የሰው ልጅ በምድር ላይ ሲኖር ለሦስት ነገሮች መዘጋጀት ይኖርበታል ።
ለኃላፊነት ፣
ለዕውቀትና
ለትዳር ።
ሦስት ነገሮችንም ማክበር አለበት ።
ቃል-ኪዳኑን ፣
ትዳሩንና
ቤተሰቡን ።
ከሰው ጋር ሊያጣሉ የሚችሉ ሦስት ነገሮችን ደግሞ መቆጣጠር ይኖርበታል ።
ምላሱን ፣
ቁጣውንና
ስሜቱን ።
እንደገና ሦስት ነገሮችን መፀየፍ ይኖርበታል ።
ሀሜትን ፣
ተንኮልና
ቅናትን ።
በመጨረሻም ለአንድ ሰው ሦስት መሠረታዊ ነገሮች ያስፈልጉታል ብዬ አምናለሁ ።
እምነት ፣
ተስፋና
ፍቅር!
መልካም ቀን ይሁንላችሁ