Get Mystery Box with random crypto!

የጌቶች ጌታ የዮሐንስ ራእይ 5 9-10፤ መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃ | New Life Ministry

የጌቶች ጌታ

የዮሐንስ ራእይ 5
9-10፤ መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ ይነግሣሉ፡ እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ።

Revelation 5
10 And made them #kings and priests to our God, And they reign on earth."

መጽሐፍ ቅዱስ፣ ''የሰማይ ሰማያት ለእግዚአብሔር ናቸው፣ ምድርን ግን ለሰው ልጅ ሰጠ'' ብሎ ይናገራል! በዚህም፣ እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው ያመልከው ዘንድ ሳይሆን ''ምድርን ግዟት'' በተባለው ቃል መሰረት፣ የእግዚአብሔርን አይነት ህይወትና አገዛዝ በተፈጠረለት ቁሳዊ ዓለም ላይ ገልጦ ይኖር ዘንድ ነው!

የምድር ገዢ ወይም ጌታ ሰው ነው! አዳም ከእግዚአብሔር በመለየት ይህን ስልጣኑን ለሰይጣን ቢሰጥም፣ በክርስቶስ የመስቀል ሥራ፣ ይህ ስልጣን ተመልሶልናልና የምድር ጌታ ተደርገናል!

አሁን፣ ክርስቶስ ኢየሱስን የጌቶች ጌታ የነገሥታት ንጉስ ብለን ስንል ጌቶችና ነገሥታት እኛ ስንሆን እርሱ ደግሞ የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉስ ነውና ጌታችንና ንጉሳችን ነው! ባለስልጣናት ተደርገናል!

ወንድም ቢንያም ተስፋዬ

@ye_adis_kidan_hiwot