Get Mystery Box with random crypto!

New Life Ministry

የቴሌግራም ቻናል አርማ new_life_ministry — New Life Ministry N
የቴሌግራም ቻናል አርማ new_life_ministry — New Life Ministry
የሰርጥ አድራሻ: @new_life_ministry
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.07K
የሰርጥ መግለጫ

በክርስቶስ አዲስ ሕይወት አገኘን!
እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን።
ወደ ሮሜ ሰዎች 6 : 4
@newlifeministrybot
2013 የከፍታ ዓመታችን ነው!!
@NEW_LIFE_MINISTRY
@AMBASSADORLIFE

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-19 08:30:44 የእግዚአብሔር ስጦታ


የዮሐንስ ወንጌል 14
15-16፤ ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ #ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ (* አጽናኝ ማለት በግሪክ ቋንቋ ጰራቅሊጦስ ማለት ነው)


በአሮጌው ኪዳን፣ ሰዎች እንኳን ሀጢአት ሰርተው፣ ሀጢአት ባይሰሩ እንኳን መንፈስ ቅዱስ ለተወሰነ ዓላማ አንዴ በእነርሱ ላይ ይገለጥና መስራት የፈለገውን ሰርቶ ይሄድ ነበርና፣ ዳዊት፣ ''ቅዱሱ መንፈስህን አትውሰድብኝ'' ብሎ ጸለየ።

በአዲስ ኪዳን ግን መንፈስ ቅዱስ ተመላላሽ ጎብኚ ሳይሆን ለዘላለም በእኛ ያደረ መንፈስ ነውና ''መንፈስህን አትውሰድብኝ'' አይባልም!
መንፈስ ቅዱስን እኛ ጋር የሚያቆየው መልካም ሥራችን ሳይሆን ልጅ መሆናችን ብቻ ነውና!

መጽሐፍ፣ ''ቅዱሱን መንፈስ አታሳዝኑ'' አለ እንጂ ''ይወሰድባችኋል'' አላለም! መንፈሰ ቅዱስ፣ ለጥቅማችን ለዘላለም በእኛ አድሯልና ስንደክም እራሱ የሚያዝነው በእኛ ሳይሆን ለእኛ ነው! ይህንን ዘላለማዊ ወዳጅ ተደሰቱበት፣ ተጠቀሙበት!

ወንድም ቢንያም ተስፋዬ

@ye_adis_kidan_hiwot
1.3K views05:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 13:35:10 ከልጁ ጋር!


የማቴዎስ ወንጌል 6
33፤ ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።


ክርስቶስ፣ ''ይህ ስለ ብዙዎች የሀጢአት ይቅርታ የሚፈሰው የአዲስ ኪዳን ደሜ ነው'' ብሎ ያለውን ደሙን በመስቀል ከማፍሰሱ በፊት፣ ''አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን ጽድቅና መንግሥት ፈልጉ፣ ሌላው ሁሉ ይጨመርላችኋል'' ብሎ አስተማረ።

አሁን ያለንበት አዲሱ የጸጋው ኪዳን ደግሞ ከፈሰሰው ከክርስቶስ ደም የተነሣ፣ የእግዚአብሔር ጽድቅና መንግሥት እኛ ጋር የደረሰበት ኪዳን ነውና አሁን ይጨመራል የተባለው ላይ ነን! ይጨመራል የተባለው ደግሞ ቁሳዊ ነገር ነው! እግዚአብሔር አባታችን ከሁሉ የሚበልጠውን ልጁን እንዲያው ሰጥቶናልና ከልጁ የሚያንሰውን ሁሉ ለጥቅማችን እንዲያው ከልጁ ጋር ሰጥቶናል!

እግዚአብሔር ከሁሉ የሚበልጠውን ልጁን ሰጥቶናል ብለን ከልጁ የሚያንሰውን ቁስ ከለከለን ብሎ ማለት እግዚአብሔር ከልጁ ይልቅ ቁስን ይወዳል ማለት አይሆንብንም? እግዚአብሔር ቁሳዊ ነገር ሁሉ ይኖረን ዘንድ መልካም ፈቃዱ ነው!


ወንድም ቢንያም ተስፋዬ

@ye_adis_kidan_hiwot
1.3K views10:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 19:53:13
Price:2500br
Address: Gerji roba
Phone: 0963122703
58 views16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-03 22:00:07

2.0K views19:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-28 13:34:37

2.2K views10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-07 13:43:47 Watch "የስኬት ትርጉም The meaning of Success, Ethiopian Motivational Video" on YouTube


3.2K views10:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-22 19:14:05 Watch "ሰይጣን ሆይ ልጅ ስጠኝ አስገራሚ መልዕክት እረኛዬ" on YouTube


3.8K views16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-15 10:44:18 ክርስቶስ የአዲስ ኪዳን የፋሲካ በግ!

ዘጸአት 14

የብሉይ ፋሲካ መሥዋዕት ነዉር አልባ ነበር!

ክርስቶስ ነዉር የሌለበትና ፍጹም ንጹህ የሆነ የእግዚአብሔር በግ ነዉ!

የሞት መላዕክ የመሥዋዕቱን ደም በእስራኤላዉያን መቃንና ጉበን ላይ በማየት አለፋቸዉ!

መጽሐፍ፣ "ደም ሳይፈስ ስርየት የለም"፣ "የሀጢአት ደሞዝ ደሞ ሞት ነዉ" ይላልና በክርስቶስ ደም ስርየትን ስላገኘን ከዘላለም ሞት ድነናል!

የእስረኤል ህዝብ የበሉት የፋሲካዉ በግ ሥጋ በእሳት የተጠበሰ መሆን ነበረበት!

የእግዚአብሔር ፍርድና ቁጣ በመስቀል በክርስቶስ ላይ ነዷል፣ በዚህም የእግዚአብሔር ቁጣ ለዘላለም በርዷል!

የእስራኤል ህዝብ የተጠበሰዉን ሥጋ ከመራር ቅጠል ጋር በሉት! ይህም፣ የበጉን ፍርድ መካፈላቸዉን ያሳያል!

እኛም ከክርስቶስ ጋር በመሰቀል መከራን ተቀብለናል፣ ከእርሱ ጋር ተሰቅለናል፣ ከእርሱም ጋር ሞተናል!

የፋሲካዉን በግ ደም በሂሶጵ ቅጠል ነበር በመቃናቸዉና በጉበናቸዉ ላይ የቀቡት!

እኛም የአዲስ ኪዳን ሂሶጵ በሆነዉ እምነት የክርስቶስን ደም በህይወታችን ላይ ረጭተናል!

የፋሲካዉ በግ አጥንት እንዳይሰበር እግዚአብሔር አዘዛቸዉ!

በመስቀል የክርስቶስም አጥንት አልተሰበረም!

በጉ በአስረኛዉ ቀን ይያዝና እስከ አስራ አራተኛዉ ቀን ድረስ ተይዞ ይቆያል! ይህም መሥዋዕት ከመሆኑ በፊት 5 ቀን ይጠብቃል ማለት ነዉ!

ክርስቶስም ከተያዘ በኋላ 5 ቆየ፣ ከዝያም የዓለምን ሀጢአት ሊያስወግድ መሥዋዕት ሆነ!

የበጉን ሥጋ የበሉ ሁሉ ጤነኛ ሆኑ(መዝ 105:37)

የክርስቶስ ሥጋ ለጤንነታችን ተገርፏልና በመገረፉ ቁስል እኛ ተፈወስን!

በረከት ናችሁ!

ወንድም ቢንያም ተስፋዬ

@ye_adis_kidan_hiwot
@new_life_ministry
3.8K views07:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-15 10:05:43 ቅድስና!

1ኛ ቆሮ 6:11

11 ከእናንተም አንዳንዶቹ እንደ እነዚህ ነበራችሁ፤ ነገር ግን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ ታጥባችኋል፥ #ተቀድሳችኋል፥ ጸድቃችኋል።

ቅድስና በማድረግ የሚገኝና ባለማድረግ የሚጠፋ የራስ ጥረት ዉጤት ሳይሆን ከእግዚአብሔር የሆነና ለአማኞች በነጻ የተሰጠ አንዱ የመለኮት ባህሪ ነዉ! ቅድስና የሚለዉ ቃል መለየት የሚልን ትርጉም ይዟል! በዚህም፣ ለእግዚአብሔር መለየት ቅድስና ሲሆን ከእግዚአብሔር መለየት ደግሞ ሀጢአት ነዉ።

በብሉይ ኪዳን ተራራ ቅዱስ የተባለዉ እግዚአብሔር ስለነካዉ ነዉ እንጂ ተራራዉ ሕግን ጠብቆና መልካም አድርጎ አይደለም፣ የቤተ መቅደስ እ
ዕቃዎችም ቅዱስ የተባሉት ጸባይ አሳምረዉ ሳይሆን ለእግዚአብሔር ስለተለዩ ነዉ፣ ቤተ መቅደሱ እራሱ ቅዱስ የሆነዉ እግዚአብሔር ስላደረበት እንጂ ታዛዥና ባለ መልካም ስብዕና ስለሆነ አይደለም!

ወዳጄ፣ በጸጋ ተቀድሰናል! በክርስቶስ ከእግዚአብሔር ለይቶን የነበረዉ ሀጢአት ተወግዷልና ለእግዚአብሔር ተለይተናል! በዚህም እግዚአብሔር የራሱን አይነት ቅድስና በዉስጣችን በማየት ቅዱሳን ብሎ ጠርቶናል!

በረከት ናችሁ!

ወንድም ቢንያም ተስፋዬ

@ye_adis_kidan_hiwot
@new_life_ministry
2.7K views07:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-08 22:23:10

share share
2.3K views19:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ