ተካፋዮች በመደረግ፣ በክርስቶስ የመስቀል ሥራ ጽድቅና ቅድስና ልጅነትና ክብር ለእኛ ቢሆንም መንፈሳዊ በረከትን ባገኘንበት በዝያው በክርስቶስ የመስቀል ሥራ የአብርሀም ዘር በመሆን በአብርሀም በረከት ተባርከን የምድርም ባለጠጎች ተደርገናል!

ወዳጄ፣ ሰማይ ቤት ስትሄድ ታርፋለህ፣ ትበለጥጋለህ እያለ ለሞት ከሚያዘጋጅህ ትምህርት ፈጥነህ ራቅ! ሰማይ ቤት የሚነዳህ መኪና እንደሌለህ ላስታውስህ! መዝሙረኛው፣ ''እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፣ የሚያሳጣኝም የለም'' ብሎ ያለው ለምድር ህይወቱ እንጂ ለሰማይ አይደለም! አባቴ ባለጠጋ ነው፣ እኔም በብልጥግናው እኖራለው!

ወንድም ቢንያም ተስፋዬ

@ye_adis_kidan_hiwot
1.2K views04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 12:03:04 የጌቶች ጌታ

የዮሐንስ ራእይ 5
9-10፤ መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ ይነግሣሉ፡ እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ።

Revelation 5
10 And made them #kings and priests to our God, And they reign on earth."

መጽሐፍ ቅዱስ፣ ''የሰማይ ሰማያት ለእግዚአብሔር ናቸው፣ ምድርን ግን ለሰው ልጅ ሰጠ'' ብሎ ይናገራል! በዚህም፣ እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው ያመልከው ዘንድ ሳይሆን ''ምድርን ግዟት'' በተባለው ቃል መሰረት፣ የእግዚአብሔርን አይነት ህይወትና አገዛዝ በተፈጠረለት ቁሳዊ ዓለም ላይ ገልጦ ይኖር ዘንድ ነው!

የምድር ገዢ ወይም ጌታ ሰው ነው! አዳም ከእግዚአብሔር በመለየት ይህን ስልጣኑን ለሰይጣን ቢሰጥም፣ በክርስቶስ የመስቀል ሥራ፣ ይህ ስልጣን ተመልሶልናልና የምድር ጌታ ተደርገናል!

አሁን፣ ክርስቶስ ኢየሱስን የጌቶች ጌታ የነገሥታት ንጉስ ብለን ስንል ጌቶችና ነገሥታት እኛ ስንሆን እርሱ ደግሞ የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉስ ነውና ጌታችንና ንጉሳችን ነው! ባለስልጣናት ተደርገናል!

ወንድም ቢንያም ተስፋዬ

@ye_adis_kidan_hiwot
1.2K views09:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ