2021-02-09 10:16:29
ለ 2 ዓመት ደም የሚፈሳት፣ ከማሕፀንዋ እና ከአፍዋ መጥፎ ጠረን የሚሸትባት እህት ለእመቤታችን ደብዳቤ ጽፉ ተፈውሳ የሰጠችው ምስክርነት!
ሼር በማድረግ ተአምሯን ለወዳጆ አዳርሱ!
የወለላይቱ እመቤት ልጆች ወጣቷ እንጦጦ ማርያም ሳትመጣ ችግሯን በደብዳቤ ጽፉ "እንጦጦ ማርያም ወስዳችሁ ስዕሏ ስራ አስቀምጡልኝ" ብላ እመቤታችን እምነቷን ተመልክታ ከደም መፍሰስ እና ከማሕፀን፣ ከአፍ መጥፎ ጠረን ባለችበት ፈውሳታለች።
መቼም እንጦጦ ማርያም ላይ ወለላይቱን እመቤትን ለመጀመሪያ ጊዜ በደብዳቤ የተማጸኗት ደገኛይቱ እቴጌ ጣይቱ ናቸው። እንጦጦ ማርያም ቤተ ክርስትያኗ ተሠርታ የተመረቀች ዕለት የምርቃት ሥነ-ስርዓቱንና ድግሱን ሊያስተጓጉል የሚችል ከፍተኛ ደመና ያዘለ ሰማዩን ያጠቆረ ዝናብ መጥቶ ነበር።
አፄ ምኒሊክ፣ እቴጌ ጣይቱ፣ መኳንንቱ፣ መሳፍንቱ፣ ካህናቱና ሕዝቡ ሲጨነቁ እቴጌ ጣይቱ ለእመቤታችን ደብዳቤ ጽፈው በደብዳቤውም እመቤታችን በተአምራቷ ዝናቡን እንድታሳልፈው ተማጽነው ቤተ መቅደስ አስገብተው ከታቦቷ አጠገብ እንዲያስቀምጡት ለካህናት ሰጥተው ካህናቱም የእቴጌይቱን ጽኑ እምነት አይቱው እንደተባሉት ቢያደርጉ ዝናብ ያዘለ፣ ውኃ ያጋተው ሰማይ ጋቢውን እንደተገፈፈ አባ ወራ እመቤታችን በአስደናቂ ተአምር ዝናብ ያዘለውን ደመና ገፋ፣ ለሕዝቡ ፀሐይን አንጥፉ ብራ አድርጋላቸው በዓሉንና ዝግጅቱን በሰላም አሳልፈዋል።
ወዳጆቼ የእንጦጦ ማርያም የክብር ስሟ "መንበረ ፀሐይ" ነው። ስለዚህ የትም ሆናችሁ ብትማጸኗት እንደ ፀሐይ ታበራላችኃለች።
ስለዚህ ለዚህችም ወጣት እንደ እቴጌ ጣይቱ በደብዳቤ ስለሰማቻት ሊደንቀን አይገባም። ምክንያቱም ጌታችን "ለሚያምን ሁሉ ይቻላል" ብላሏልና። ማር 9፥23
3.6K views07:16