Get Mystery Box with random crypto!

ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️

የቴሌግራም ቻናል አርማ mirttshefoch — ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️
የቴሌግራም ቻናል አርማ mirttshefoch — ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️
የሰርጥ አድራሻ: @mirttshefoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 31.66K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 20

2023-03-22 03:59:51 ከእራስህ ጀምር!

አዛኝ ልብና ሩህሩህ አንጀት ስላለህ ከእራስህ በፊት ለሌሎች የመድረስ ልማድ ውስጥ ተገኝተህ ይሆናል፣ እራስህን ወደኋላ ብለህ ለሰዎች የምታደርገው ነገር ይኖራል፣ አንተ ሳታገኝ በዙሪያህ ያሉ ሰዎች እንዲያገኙ ብዙ ትጥርም ይሆናል። ይህ እሳቤና ተግባርህ ጥሩ ሆኖ ሳለ በቆይታ ብዛት ያን መልካምና ቅን የተባለውን ሰው እየበደልከውና እየጎዳሀው በሔድክ ልክ ለምትወዳቸው ሰዎችም እስከማትደርስበት ደረጃ ላይ ልትደርስ ትችላለህ። ቅድሚያ ለእራስ መስጠት እራስ ወዳድነት አይደለም፤ ለሌላውም ማድረግ የሚገባውን ችላ ማለት አይደለም። በሁለት እግሩ ያልቆመ ሰው ሌላውን ሊደግፍ አይችልም፤ ለእራሱ በደንብ መመልከት የማይችል ሰው ሌላ ሰው መምራት አይችልም። ለእራስህ የምታደርገው ነገር በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ ለምተረዳው ሰው ይደርሳል። እኔ ብቻ በሚል እሳቤ ሳይሆን እኔ ብቁ ስሆን ብዙዎችን ብቁና ዝግጁ ማድረግ እችላለሁ በሚለው እሳቤ።

አዎ! ጀግናዬ..! ከእራስህ ጀምር! ሰዎችን ለማበርታትና ለማንቃት ከመድከምህ በፊት እራስህን አበርታ፣ እራስህን አነቃቃ፤ ሌሎችን ለመርዳት ከመሯሯጥህ በፊተ እራስህን እርዳ፣ እራስህን አጠንክር፤ ለማስተማር ከመዘጋጀትህ በፊት እራስህን በሚገባ አስተምር፤ ስለደስታ ከማስረዳትህ በፊት ደስተኛነትን ከእራስህ ጀምር። ብርቱ ሰው ሌላውን ለማበርታት አይቸገርም፤ ንቁና ዝግጁ ሰው ሌላውን ለማንቃትና ለማዘጋጀት ብዙ አይፈተንም። በውስጥህ የፈጠርከው ጥንካሬ ባትፈልግ እንኳን ወደ ቀረቡህ ሰዎች ይጋባል፤ ከውስጥህ የሚመነጨው ደስታ ከቃል በላይ በተግባር ደስታን ሲፈጥር ትመለከተዋለህ። ሁሌም መነሻው እውነተኛ ማንነት ሲሆን ውጤቱም በእጀጉ አመርቂና አስደሳች ይሆናል።

አዎ! ሰዎችን ለመለወጥ ብዙ መድከም ካልፈለክ በቅድሚያ እራስህን ለመለወጥ ድከም፤ አርዓያ ለመሆን ተፋለም። በብዙዎች ተቀባይነት ማግኘት ከፈለክ በመጀመሪያ እራስህን ሙሉ በሙሉ ተቀበል፤ ስለ ይቅርታና ውስጣዊ ሰላም ከማስረዳትህ በፊት እራስህ የይቅርታ ልብ ይኑርህ፣ እራስህ ሰላም ሁን፣ ውስጥህን አረጋጋ፣ በእራስህ ደስታን ፍጠር። አንተ ጋር የሌለን ነገር ለመስጠት ብትታገል ትርፉ ድካምና ህመም ብቻ ነው። ልባዊ እርዳታና ፍሰት ያለው አበርክቶት መነሻው ሆኖ መገኘት ነው። የሆንከውን ለመስጠት ፍረሃትም ሆነ ጭንቀት አይኖርብህም። እራሱን መጠበቅ የሚችል ሰው ለሌላው ከለላ መሆን አይከብደውም፤ ሌላውን መታደግና መንገድ መምራት አያስቸግረውም። የትም ከመሔድህ በፊት የሚፈልግህ ማንነት ውስጥህ እንዳለ አስተውል። ማንንም ከማከምህ በፊት እራስህን ማከምና መፈወሱን እወቅበት፤ ስለማንም መልካም ነገር ከማሰብህ በፊት ስለ እራስህ ጥሩና መልካም ነገር አስብ፤ ማንንም ከማድነቅህ በፊት እራስህን አድንቅ። ያንተ ጥሩ ሃሳብ ሙሉ የሚሆነው፣ አድናቆትህም ከልብህ የሚመነጨው፣ በስሜት የሚመራው እራስህ ላይ የተተገበረ እንደሆነ ነው።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
28 viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  00:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-22 03:59:20 ለምን አሉታዊነትን?

ሰውነት ሚዛን እያለው፣ መልካም ማሰብና ማድረግ እየቻለ፣ ለሰዎች ጥሩ መፈፀም እየቻለ ግና በአሉታዊነት ገመድ ታስሮ እራሱን ጥሎ ሌሎችን ለማሰናክልና ለመጣል ይደክማል። አሉታዊነት ቢጎዳ ቀዳሚው ተጎጂ አንተ ነህ፣ አዎንታዊነት ቢጠቅም ቀዳማዊው ተጠቃሚ አንተ ነህ። ለማንም ለምንም ብለህ ሳይሆን አሉታዊና እንቅፋት ከመሆን ይልቅ ዝም የማለት ምርጫም አለህ። ያንተ ውድቀት ሳያንስ ሌላውንም ወደ ውድቅት ለመሳብ አትድከም። መደጋገፍን፣ መረዳዳትን፣ መበረታታትን የመሰለ መልካም ምግባር እያለ ስድብን፣ ነቀፋን፣ ክፋትን መምረጥ የምትወድቅበትን ጉድጓድ ቢያርቀው እንጂ በህይወትህ አንዳች የሚጨምርልህ ነገር አይኖርም። አንድ ሰው በገዛ ፍቃዱ ፈልጎና መርጦ ያደረገውን ነገር ግዴታ የመውደድና የማድነቅ ግዴታ የለብህም፤ እንዲሁ ባንተ የእሳቤ ደረጃና አቅጣጫ እንዲፈፀም መጠበቅ አይኖርብህም። አንተ ባትችል የሚችሉት ችለው፣ አድርገው ቢገኙ የምታጣው ነገር ምን ይሆን?

አዎ! ጀግናዬ..! ለምን አሉታዊነትን? ለምን ክፋትን? ለምን ስድብን? ለምን ነቀፋን? ለምን ሰዎችን በሚያደናቅፍ መንገድ መታወቅን ፈለክ? መጥፎ፣ ጎጂና አጥፊ ስሜት ሆኖ ሳለ ስለምን ከዝምታና ከአዎንታዊነት፣ ደግ ከማሰብ እርሱን መረጥክ? የሚገነባህ አዎንታዊነት ሆኖ ሳለ ስለምን በሚያፈርስህ አሉታዊነት ትመላለሳለህ? የሚጠቅምህ መልካም ማሰብ ሆኖ ሳለ ስለምን ክፋትን መረጥክ? ሰላም ያለው፣ ፍቅር የሚነግሰው፣ መትረፍረፍ የሚመጣው በጥላቻ ውስጥ አይደለም፤ በሰው ውድቀት ውስጥ አይደለም፤ በአሉታዊነትና የሌሎችን ስሜት በመንካት አይደለም። የሰላም ምንጭ አዎንታዊነት ነው፤ ደስታ መገኛው መልካምነት ነው፤ የሃሴት ማደሪያ ቅንነት ነው፤ የመትረፍረፍ መሰረቱ ደግነት ነው።

አዎ! የሚጥረውን ስላበረታታህ፣ ለደከመው ብርታት ስለሆንክ፣ ተስፋ ላጣ ተስፋን ስለሰጠህ፣ በህይወት መንገዱ ድጋፍ ለሚፈልግ ድጋፍ ስለሆንክ የምታገኘው እንጂ መቼም የምታጣው ነገር አይኖርም። በህይወትህ የሚገለጠው በሰዎች ላይ የምታንፀበርቀውና የምታደርገው ነገር ነው። የሌሎችን ድካም መረዳት ከቻልክ ሁሌም ከጎንህ የሚቆም ሰው አታጣም፤ የድጋፍ እጅህን የማትሰስት ከሆነ ሁሌም የምትደገፈውን ከጎንህ ታገኛለህ። የማይወክልህን አሉታዊነት፣ የማይገልፅህን ክፍታ እንድታንፀበርቅ የሚያደርግህን ኢጎ (ego) ከእራስህ ላይ አስወግድ፤ ማንንም ከማይጠቅም ጭፍን ጥላቻና ምቀኝነት ውጣ። መልካም አስብ፣ መልካም አድርግ፣ በመልካም መንገድ ተመላለስ፣ የሚሰራን ደግፍ፣ የሚለፋን ከልብህ አበረታታ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
30 viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  00:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 21:22:32
“በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ስታልፊና እጅ ላለመስጠት ስትወስኝ ጠንካራ ሴት ትሆኛለሽ። ብዙ ጊዜ ጥንካሬ ከማሸነፍ አይመጣም ተሸንፈሽም ጥረትሽ ጥንካሬን ያጎናጽፍሻል። እውን ልታደርጊው የምትፈልጊዉ ነገር ላይ በጭራሽ ተስፋ አትቁረጭ። ትልቅ አላማ ይኑርሽ ምክንያቱም ትልልቅ አላማዎችን የያዙ ግለሰቦች ባዶ እጃቸውን ሆነው እንኳን ሁሉንም ከያዙ ሰዎች የበለጠ ኃያሎች ናቸው።”
“ሁሉም ሰው ሲወለድ ቦታ እና ጊዜ እንዲሁም የቤተሰቦቹን የሕይወት ደረጃ መምረጥ አይችልም። ነገር ግን ወደፊት ማን እና ምን መሆን እንዳለበት መምረጥ ይችላል። የአንቺም ሕይወት እንዲሁ ነው። ማስተካከል ትችያለሽ። የሆነብሽን ሁሉ ረስተሽ የምታስቢውን ለመሆን በቂ ጥረት ማድረግ አለብሽ። ስኬታማ ሰው ማለት ሌሎች በወረወሩበት ድንጋይ ጠንካራ መሰረት የጣለ ሰው እንጅ መልሶ የወረወረ አይደለም።”
“ለስኬት የመጀመሪያው እርምጃ የምትወስጅው ራስሽን መጀመሪያ ካገኘሽበት ቦታ ምርኮኛ ላለማድረግ በምትቃወሚበት ጊዜ ነው። ለራስሽ ጥሩ ግምት ይኑርሽ፤ ደስታ የምታገኝበትን መንገድ በመምረጥ አካሄድሽን በቁጥጥርሽ ስር አድርጊ፤ ጥንካሬ እና እድገት የሚመጡት በማያቋርጥ ትግል እና ጥረት እንደሆነ ውስጥሽን አሳም
//ከሉባር መጽሐፍ የተወሰደ//
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
1.3K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 20:40:24
አንድ ጊዜ ታዋቂው ሳይንቲስተት አልበርት አይንስታይን በክፍል ውስጥ ባለው ሰሌዳ ላይ የሚከተሉትን ስሌቶች እየጻፈ ለተማሪዎቹ እያሳየ ነበር ፡-

(9 X 1 = 9) . . .
(9 X 2 = 18) . . .
(9 X 3 = 27) . . .
(9 X 4 = 36) . . .
(9 X 5 = 45) . . .
(9 X 6 = 54) . . .
(9 X 7 = 63) . . .
(9 X 8 = 72) . . .
(9 X 9 = 81) . . .
(9 X 10 = 91)

ከእነዚህ የሂሳብ የድምር ስሌቶች ሁሉም ትክክል ሆነው ሳለ ለመጨረሻው የሰጠው መልስ 90 መሆን ሲገባው 91 በመሆኑ እንደተሳሳተ የተመለከቱ ተማሪዎቹ በጣም ሳቁበት ፡፡ “ይህንን የመሰለ ሊቅ እንዴት ይሳሳታል” ነበር የሳቁ መነሻ ፡፡

እሱም ሳቃቸውን እስከሚጨርሱ ጠበቀና ፣ “የመጀመሪያዎቹን ዘጠኙን ጥያቄዎች በትክክል መመለሴን በማንሳት ማንም ተማሪ አላደነቀኝም ፡፡ ነገር ግን አንዷን ስለተሳሳትኩኝ ብቻ ሁላችሁም ሳቃችሁብኝ ፡፡ ይህ ማለት ምንም እንኳ በአብዛሃኛው ነገር ስኬታማ ብትሆኑም ሕብረተሰቡ አንዷንና ትንሿን ስህተት የማጉላት ዝንባሌ አለው ፡፡

ስለዚህ ምን እንደበረዶ ብትነጣ ከሰዎች ትችትና ነቀፌታ አታመልጥምና ለሰዎች ብለህ ትልቁን ሕልምህን ከማሳካት ወደኋላ አትበል ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
1.6K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 07:06:41 ቀጂነት!
፨፨//፨፨
አንድ ሰው በሕልሙ ፈጣሪን አገኘውና አጋጣሚውን በመጠቀም ሁል ጊዜ በእውኑ ያስብ የነበረውን ጥያቄ ጠየቀው ይባላል - በጥንት አፈ-ታሪክ፡፡ ጥያቄው እንዲህ የሚል ነበር፡- “ከአፈር ሰውን ማበጀት እኮ ያን ያህል ከባድ አይደለም፣ ለምን እንደተአምር ይታያል?” አጠያየቁ ለክርክር በተዘጋጀ ዝንባሌ እንደነበረ የፊቱ አስተያያት ያሳብቅበታል፡፡ ፈጣሪም፣ በታላቅ ትእግስትና ርህራሄ እየተመለከተው፣ “እስቲ ሰውን ከአፈር መስራት ቀላል ከሆነ ከአፈር ሰውን ፍጠርና አሳየኝ” በማለት መለሰለት፡፡ ሰውየውም አፈር ከመሬት ለማንሳትና ስራውን ለመጀመር ጎንበስ ሲል፣ ፈጣሪ አቋረጠውና “ያሰብከውን ሰው ለማበጀት ከመነሻው የራስህን አፈር መጠቀም አለብህ” አለው ይባላል፡፡

ቀጂነት፣ የእኛ ያልሆነውን ነገር የእኛ እንደሆነ ማስመሰል፣ አዲስ ነገር ከመጀመር ይልቅ ሌላው አንድ ነገር ሲጀምር አጠገቡ ሄዶ ያንኑ መድገም፣ አዳዲስ ነገሮች የጀመሩ ሰዎችን ስራ ማንቋሸሽና ማራከስ  . . . የዘመናችን ችግር! ብዙ ሰው የራሱን ነገር ከመጀመርና አዲስ ፈር ከመቅደድ ይልቅ የሌላውን ማየት፣ መከታተልና መቅዳት፣ አልፎም ማራከስ ይቀናዋል፡፡ በቢልየን የሚቆጠር የአለም ሕዝብ የጣት አሻራ በማይመሳሰልበት … የዚህ ሁሉ ሕዝብ የአይን ንድፍ በሚለያይበት … የሁላችን የጸጉር መለያ ኮድ በማይገናኝበት … በየሃገራቱ የሚወርዱ የበረዶ ብናኝ ቅርፊቶች (Snowflakes) ቅርጽ በሙሉ አንድ አይነት ባልሆነበት … በፈጠራ ውበት በሞቀና በደመቀበት አለም ውስጥ እየኖርን የሌላውን ሰው ግኝትና ጅማሬ ካልቀዳን ወይም ካላዋደቅን የምንሻሻል ካልመሰለን፣ የሆነ የጎደለ ነገር አለ፡፡

በጉዳዩ ላይ በሚገባ ለማሰላሰልና ወደ እውነት ለመጓዝ . . . 
- ሌላ ሰው ጋር የሌለና አንተ ጋር ብቻ ያለ የፈጠራ እይታና ብቃት ፈጣሪ ራሱ እንደሰጠህ ማስታወስ ለአዳዲስ ነገሮች እንድትነሳሳ ያደርግሃል፡፡
- ከምንምና ከባዶ ተነስተህ ምንም አይነት ነገር መፍጠር እንዳማትችል ማወቅ ሚዛናዊና እውነታን ያገናዘብክ ሰው ያደርግሃል፡፡
- ያለህ የፈጠራ ብቃት የተነሳው በሌሎች ፈር-ቀዳጅነት መሰረት ላይ መሆኑን መገንዘብ ሌላውን አክባሪ ያደርግሃል፡፡
-ለመነሻነት የምትጠቀምባቸውን የሌሎች ሰዎች ፈጠራዎች፣ ግኝቶችና ስራዎች እውቅና መስጠት ትልቅ ሰው ያደርግሃል፡፡
- የሰውን ሃሳብ፣ ፈጠራና የአእምሮ ንብረት አለመስረቅ ጨዋና መልካም ዜጋ ያደርግሃል፡፡
- የግድ ከሌላው ሰው ካልቀዳህና ካልኮረጅክ ምንም ነገር ማድረግ እንደማትችል ከማሰብ ነጻ መሆን ከጠባብነትና ከውስንነት እንድትወጣ ያደርግሃል፡፡
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
3.0K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 07:06:14 እውነተኛው ፍቅርህ ያስችልሃል!
፨፨፨፨፨፨//////////////፨፨፨፨፨፨
በፍቅር መጣህ በፍቅር ፀጋ ፍቅርን ለበስክ፣ ምድርን ባረካት፣ ነፃም አወጣሃት። የታላቁን ሃይል የፍቅርን ፍፁምነት በመስቀሉ በመሰዋት፣ እራስህን በመስጠት አሳየሀን። አምላክ ለሚወደን ልጆቹ ለፍቀሩ ሲል እራሱን ለሞት አሳልፎ ሰጠ። መውደድ ዋጋው ይህን ያክል ነው፤ ፍቅር ክፍያው እዚህ ይደርሳል። ማንም ለወደደው ነገር እስከ ሞት መሶዓትነት የመክፈል ሃይል አለው፤ ፀጋው ተሰጥቶታል። ዋናው ጉዳይ ግን እንፈልገዋለን የምንለውን ነገር በእርግጥም እንፈልገዋለን ወይ ነው። የቃላት ፍላጎት ከስሜትና በሙሉ ማንነት ከመፈለግ የተለየ ነው። መንፈሳዊነትን ከልቡ ለሚሽት ሰው በሮች ሁሉ ክፍት ናቸው፤ በመረጠው ዘርፍ አሻራውን ማሳረፍ ለሚፈልግ ሰው መንገዶች አሉ፤ የእራሱን ትርፋማ ስራ መስራት ለሚፈልግ ሰው እድሎች ሞልተዋል። ችግሩ ግን ሪስክ መውሰድ አለመፈለጉ ነው። መንፈሳዊ ህይወቱ ላይ ጠንካራ ከሆነ አብሮ የሚመጣውን ፆም፣ ፀሎት፣ ስግደትና ንሰሃ መግባቱን ይፈራል። በመረጠው ዘርፍ ተፅዕኖ በመፍጠር ውስጥ ገንዘብ ለማግኘት የሚደረገው የብድር መንገድ አደጋ እንዳለው እያሰበ ወደኋላ ይሳባል።

አዎ! ጀግናዬ..! እውነተኛው ፍቅርህ ያስችልሃል፤ ትክክለኛው ፍላጎት ምኞትህን ያሳካዋል፤ የማያቋርጠው መሻትህ የልብህን ያደርሳል። ክርስቶስን መስቀል ላይ ያዋለው፣ ቦሃላም ለሞት አሳልፎ የሰጠው ለእኛ ለልጆቹ የነበረው ፍፁም ፍቅር ነው። ሳይሰቀልና ሳይሞት ሊያድነን ይችል ነበር ነገር ግን የፍቅርን ሃይል ሊያሳየን፣ የመውደዱን ጥግ ሊያስረዳን ተሰቅሎ ሞቶ አድኖናል። ማንም እንደርሱ ፍፁም ፍቅር ላይኖረው ይችላል ነገር ግን የፍቅርን ሃያልነት ያውቃልና ሃይሉ እስከሞት ሊያደርስ እንደሚችል ይገነዘባል። ሰው ለማይረባ ነገር እንኳን እራሱን፣ ማንነቱን፣ ስብዕናውንና ህይወቱን ያጣል። ለሚወደውና ለሚያፈቅረው የህይወት አላማዬና ትርጉሜ ነው ለሚለው ነገር የሚጠበቅበትን ሁሉ ቢወጣ ምንም ከባድ አይደለም።

አዎ! አሁን ባለበት የተመቻቸ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ እፈልገዋለሁ የሚለውን ነገር ማግኘትን መመኘት ከፍቅርና ፍላጎት ይልቅ እያደረ ከንቱ ጊዜያዊ ምኞትና ቅዠት መሆኑ አይቀርም። ከሽንገላ ፍቅር ውጣ፣ በምክንያት፣ በግንና በሰበብ ከተከበበ ፍቅር መሳይ ቅዠት ወይም ምኞት ተላቀቅ። ለምትወደው ነገር መክፈል ያለብህን መሱዓትነት በጊዜ ከፈል፤ የሚጠበቅብህን ሃላፊነት ተወጣ፤ አደጋውን አምነህ፣ ወደህና ፈቅደህ ተቀበል። የፍቅርን ዋጋ በምትወደው ነገር ላይ ተግብረው፤ ከአምላክህ የተማርከውን የመውደድ ጥግ በትንሹም ቢሆን ባለህበት ሙያ፣ ስራ ወይም የህይወት ሃላፊነት ላይ ተግብረው። የሰዎች ደስታ የሚያስደስትህና ከልብህ የምትፈልገው ከሆነ ለእርሱ ብለህ መጓዝ የሚገባህ ድረስ ተጓዝ። በፍቅርህ ልኬት እስከጥግ ተፋለም፤ መሻትህንም በእጅህ አስገባ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
2.6K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 04:16:24
የሰው ልጅ በምድር ላይ ሲኖር ለሦስት ነገሮች መዘጋጀት ይኖርበታል ።
ለኃላፊነት ፣
ለዕውቀትና
ለትዳር ።
ሦስት ነገሮችንም ማክበር አለበት ።
ቃል-ኪዳኑን ፣
ትዳሩንና
ቤተሰቡን ።
ከሰው ጋር ሊያጣሉ የሚችሉ ሦስት ነገሮችን ደግሞ መቆጣጠር ይኖርበታል ።
ምላሱን ፣
ቁጣውንና
ስሜቱን ።
እንደገና ሦስት ነገሮችን መፀየፍ ይኖርበታል ።
ሀሜትን ፣
ተንኮልና
ቅናትን ።
በመጨረሻም ለአንድ ሰው ሦስት መሠረታዊ ነገሮች ያስፈልጉታል ብዬ አምናለሁ ።
እምነት ፣
ተስፋና
ፍቅር!
መልካም ቀን ይሁንላችሁ
3.8K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  01:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 04:12:53 ፋታ ውሰድ!

እዚም እዛም ፈታኝ ሁነት፣ ትናንትም ዛሬም አንዳይነት የድግግሞሽ ህይወት፣ ቅድምም አሁንም ተመሳሳይ አሰላቺ ሃሳብ ይኖራል። ከዚህ ሁሉ ድካም እርፍት አድርግ፤ ከድካሙ ሰውነትህ ይረፍ፣ ከሃሳቡ አዕምሮህ ይረፍ፣ ከዝለቱ ጡንቻዎችህ ይረፉ። በጣም ብዙ ደከምክ፣ ለፋህ፣ የማትወደውን ስራ ሌትተቀን ተጋህበት፣ በማይመች ሁኔታ ውስጥ ትልቁን ዋጋ ከፈልክ፣ ከሰዎች ተጋጨህ ነገር ግን ስሜት አጣህበት፣ ህይወትን አጣህበት፣ ትርፉ እንደጠበክው አይደለም፤ ይባሱንም ጉዳትና ህመም አተረፍክ። ስለእራስ ስሜትና ደህንነት ሳይጨነቁ የሚለፉ ሰዎች መጨረሻቸው አያምርም። ሁሉን አጥተህ ያመጣሀው ንብረት ምን ሊጠቅምህ ነው? ከቤተሰብህ ቀንሰህ ስራህ ላይ ያዋልከው ሰዓት ቦሃላ ኬት ሊመጣ ነው?

አዎ! ጀግናዬ..! ለተወሰነ ጊዜ አረፍ በል፤ ፋታ ውሰድ፤ እራስህን ለማረጋጋት ጊዜ ውሰድ፤ እራስህን ለመጠገን የተወሰነ ሰዓት መድብ። ባለማስተዋል ስትጣደፍ የሚያመልጡህን ውድ ስጦታዎች አስተውል። ጤናህ፣ ውስጣዊ ሰላምህ፣ እርካታህ፣ የህይወት ጠዓሟ፣ ቤተሰቦችህ፣ ዘመዶችህና ወገኖችህ ይታወሱህ። ከፍታው ላይ የምትደርሰው እራስህን እያጠፋህና ከባቢህን ረስተህ አይደለም። የህይወት ሩጫ ፋታ ባይሰጥም ዋጋ የማይወጣላቸውን በረከቶችህን ለመጎብኘትና ለመንከባከብ ግን ጊዜ አታጣም። በእጅህ ሳሉ የሚረክሱ ስታጣቸው ግን የሚወደዱ ስጦታዎች አሉ። ዛሬ ችላ ብለህ የምታጣው ጤንነት ነገ ያፈራሀውን ሁሉ ብታፈስበት ላይመለስ እንደሚችል አስታውስ። 

አዎ! ድካምም ምክንያት አለው፤ የእራሱ ትርጉም ይኖረዋል። ትርጉሙን በጊዜ ካላበጀህለት ከረፈደ ቦሃላ በእጅህ የነገበረውን ሁሉ ስታጣ ብታስታውሰው ምንም ዋጋ የለውም። በደጉ ጊዜ ንቃ፣ በመልካሙ ሰዓት እራስህን ጠግን፣ በብርታትህ ወቅት አካባቢህን አስታውስ። ድካም ለማንም አይቀርም፤ በእድሜ መዛል የሁሉም ፀጋ ነውና አንድ ቀን መምጣቱ አይቀርም። እርሱን ለማቆየትም ሆነ ሲመጣ ከቁጪት ለመዳን በጊዜው ለእራስ መድረስና እራስን መንከባከብ ተገቢ ነው። ቋሚ የእድሳት ጊዜ አስቀምጥ፤ ለብቻህ ዝም የምትልበትን ሰዓት አመቻች፤ ከእራስህ ጋር ለማውራት፣ ከአለም ለመለየትና ጥልቁን ስሜትህን ለመቃኘት አቅድ፤ ከህይወት ጡዘትም ለተወሰነ ጊዜ ፋታ ውሰድ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
3.3K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  01:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 04:12:21 ፈውሳችን በእርሱ ነው!

በተለት ተዕለት የህይወት መንገድ የሚወጣና የሚወርድ፣ የሚመጣና የሚሔድ፣ የሚያሳምምና የሚፈውስ የህይወት ገፅ አለ። በመኖር ውስጥ ጉራማይሌው ማንነት በገሃድ ይገለጣል፤ የማይታወቁ ባህሪያት ገሃድ ይወጣሉ፤ ያልተሰሙ ታሪኮች ይሰማሉ። እራስን በማዳመጥ ሂደት ከጊዜያዊው ህመም በላይ ዘላቂውና ፈዋሹ እራስን ማከም የተረጋጋውን ሰላማዊ ህይወት ያጎናፅፈናል። እራስን ማከም የሁላችንም ስጦታ ነው፤ እራሳችን ለእራሳችን ብቁ እንደሆንን የምናሳይበት ነው፤ በእኛ ውስጥ ፈውሳችን አምላክ እንደሆነ የማረጋገጥልን ነው። እራስን ማከም፣ እራስን መፈወስ (self-healing) የእራሱ መንገድ ቢኖረውም አንድ ሰው ያለማንም እርዳት ከደረሰበትና በጊዜው ካለበት ችግር መውጣት ከፈለገ እራሱ ላይ ያለውን ስልጣን ተጠቅሞ እራሱን በእራሱ እየጠገነና እየፈወሰ ነፃ መሆን የሚችልበት ሁነኛ መንገድ ነው።

አዎ! ጀግናዬ..! ፈውሳችን በእርሱ ነው፤ የምንድነው በአምላካችን ሃይል ነው፤ እንደ አዲስ የምንታደሰው፣ ከህመማችን የምንነፃው፣ ያለፈ ታሪካችንን የምንሽረው፣ ማንነታችን የምናሻሽለው፣ ስብዕናችንን ወደ ላቀው ደረጃ ከፍ የምናደርገው በፈጣሪያችን መልካም ስጦታና በእራሳችን ይሁንታ ነው። ያንተ አንገት ደፍቶ መሔድ ግድ የሚሰጠው ሰው ያለ ይመስልሃል? ያንተ በመከዳትና በመገፋት መሃል መሰቃየት የሚያስጨንቀው ሰው ያለ ይመስልሃል? ያንተ ከብዙሃኑ መንገድ ወጥቶ ለብቻ መጓዝ የሚያሳስበው ሰው ያለ ይመስልሃል? አይምሰልህ። ያንተ እራስህን በእራስህ ማከም፣ አገግሞ መምጣት፣ እራስን መዝኖ አስተካክሎ መመለስም ያንተ እንጂ የሌላ ሰው ጉዳይ አይደለም። በነፃ አለም ነፃ ፍቃድ አለህ፣ ፍፁም አባት ፍፁም አምላክ አለህ። እራስህን ለማዳን ስታስብ የምትተማመነውና የምትደገፈው ሰውን ሳይሆን ችሩ አምላክህን ነው።

አዎ! ሰው ለሰው ያስፈልጋል ነገር ግን አንዳንዴ ለእራስህ ምንያክል ብቁ እንደሆንክ ማየት ይኖርብሃል። ሰዎች በየደቂቃው በሚቀያየሩበት አለም እራስን በእራስ ለማከም መሞከር፣ " ከአምላኬ ቀጥሎ ለእራሴ እኔ አለው፣ እኔ ደርስለታለው " ማለት ወሳኙና አዋጩ መንገድ ነው። በአንተ ውስጥ ከሚመላለሰው አሉታዊና ጎጂ ስሜት ከእራስህ ውጪ ሌላ ነፃ የሚያወጣህ ምድራዊ ሃይል የለም። ጭንቀትህን ለፈጣሪህ የምትናገረው፣ ህመምህን ለሰዎች የምታማክረው፣ ያለፈ መጥፎ ታሪክህን የምትሽረውና በአዲስ ማንነትና መንገድ ተመልሰህ የምትመጣው አንተ ነህ። ነፃ መሆን ከፈለክ ነፃ የምትሆንበት መንገዶች አሉ። እራስህን በእራስህ ነፃ ከምታወጣው ነፃነት የተሻለ መንገድ ግን አታገኝም። በአንተ ውስጥ የሚሰራው አምላክህ ነው፤ ብርታትህ፣ ድጋፍህ፣ አለኝታህ፣ ጠባቂህ፣ ፈዋሽህ እርሱ ነው። በፈጣሪ ሃይል፣ ባንተ ፍቃድ እራስህን ፈውስ፣ ስብራትህንም ጠግን።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
3.2K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  01:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 05:05:44 ባያሳምንሽም ተቀበይው!

ፍቅርን የመረጠ ፣ አብሮነትን የፈለገ ፣ ረጅሙን የህይወት ጉዞ ካንተ ጋር ማሳለፍ የፈለገች ሴት ፣ ቀሪውን ዘመኑን ካንቺ ጋር መሆንን የመረጠ ወንድ የትኛውም ነገር ግንኙነቱን እንዲያቋርጥ አያደርገውም ። ብዙ ምክንያቶች ቢደረደሩም አንድ ጥሎሽ ሊሔድ ከፈለገ ሰው አሳማኝ ምክንያት አትጠብቂ ። " ችግሩን ለምን አውርተን አንፈታውም ? እንደዚህ እሆንልሃለሁ ፤ የፈለከውን አደርግልሃለሁ " እያልሽ ክብርሽን ማውረድ አይጠበቅብሽም ። አለመፈለገ በንግግር የሚፈታ ጉዳይ አይደለም ፤ ስሜት ማጣት በእንክብካቤና በመለመን የሚቀየር አይደለም ። ለማይፈልግ ሰው ትንሿ ነገር በቂው ነች ፤ ግንኙነቱን ከሚያዘልቀው ይልቅ የሚያቋርጥበትኝ ምክንያት መፈለግ የሁልጊዜ ስራው ነው ።

አዎ! ጀግኒት! ባያሳምንሽም ተቀበይው! ላንቺ ትርጉም ባይሰጥ ፣ ባይመስልሽም እርሱ እስካመነበትና አብሮነቱን ለማፍረስ በቂ ነው ብሎ እስካመነ ልታስገድጂው አትሞክሪ ። ማንም ሰው መለያየትን ሲመርጥ ቃል አውጥቶ አልፈልግሽም ወይም አልፈልግህም ፣ የኔና ያንቺ ወይም ያኔና ያንተ ጉዳይ አብቅቷል የማለት ግዴታ የለበትም ። ሁሌም ከቃሉ በላይ ተግባሩ በሚገባ ይናገራል ፤ ለማየት ባንፈልግም በተሻለ አገላለፅ አሳማኙን ምክንያት በግልፅ አቅርቦልናል ። ትንሹን እያገዘፈ ፣ ክፍተት በተፈጠረ ቁጥር በመለያየት እያስፈራራ ፣ ሁሌም ጥፋተኛ እያደረገሽ ፣ ለእራሱ ጥፋትም አንቺን እየወቀሰ ፣ በሆነ ባልሆነው እየሔደ የሚመጣን ሰው ከቻልሽ በቅርበት ለማወቅ ሞክሪ ካልሆነም እራስሽ ጠብቂ ። ፍቅርን በምርጫ እንጂ በግዴታ መገንባት አይቻልም ።

አዎ! ጀግናዬ..! ሁሌም አብሮ ለመሆን ፣ በፍቅር፣ በመዋደድ ፣ በመተሳሰብ ፣ በመረዳዳት አብሮ ለመቆየት ብዙ ምክንያቶች ይኖራሉ ። እርሱን ለማይፈልግ ደግሞ ለመለያየት እጅግ ብዙ ምክንያቶች አሉለት ። ካንተ ለመለየት ምክንያቶችን መደርደር ስትጀምር ፣ ከእኔ የተሻለ ሰው ይገባሃል ስትልህ ፣ ቤተሰብ፣ ወገን ፣ ዘመድ ግንኙነታችንን አልወደደው ስትልህ ዝም ብለህ እመናት ። ምክንያቶች ከጀርባቸው ፍላጎት የማጣትን ስሜት ይዘው እንደሚመጡ አስተውል ። አንተ በማፍቀርህ ብዙ ነገር ለመሰዋት ዝግጁ በሆንክበት ሰዓት የእርሷ በዛው ልክ አለመምጣትና ሌሎች ነገሮችን ማስቀደም ቢያሳምምህም አምኖ መቀበሉ ግን ይጠቅምሃልና ተቀበለው ። ሌላ አሳማኝ ምክንያት በመጠበቅ የህመም ጊዜህን አታራዝም ። ከሚደረድርልህ ምክንያት በላይ ከጀርባው ያለውን ፍላጎት ማጣት ጠንቅቀህ ተረዳ ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
725 viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  02:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ