Get Mystery Box with random crypto!

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የሰርጥ አድራሻ: @memehirhenok
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 12.40K

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 29

2022-10-06 21:24:09 #_የንስሐ_እና_የቄደር_ጥምቀት_ጥሪ!

#_እሑድ_መስከረም_29_ጠዋት_2_ሰዓት

#_በወይን_አምባ_ቅድስት_ማርያም_ቤተ_ክርስትያን!

"ጥሩ ውኃንም እረጭባችኃለሁ እናንተም ትጠራላችሁ" ሕዝቅ 36፥25

"የትኛውንም ኃጢአት ብንሠራ ሁሉም ኃጢአተቶች ከንስሐ በታች ናቸው። ከንስሐ በላይ የሆነ ኃጢአት የለም። የእኛ ኃጢአት ከእግዚአብሔር ቸርነት በላይ አይደለም"

#_ቄደር_ለመጠመቅ_የሚያበቁን_ኃጢአቶች_የትኞቹ_ናቸው?

#_ቄደር_ለምን_እንጠመቃለን?

#_ቄደር_በመጠመቃችን_ምን_ጥቅም_እናገኛለን?

የነፍስ ጉዳይ ነውና ሳትቸኩሉ በደንብ አንብቡት!

"የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት ለጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና።" 1ኛ ጴጥ 4፥3

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

#_ሼር_በማድረግ_የነፍስ_ግዴታዎትን_ይወጡ!

ተወዳጆች ሆይ እሑድ መስከረም 29 ጠዋት 2 ሰዓት በወይን አምባ ማርያም ቤተ ክርስትያን የቄደር ጥምቀት እና ንስሐ የመስጠት አገልግሎት ስላለ መጥታችሁ ንስሐ ግቡ ቄደር ተጠመቁ። እባካችሁ ሰዓቱን ጠብቃችሁ ኑ። በተቻለ መጠን ደጇ ሁለት ሰዓት ድረሱ!

የጸሎት መርሃ ግብሩ ካለቀ በኃላ ብትጠመቁ ዋጋ የለውም። ምክንያቱም ለምሳሌ የጸሎቱ መርሃ ግብር ላይ አቡነ ዘበሰማያት 41 ጊዜ ካርያላይሶን 41 ጊዜ እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ ወዘተ እንድትጸልዩ ስለሚሰጣችሁ እነዚህን ጸሎቶች ሳትካፈሉ ሰዓት አርፍዳችሁ ብትመጡ መጠመቅ አይቻልም። ስለዚህ የነፍስ ጉዳይ ነውና ሰዓት ይከበር።

#_ቄደር_ለመጠመቅ_የሚያበቁን_ኃጢአቶች_የትኞቹ_ናቸው?

ቀደር ለመጠመቅ የሚያበቁን ኃጢአቶች ለምሳሌ ረቡዕ ብና አርብ የፍስክ ከበላን፣ ውርጃ ከፈጸምን፣ ከሃይማኖታችን ውጪ ካሉ ሰዎች ጋር ሩካቤ ሥጋ ከፈጸምን፣ በልጅነት እና ካደግን በኃላ ግብረ ሰዶም ከፈጸምን፣ ከእንስሳት ጋር ግንኙነት ካደረግን፣ በልጅነት መሬትን ካወሰብን፣

ከሥጋ ዘመድ ጋር ግንኙነት ከፈጸምን፣ ቅዱስ ቁርባን ተቀብለን በዝሙት ከወደቅን፣ በቅዱስ ቁርባን አግብተን ባል በሚስት ላይ ሚስት በባል ላይ ከዘሞተች፣ ኢ- ሩካቤ ከፈጸምን ማለት ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ ግንኙነቶችን ከፈጸምን፣ የአሕዛብን ምግብ ከበላን፣ ኦርቶዶክስ ሆነን ወደ ሌላ እምነት ገብተን ከተመለስን፣

ለዛር ለጨሌ ለአቴቴ ከገበርን፣ የተገበረውን መስዋዕት ከበላን፣ ጠንቋይ ቤት ከሄድን፣ ዛር አንጋሽ ጋር ከሄድን፣ ግለ ወሲብን ከፈጸምን፣ ሴት የወር አበባዋን ሳትጨርስ ግንኙነት ካደረገች፣ ወንድም የወር አበባ ካልጨረሰች ሴት ጋር ግንኙነት ካደረገ፣ ጫት ሲጋራ ከተጠቀምን ወዘተ ቄደር የግድ መጠመቅ አለብን።

ወዳጆቼ ልብስ በሳሙና ይታጠባል በመጨረሻ በኦሞ ተዘፍዝፎ ይለቀለቃል። በዚህም ጸዐዳ ይመስላል። ንስሐ ኃጢአታችንን የምናጥብበት ሳሙና ነው። ቄደር ደግሞ ኦሞ ነው ያነጻናል።

በተለይ ንስሐ ገብታችሁ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ያሰባችሁ ቄደር ተጠምቃችሁ ብትቀበሉ መልካም ነው። በንስሐ ያላካተትነው ኃጢአት በቄደር ይነጻልና። እንዲሁም በቄደር ነጽተን ቅዱስ ቁርባን ብንቀበል ይሰምርልናል።

ሌላው ንስሐ ለመግባት አስባችሁ የንስሐ እድሉን ያላገኛችሁ እና ንስሐ አባት የሌላችሁ እሑድ መስከረም 29 ቀን ጠዋት 2 ሰዓት መጥታች በደብሩ ካህናት ንስሐ መግባት ትችላላችሁ።

የእናንተን ችግር የሚረዱ በተለይ ለካህናት መናገር የምትጨነቁበትንና የምታፍሩበትን ለምሳሌ ግለ ወሲብንና የወሲብ ፊልምን የተመለከቱ ወዘተ ዘመን አመጣሽ ኃጢአትን የሚረዱ ካህናትን ስላዘጋጀን መጥታችሁ በነፃ ንስሐ ግቡ፣ የኃጢአት ሸክምን በእናታችሁ ቤት አራግፉ።

የወለላይቱ እመቤት ልጆች የትኛውንም ኃጢአት ብንሠራ ሁሉም ኃጢአተቶች ከንስሐ በታች ናቸው። ከንስሐ በላይ የሆነ ኃጢአት የለም። የእኛ ኃጢአት ከእግዚአብሔር ቸርነት በላይ አይደለም።

የእኛ ኃጢአት የደም ጠብታ ነው። የእግዚአብሔር ቸርነት ደግሞ ውቅያኖስ ነው። ስለዚህ የደም ጠብታ የውቅያኖስን ውሃ እንደማያደፈርስ ሁሉ የትኛውም የእኛ ኃጢአት የእግዚአብሔርን ቸርነት አይበልጥም። ንስሐ ግቡ ቄደር ተጠመቁ።

ስለዚህ እሑድ መስከረም 29 ቀን ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ወይን አምባ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን ኑ። ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ጸሎቱ ይጀመራል መጥታችሁ ተጠመቁ።

#_የትራንስፖርት_መምጫው ፦

ከየትኛውም አቅጣጫ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፣ ሠፈራ ብላችሁ በባጃጃ ተሳፍራችሁ፣ ድልድዩን እንደተሻገራችሁ አስፓልቱ ጫፍ ላይ ቤተ ክርስትያኗ ትገኛለች።

ከመገናኛ ቀጥታ ወይን አምባ ማርያም የሚል ታክሲ አለ ቤተ ኮርስቲያኑ በር ላይ ያወርዷቹኃል።

ከመገናኛ በቀጥታ ጎሮ ብለው ተሳፍረው፣ ጎሮ አደባባይ ወርደው፣ ከዚያ ባጃጅ ተሳፍረው፣ ሠፈራ ድልድይ ጫፍ ላይ ስትወርዱ ትገኛለች፡፡

ከሲ አምሲ፣ ከአያት፣ ከሰሚት የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርደው፣ ባጃጅ ተሳፍረው ሠፈራ ድልድይ ጫፍ ወርደው ትገኛለች፡፡

ከቃሊቲ፣ ከቱሉ፣ ዲምቱ፣ ከኮዬ ፈጩ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርደው ከዚያ በባጃጅ ተሳፍረው ሠፈራ ድልድይ ወርደው ጫፍ ላይ ትገኛለች፡፡

ሐሙስ መስከረም 26-1-15 ዓ.ም
አዲስ አበባ
4.3K viewsedited  18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 20:22:46

2.4K views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 08:17:28
101 views05:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 08:17:19 እመቤታችን እኛን ሀገራችንን ብትወድ አስራት አድርጋ ተቀበለችን፡፡ እኛ ግን ለእሷ እንደ ቅዱስ ደቅስዮስ መሆን አቃተን፡፡ የፍቃድ ነው እየልን ከመሳነፍ ጾመን ጸጋ ብናተርፍ ይሻለናል፡፡ የማህሌተ ጽጌ ደራሲዎች አባ ጽጌ ድንግል እና አቡነ ገብረ ማርያም ከዚህ ዓለም ድካም እስካረፉበት ዘመን ዘመናቸውን በየአመቱ ጾመ ጽጌ ይጾሙ ነበር። በዚህም ከእመቤታችን ዘንድ ብዙ ጸጋና በረከት አግኝተዋል፣ በእሷም ዘንድ እጅግ ተወዳጅነትን አትርፈዋል።

ቅዱስ ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮንቶስ 6፥12-13 ላይ ‹‹መብል ለሆድ ነው ሆድም ለመብል ነው እግዚአብሔር ግን ይህንንም ያንንም ያጠፋቸዋል›› ብሎናል፡፡ ስለዚህ የጤና ችግር የሌለብን ሰዎች ፅጌ ጾምን ብንጾም ከወለላይቱ እመቤት ከስደት በረከት እንካፈላለን፡፡ ችግራችንን እናስፈታለን በእሷም ዘንድ ልዩ መወደድን እንደ አባቶቻችን እናተርፋለን፡፡

እመቤታችን ሀገራችን መጥታ እኛንም ሀገራችንንም ባርካ የስደቷ መታሰቢያ ተደርጎ የተሰጠንን ፅጌ ጾምን ጾመን ለሀገራችን ለቅድስት ቤተ ክርስትያናችን ለሕዝባችን ሰላም የሚወርድበት እኛም አንድ የምንሆንበት ወለላይቱ እመቤት ታድርግልን።

በተለይ ሀገራችን በአሁኑ ጊዜ ከገጠማት ችግር እንድትላቀቅ፣ እመቤታችን እኛንም ከልጅዋ እንድታስታርቅ፣ ጦርነቱ፣ በሽታው፣ ከሀገራችን እንዲርቅ፣ አንድ ሆነን የምንጾምበት የምንጸልይበት ጊዜው አሁን ነው፡፡ ለሁላችሁም በያላችሁበት መልካም ጾመ ፅጌ ይሁንላችሁ!

መስከረም 26/1/15 ዓ.ም

አዲስ አበባ
104 views05:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 08:17:19 እመቤታችን ለእኛ እንደምትሆንልን ቢሆኖ ኖሮ ፅጌ ጾምን የተሰደዱትን የሚያረጋጋ ልጅዋን ይዛ መሰደድዋን፣ የተራቡትን የሚመግብ ልጅዋን ይዛ መራብዋን፣ የተጠሙትን የሚያጠጣ ልጇን ይዛ መጠማትዋን፣ በአጠቃላይ የእመቤታችንን እንግልት አስበን በጾምን ነበር፡፡ ፅጌ ጾምን በአግባቡ ብንጾም በጾማችንም ለወለላይቱ እመቤት ፍቅራችንን ብንገልጽላት ከስደትዋ በረከት ተሳታፊ በሆንን ነበር፡፡ እሷም የበለጠ ፍቅሯን ጸጋዋን ባሳደረችብን ነበር፡፡

የወለላይቱ እመቤት ልጆች እውነት እንነጋገር ከተባለ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት የአዋጅ ጾም ነው፡፡ ጾመ ነነዌን የምንጾመው የታላቅዋ የነነዌ ሕዝብ ጾመው የእግዚአብሔር መቅሰፍት ስለራቀላቸው እኛም እንደ እነሱ የእግዚአብሔር ቁጣ እንዲርቅልን እንጾማለን፡፡ እነሱ በዳኑት እኛም እንድንድን እነሱን እያሰብን አብነት አድርገን እንጾማለን፡፡

ዛሬ ነነዌ የቀድሞ ስሟንና ሃይማኖትዋን ይዛ የምትገኝ አገር አይደለችም በድሮ ታሪኳ እናስባታለን እንጂ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታ የወንጌል አገልግሎታቸውን እንዲባርክላቸው ስለጾሙ እኛም እነሱን አብነት አድርገን ሰኔ ጾምን እጾማለን፡፡ ደስም ይላል እጅግም መልካም ነው ቀኖናም ነው፡፡

ግን ለነነዌ ሕዝብ ከተደረገላቸው ነገር ለእኛ በወለላይቱ እመቤት በኩል የተደረገልን የመዳናችን ምስጢር እና ውለታ አይበልጥም? በተለይ ለእኛ ለኢትዮጲያውያን፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን ሰጡን ወለላይቱ እመቤት ደግሞ የወንጌሉን ባለቤት ጌታን ወልዳ ሰጠችን፡፡ ዛሬ ታሪካቸው እንጂ ውለታቸውን የማናውቀውን የነነዌ ሕዝብን ጾም እዚህ አምጥተን በአዋጅ እየጾምን የእናታችንን የእመቤታችንን የስደትዋ መታሰብያ የሆነውን ፅጌ ጾምን አለመጾማችን ትዝብት አይሆንም?

እባካችሁ የወንጌል መምህራን ‹‹ፅጌ ጾም የአዋጅ ጾም አይደለም እያላችሁ›› ቀለል አድርጋችሁ ምዕመናኑን ከወለላይቱ እመቤት በረከት እና ጸጋ አታርቁ፡፡ እናንተ ባትጾሙ እንኳን የፅጌ ጾምን ጥቅም እና በረከት ንገሯቸው አስተምሯቸው፡፡ ስለ ፍቅሯ እና ስለ ስደቷ መታሰብያ የሚጾሙ ብዙ አሉ፡፡ ግን ብዙዎቹ የፅጌ ጾምን ጥቅም እና የሚያሰጠውን በረከት ስለማያውቁ አይጾሙም፡፡

ምስጢረ ሥጋዌ ምስጢረ ቁርባን ስንል በእነዚ ድንቅ ምስጢራት ወለላይቱ እመቤት በዋጋ የማይተመን ሚና አላት፡፡ ለሰው ልጆችም የድህነት ምክንያት ናት፡፡ ይህን ውለታዋን ያወቁ አባቶቻችን ፅጌ ጾምን በሱባኤ ሲጠቀሙበት እኛ ደግሞ ስንት ችግር እና መከራ ተሸክመን በመብላት እናሳልፋለን፡፡ እንዲህ ላለነው ቅዱስ ጳውሎስ በፊልጵስዮስ መልእክቱ 3፥19 ላይ ‹‹ሆዳቸው አምላካቸው ነው፣ ክብራቸው ነውራቸው ነው፣ አሳባቸው ምድራዊ ነው›› እያለ ይወቅሰናል፡፡

እስከ መቼ ሆዳችን አምላካችን ይሆናል? እስከ መቼ ክብራችንን ነውር አድርገን እናስባለን? እስከ መቼ ሐሳባችን ሰማያዊ ሳይሆን ምድራዊ ብቻ ይሆናል? የወለላይቱ እመቤት ልጆች በተአምረ ማርያም ላይ እንደሰማነው በፍጹም ልቡና በፍጹም ሐሳቡ ወለላይቱ እመቤትን ይወዳት የነበረው ኤጲስ ቆጶሱ ቅዱስ ደቅስዮስ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችንን ባበሰራት ቀን በዓሏን እንዳከበረና የልደትን በዓል ከማክበር አስቀድሞ 8 ቀን እንደ ጾመና ታህሳስ ሃያ ሁለትን ስለ ፍቅሯ እንዳከበረ ይነግረናል፡፡

ቅዱስ ደቅስዮስ የጾመው ከሰባቱ አጽዋማት ውስጥ የለም የአዋጅም አይደለም፡፡ ግን ቅዱስ ደቅስዮስ ስለ እመቤታችን ፍቅር ብሎ ጾመ ታድያ ምን አገኘ? ካልን የደቅስዮስን የፍቅር ጾም የወደደችለት ወለላይቱ እመቤት በእጅዋ የከበረ ልብስ ይዛ ተገለጸችለት፡፡ ‹‹በእውነት አገልጋዬ ወዳጄ ደቅስዮስ ሆይ እኔ አመሰግንሃለሁ በአንተም ደስ አለኝ፡፡ ሥራህንም ወደድሁ›› አለቸው፡፡

ወዳጆቼ ወለላይቱ እመቤት በስቶቻችን ተደስታ ይሆን? የስንቶቻችንን ሥራ ወዳልን ይሆን? ስንቶቻችን በእሷ ዘንድ መወደድን አትርፈን ይሆን? እመቤታችን ለቅዱስ ደቅስዮስ ‹‹በእኔ ደስ እንዳለህ ገብርኤል የሚባል መልአክ ባበሰረበት ቀን በዓሌን አክብረሃልና ስለ እኔ ሰውን ሁሉ ደስ አሰኝተሃልና እኔም ዋጋህን ልሰጥህ እወዳለሁ፡፡

አንተም በዚህ ዓለም በሰው ፊት እንዳከበርከኝ አከብር ዘንድ እወዳለሁ፡፡ እሷን ትለብስ ዘንድ ይህችን ልብስ እነሆ አመጣሁልህ፡፡ በላዩም ትቀመጥባት ዘንድ ይህንን ወንበር አመጣሁልህ፡፡ ከሰው ወገን አንድስ እንኳ ይህችን ልብስ ሊለብሳት በዚህችም ወንበር ላይ ሊቀመጥባት አይችልም፡፡ ነገሬን ያፈረሰ እሱን አጠፋዋለሁ›› ብላ ሰጥታው ከእሱ ተሰወረች፡፡

ቅዱስ ደቅስዮስ ስምንት ቀን ስለ ፍቅሯ ማንም ያልጾመውን ጾም ጾሞ ለሰው ያልተሰጠ ጸጋ ከእሷ አገኘ፡፡ እኛስ ታላቁን የስደትዋን ጾም ብንጾም ምን እናገኝ ይሆን? እንዴትስ አመስግናን ይሆን? እንዴትስ ደስ ተሰኝታብን ይሆን? በሰው ፊት ጾምዋን ‹‹የፍቃድ ነው›› እያልን ከምናቃልል ለሌሎችም እንዳይጾሙ የስንፍና ምክንያት ሳንሆን አክብረን ብንጾም ወለላይቱ እመቤት እንደ ቅዱስ ደቅስዮስ ባከበረችን ነበር፡፡

ቅዱስ ደቅስዮስ በጾሙ ያገኘውን የክብር ልብስና የክብር ወንበር ከእሱ ውጪ ለሚቀመጥበት እና ለሚነካው ሰው መከራ እንደሚመጣበት ተነግሮታል፡፡ እኛም የፅጌ ጾምን ስለ ፍቅሯ በመጾማችን የስንፍና ቃል ለሚናገሩን መከራ ይገጥማቸዋል፡፡ ከዚህ በኃላ አባታችን ቅዱስ ደቅስዮስ የዚህ ዓለም አኗኗሩን በተጋድሎ ካበቃ በኃላ ወለላይቱ እመቤት ነፍሱን አቅፋ ከእሷ ጋር በተድላ ገነት አኑራዋለች፡፡

ከቅዱስ ደቅስዮስ በኃላ የተሸመው ኤጲስ ቆጶስ እሱ ሳይጾም ሳይለፋ ሳይደክም በድፍረት የቅዱስ ደቅስዮስን ‹‹ልብስና ወንበሩን አምጡልኝ እኔም ሰው እሱም ሰው›› ብሎ አስመጥቶ በድፍረት ቢቀመጥበት ተቀስፎ ሞቷል፡፡ ኤጶስ ቆጶሱ እንደ አሁኑቹ እንደ እኛ ጾምን የማይሻ ግን በአፍ ብቻ አውርቶ ጸጋን ማግኘት ስለወደደ ሞተ፡፡ ጸጋ ደግሞ እንዲሁ አይገኝም፡፡ ክብር በከንፈር አይገኝም፡፡

ወዳጆቼ እኛም በፅጌ ጾም ከምንከራከር ‹‹የፈቃድ ነው›› እያለን ሰንፈን ሰውን ከምናሳንፍ ብንጾም ኖሮ፣ ቅዱስ ደቅስዮስ የሆነላትን ብንሆንላት ኖሮ፣ እመብርሃን እንደ ቅዱስ ደቅስዮስ ስንት ክብር እና ጸጋ ባሰጠችን በሰጠችን ነበር፡፡

ውድ የወለላይቱ እመቤት ልጆች የቅዱስ ደቅስዮስ የስምንት ቀን የፈቃድ ጾም ምን ያህል ክብር እንዳሰጠው አያችሁ? እኛማ የስደትዋ መታሰብያ የሆነውን ፅጌ ጾምን አርባ ቀን ብንጾመውማ ምን እናገኝ ይሆን? የሚፈትነን እድላችንንና ሕይወታችንን የነጠቀን ዓይነ ጥላው መተት ድግምቱ የቤተሰባችን ዛር እና ሌሎችም ክፉ መናፍስት በራቁን የተቋጠረብን በእሷ ጸሎት በተፈታልን ነበር፡፡

ግን እዚህ ላይ አንድ ነጥብ ያዙልኝ፣ እንዲህ ስል ፅጌ ጾምን በግሌ የአዋጅ ይሁን እያልኩ ሳይሆን የወዳጅ ይሁን ነው፡፡ ምክንያቱም ብንጾመው እጅጉን ተጠቃሚና አትራፊዎች ነንና፡፡ መከራ ወደ ምድር የመጣው በጾም ሳይሆን በመብል ነው፡፡ ወፎች የሚያዛቸው ወጥመዱ ሳይሆን ሆዳቸው ነው፡፡ ሊበሉ ሲሄዱ ነው በወጥመድ የሚያዙት፡፡ የቻልን በርትተን ብንጾም ብሎም ሱባኤ ገብተን ብንጠይቃት መልስ አናጣም፡፡

አንዳንድ ሰነፎች ‹‹ፅጌ ጾምን ያልጾመ ችግር የለውም፡፡ በመጾሙም አይጸድቅም ባለ መጾሙ አይኮነንም›› ይላሉ፡፡ በእርግጥ ልክ ነው፡፡ ግን በወለላይቱ እመቤት የፍቅር ሚዛን ላይ ተመዝኖ እንደ ገለባ መቅለል እንዳለ መርሳት የለብንም፡፡
80 views05:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 08:17:19 #_የፍቃድ_ጾም_ነው_እያልን_ያልተጠቀምንበት_ታላቁ_የጽጌ_ጾም!

#_ጾሙን_በመጾማችን_ምን_አይነት_ጸጋ_እና_በረከት_እናገኛለን?

/ቪዲዮውን ለማየት ያልተቻላችሁ ይኸው በጽሑፍ ቀርቦላቹኃል!/

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ለእመቤታችን ልጆች አዳርሱ!

የወለላይቱ እመቤት ልጆች በቅድሚያ እንኳን ለእናታችን ለወለላይቱ እመቤት የስደቷ መታሰብያ ለሆነው ጾመ ፅጌ አደረሳችሁ፡፡ ፅጌ ጾም የምንለው በአጭሩ የእመቤታችንን የስደቷን ጊዜ የምናስብብት ጾም ነው፡፡ ይህም ከመስከረም 26 እስከ ህዳር 6 ቀን ያለው ነው፡፡

በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ሕግና ሥርዓት መሠረት ከመስከረም 26 ቀን እስከ ሕዳር 6 ቀን ያለው 40 ቀን የወለላይቱን እመቤት እና የተወዳጅ ልጇን ስደት በማሰብ ዘመነ ፅጌን ወይም ወርኃ ፅጌን ታስባለች ታከብራለች፡፡

ይህ 40 ቀን የእመቤታችን እና የልጇ ስደት የሚታሰብበት ዘመን ነው፡፡ እንደሚታወቀው ወቅቱ የአበባና የፍሬ ስለሆነ እመቤታችን በአበባ ጌታችን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምላክነቱ እሷ በአምላክ እናትነቷ በተለያዩ ምስጋናና ጥዑም ዜና ይመሰገናሉ፡፡

ስደት ሲነሳ ሐዋርያት በወንጌል የተነሳ ተሰደዋል ሞተዋል፡፡ ቅዱሳን ስለ ክርስቶስ ፍቅር በየገዳሙ ተሰደዋል፡፡ እነዚህና ሌሎችም ስለ ስሙና በስሙ ምክንያት ሲሰደዱ የእመቤታችን ስደት ግን ልዩ ነው፡፡

የወለላይቱ እመቤት ልጆች እመቤታችን ልጅዋን ቅዱስ አማኑኤልን ይዛ ነው የተሰደደችው፡፡ ቅዱሳን በአምላካቸው ስም ሲሰደዱ እመቤታችን ደግሞ አምላክን ይዛ ተሰዳለች፡፡

እመቤታችን የተሰደደችው ምድራዊ ንጉስ ሄሮድስን ፈርታ ሸሽታ አይደለም፡፡ እሷማ ይዛው የተሰደደችው ሄሮድስን በዓይኑ እይታ ብቻ ከምድረ ገጽ የሚደመስሰውን አልፋና ኦሜጋ ኢየሱስ ክርስቶስን ይዛው ነው፡፡ ደግሞም እናውቃለን በየሐዋርያት ሥራ በምዕራፍ 5 ቁጥር 1-10 ላይ ልጅዋ ሐናንያና ሰጲራን ሳይመታ የጣለ እና የገደለ ነው፡፡

ስድት የማይገባት የእኛ እናት ወለላይቱ እመቤት የእኛን የኃጢአተኞችን ፈንታ ነው የተሰደደችው፡፡ እመቤታችን በመሰደድዋ ከገነት እንድንሰደድ ያደረገን ሰይጣንን አሳዳዋለች፡፡ በስደትዋ ወቅት በቀላሉ የማይነገር ከሕሊና በላይና ልብ ሰባሪ መከራ ተቀብላለች፡፡ በዚህም ስደትን ተሰዳ ባርካ ሰጥታናለች፡፡

በተለይ በውጭ አገር ያላችሁ ወንድም እህቶቼ በስደታችሁ መከራ ሲገጥማችሁ ስደትን ከእናንተ በበለጠ የእግር ጥፍራ እስኪነቀል ሀገር ለሀገር የተሰደደችውን እመቤታችንን እያስታወሳችሁ ተጽናኑ በነገሮች ሁሉ እንድትረዳችሁ ተማጸኗት፡፡

የወለላይቱ እመቤት ልጆች አሁን ስለ ስደት ለማውራት ሳይሆን በስደትዋ ምክንያት ታስቦ ስለሚጾመው ስለ ፅጌ ጾም ነው፡፡ በመሠረቱ ጾም ጾም ሲባል መጾሙ ላይ እንጨቃጨቃለን መብላቱ ላይ ግን እንስማማለን፡፡ ይህ የሚሆነው ለነፍሳችን ሳይሆን ለሥጋችን ስለምናደላ ነው፡፡

ለስንት ዘመን ስንበላ የከረምነው ዓሳ ‹‹ይበላል አይበላም›› እያልን የምንጨቃጨቀው የመጾም ሳይሆን የመብላት ፍላጎታችንን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ ለዚህም ነው የዓሳ ጉዳይ ሐሳብ ሆኖብን ጎራ በመለየት በመብላት የተጠመድነው፡፡

ወዳጆቼ ይህ ችግራችን ገፍቶ በገና ጾም ቅበላ ላይ ገና ጾም የሚገባው ‹‹ህዳር 14 ነው አይደለም ህዳር 15 ቀን ነው የሚገባው›› እያልን የምንወዛገበው አንዱ የመብላት ፍላጎታችን ማሳያችን ነው፡፡ ብቻ ጾም ሲነሳ ጻር የሚሆንብን ሥጋን ለመብላት ካለን ሥጋዊ ፍቅር እንጂ ሌላ አይደለም፡፡

እውቀትና ጥበብ እንጂ ሃይማኖት የሌላቸው የሰለጠኑት ምዕራባውያን እና ሌሎች ሀገራት ሥጋ ለሥጋችሁ ስጋት ነው ያስረጃል ጤና ይነሳል እያሉ በሚዲያ እያስተማሩ ብሎም እያስጠነቀቁ ሕዝባቸውን አትክልት ተመጋቢ ሲያደርጉት እኛ በሃይማኖት የምንኖረው ጠንካራ ጿሚ መሆን አቃተን፡፡

አዳም እና ሔዋን በገነት ሲኖሩ ይመገቡት የነበረው ሥጋ ሳይሆን አትክልት እና ፍራፍሬ ነው፡፡ በየትኛውም መጽሐፍ በገነት ሥጋ በሉ የሚል ተጽፎ አናገኝም፡፡ ይልቁንም ከገነት ከተባረሩና ወደዚህ ምድር ከወደቁ በኃላ ነው ሥጋን የበሉት፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሥጋ ከበደል በኃላ የመጣ የሰው ልጆች ምግብ ሆነ፡፡

አንዳንዶቻችን መምህራን ስናስተምር ‹‹የጾም ጥቅሙ፣ ሥጋን ለነፍስ ለማስገዛት እንጂ ለሌላ አይደለም፡፡ ሥጋህን ከገዛህ በጥቂቱ ጾመህ ብትበላ ችግር የለውም›› እያልን የራሳችንን የጾም ድክመት ለሰዎች እያሳየን በጾም ሕይወት እንዳይጠነክሩ እናደርጋለን፡፡

አባቶቻችንና እናቶቻችን በየገዳሙ ከሚገባቸውና ከመጠን በላይ የሚጾሙት ሥጋቸውን ለነፍሳቸው ማስገዛት አቅቷቸው ሳይሆን ጾም ወደ ብቃት ደረጃ ከሚያደርሳቸው መንገድ አንዱ መሆኑን ስለሚያውቁና ስለተጠቀሙበት ነው፡፡

አባቶቻችን ከጾም ትጋታቸው የተነሳ በመጨረሻ ከተፈጥሮ ሕግ በላይ በመሆን እህል እስከ አለመብላት ውኃ እስካለመጠጣት ደረጃ ይደርሳሉ፡፡ በጾም ትጋታቸው ድካማቸው ተቆጥሮላቸው ከመልአክ እጅ ሰማያዊ ሕብስትና ጽዋ እየተቀበሉ እስከ መብላት ይደርሳሉ፡፡

እዚህ ደረጃ ላይ የሚደርሱት እንደ እኛ ‹‹አግዚአብሔር የማያውቀው የለም›› እያሉ በመብላት በመጠጣት ሳይሆን በጾም ተወስነው ነው፡፡
ጾም አንዱና ዋኛው የጸጋ መንገድ ነው፡፡ የትኛውንም ገድለ ቅዱሳን ብንመለከት አባቶቻቸን በልተው ሳይሆን ጾመው ነው የበቁት የተሰወሩት፡፡

ለዚህም ነው ጾሞ እንጂ በልቶ የበቃ ቅዱስ እስከ ዛሬ ያልተገኘው፡፡ ምናልባት ከበቁ በኃላ እንደ ፈለጉ ሊበሉ ይችላሉ፡፡ የአባቶቻችን የመንፈሳዊ ሕይወት አኗኗር የተመሠረተው በጾም ላይ ነው፡፡ ጾም ለእነሱ ቅጣት ሳይሆን ደስታ ነው፡፡ ጾም ለእነሱ ለሥጋቸውም ለነፍሳቸውም የተመቸ ነው፡፡

አባቶቻችን ወጥ የሆነ የጾም ሕይወት ነው ያላቸው፡፡ እኛ ደግሞ ስንጾም ለተወሰነ ሰዓት ከእህል ከውኃ እንከለከልና በኃላ ሰዓቱ ሲደርስ ጾሙን በምግብ ለማካካስ እንጥራለን፡፡ ጾም በመንፈሳዊ ጥቅሙ መንፈሳዊ ጥንካሬን እንድናገኝ በኃጢአታችን እንድንጸጸት ወደ እግዚአብሔር እንድንቀርብና ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅርም የምንገልጽበት ጭምር ነው፡፡ እውነተኛ ጾም አንድን መንፈሳዊ ሰው እራሱን እንዴት መቆጣጠር እንዳለበት ያሰለጥነዋል፡፡ ራስን መቆጣጠር ደግሞ ለቅድስና ሕይወት ዋና መሠረት ነው፡፡

ስለዚህ ጾምን የምናዘወትር ከሆነ ሥጋችንም ነፍሳችንም በጾም ቁጥጥር ስር ሆነች ማለት ነው፡፡ የሚጾም ሰው ሥጋውን እየጎዳ ነፍሱን የእግዚአብሔርን በረከት ያጠግባታል፡፡ የሚጾም ሰው ለጊዜው በሥጋ ቢከሳ ቢጎሳቆልም በነፍሱ ግን ምቾት ያለው ሰው ነው፡፡ በነገራችን ላይ ከምግብ እና ከመጠጥ ያልተቆጠበ ሰው ሕይወቱን ለጌታችን አሳልፎ ለመስጠት ሥጋውን ለመቆጣጣር እና ለመግዛት ይከብደዋል፡፡

የወለላይቱ እመቤት ልጆች ብዙዎቻችን እንደለመድነው እንደተማርነውም ‹‹ፅጌ ጾም የፍቅር ጾም እንጂ የአዋጅ ጾም አይደለም›› እንላለን፡፡ ልክም ነው፡፡ ግን ፅጌ ጾም የፍቅር ጾም ከሆነ ለምን በፍቅር አንጾምም? ‹‹አይደለም›› በምትለዋ አፍራሽ አማርኛ በፅጌ ፆም ስንቱ ሳይጠቀምበት ቀረ፡፡ ከሌሎቹ አጽዋማት እያሳነስነው ስንት የእመቤታችን በረከት ቀረብን፡፡ ዛሬ እንኳን በልተን ጾም ትተን ቀርቶ ጾመንም ጸልየንም ሰይጣን ከእኛ አልርቅ ፈተናችን አልላቀቅ ብሎናል፡፡
96 views05:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 13:30:25

1.7K views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 08:51:20
395 views05:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 08:51:03 ማዲንጎ ዘፋኝ እንደሆነ እያወቀ እንጦጦ ማርያም የመጣው ቤተ ክርስቲያን ፍርድ ቤት ሳትሆን ሐኪም ቤት እንደሆነች ስላወቀ ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በልጆቿ የምትፈርድ ሳትሆን ምህረት የምትለምን ናት፡፡ አንድ መርሳት የሌለብን ነገር ማዲንጎ ኦርቶዶክስ ነው፡፡ በእግዚአብሔር የሚያምን፣ በእመቤታችን ምልጃ የሚታመን፣ ስመ ክርስትና ያለው ሰው ነው፡፡

ወዳጆቼ ዘፋኝ በሞተ ቁጥር እኛው ዘፈናቸውን የምናዳምጥ አንድ ጥቅስ አንጠልጥለን፣ ጥቅሷን እየጠቀስን የሞተውን ሰው በጥቅስ ባንዘልፍ መልካም ነው፡፡ መጨረሻችንን ስለማናውቅ የሰውን ሞት አይተን፣ የሰማዩን ፍርድ ሳንመለከት አንፍረድ፡፡

በጌታ ቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ ለመዳን፣ ገነት ለመግባት ሦስት ሰዓት አልፈጀበትም፡፡ ሌባም ይሁን፣ ቀማኛ፣ ዘማዊ፣ ዘፋኝ ይሁን ከፈጣሪው ጋር ያለውን ግንኙነት ስለማናውቅ በማናውቀው ጥልቅ ባንል መልካም ነው፡፡ እንደ ክርስቲያን ማንም ሰው ቢሞት እግዚአብሔር እንዲምረው መጸለይ እንጂ መፍረድ እና ሲዖል እንዲማገድ ሟሟረት የለብንም።

ወዳጆቼ እኔ ማዲንጎን በዘፋኝነቱ እየደገፍኩት አይደለም፡፡ ነገር ግን ዘፈኑን የሰማው ነው የሚኮንነው፡፡ ሁሉም በተለያየ ቦታ እና ሁኔታ እንዲሁም ቤቱ ቁጭ ብሎ ዘፈን በማዳመጥ ዘፋኙን እየተባበረ ዘፋኝ ገነት አይገባም ይላል፡፡ ዘፋኝ ገነት አይገባም ማለት እኮ የማይዘፍን ገነት ይገባል ማለት አይደለም፡፡

ሁሉም በሥራው ነው ገነት የሚገባው፡፡ አንድ ዘፋኝ ዘፈኑን በዩትዩብ ሲለቅ ቀድመንና ተሽቀዳድመን ዘፈኑን የምናዳምጥ እኛው ክርስቲያኖች ነን። ከሚሊዮን ተመልካቾቻው ውስጥ ከግማሽ በላዩ እኛው ክርስቲያኖች ነን። ፈዘናቸውን የምናዳምጠው፣ እነሱንም የምናደንቀው፣ ስናገኛቸው አብሬ ፎቶ ከልተነሳው የምንለው እኛው ሲሞቱ ኮናኞች እኛው።

አንድ የማውቃቸው ጳጳስ ‹‹ስለ ዘፈን እና ስለ ዘፋኝ ምን ይላሉ?›› ስላቸው፡፡ ‹‹አይ ልጄ ሰው በአፉ ባይዘፍንም በልቡ ይዘፍናል›› አሉኝ፡፡ በአፋችን ሳይሆን በልባችን የምንዘፍን ብዙ ነን፡፡

ወደ ማጠቃለያው ስመጣ ማዲንጎ ሌሊት ሲዘፍን አድሮ ጠዋት አመም ሲያደርገው በቅርቡ ወዳለ ክሊኒት መኪናውን እያሽከረከ ሄዶ ለሕመሙ ማስታገሻ እንተወጋ እዛው አርፏል፡፡ እንዲህ አይነት ሞት ምናልባት ሕክምናው በምርመራ እና በአሟሟቱ ሂደት የራሱን ውጤት እና መላ ምት ይናገራል፡፡ በመናፍስቱ ውጊያ ግን እንደዚህ አይነት ማለትም ሰው ሳያመው እየሠራ ቆይቶ በድንገት አመመኝ ብሎ ከሞተ ከመተት እና ከጥላ ወጊ ጋር ይያያዛል፡፡

በተለይ በዚህ በጥበቡ፣ በሩጫው፣ በኳሱ በእውቅናው ዓለም ወዘተ ከፍተኛ የሆነ በመተት እና በጥላ ወጊ የመገፋፋት፣ እድል የመቀማማት፣ አንዱ አንዱን የማጥፋት ክፉ አባዜ አለ፡፡ ማዲንጎ ብቻ ሳይሆን በእሱ ሞያ ያሉ አርቲስቶች ቀድመው የማዲንጎን አይነት የሞት ጽዋእ ጠጥተው አልፈዋል፡፡ እንደውም አንዱ ዘፋኝ ችግሩን ስላወቀ "እባካችሁ ጸበል ውሰዱኝ" እያለ ጸበል ሳይወስዱት እንደሞተ አውቃለሁ።

በመተት እና በጥላ ወጊ የሚሞት ሰው አሟሟቱ ይናገራል፡፡ ጤነኛ ሆኖ በድንገት አመመኝ ብሎ የሕክምና ተቋም ሳይደርስ በድንገት ይሞታል፣ አመመኝ ብሎ ሐኪም ቤት ቢሄድም እርዳታ ቢደረግለትም ይሞታል፡፡ ልቤን፣ ልቤን ወጋኝ፣ ራሴን ወጋኝ፣ ደረቴን ወጋኝ፣ ጎኔን ወጋኝ፣ መተንፈስ አቃተኝ፣ ደከመኝ ወዘተ እያለ በድንገት ይሞታል፡፡ ጠዋት ታይቶ ከሰዓት ይሞታል፣ ከሰዓት ታይቶ ማምሻ ይሞታል፣ ማታ በሰላም ተኝቶ ጠዋት ሞቶ ይገኛል፡፡ ቤት ወይም ቢሮ አልያም የሥራ ቦታ ቁጭ ብሎ፣ እየሠራ በድንገት ይሞታል፡፡

ወዳጆቼ ስንት መላከ ሞት የሆኑ ክፉ ሰዎች አሉ፡፡ በተለይ በጥበቡ፣ ሩጫው፣ በኳሱ ወዘተ ዓለም ያላችሁ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር ካልቀረባችሁ፣ በጸሎት ካልበረታችሁ ሕይወታችሁን፣ ዕድላችሁን በምቀኞቻችሁ፣ በወዳጅ መሳይ ጠላቶቻችሁ ትነጠቃላችሁ፡፡ አንድ መረሳት የሌለበት አንድ ሰው በአንድ ሥራው ሲታወቅ የሚወዱትን ያህል አንዳንድ የሚጠሉት አለ። ከፍታውን ሲያዩ ዝቅታውን ለማየት ከላይ ወደ ታች የመጎተት ክፉ ሥራ የሚሠሩ አሉ። ታላቅ ስኬቱን ሲያዩ ለሞቱ ጉድጓድ የሚቆፍሩ አሉ።

ስለዚህ ኃላፊ በሆነ ዓለም ላይ እየኖርን የማያልፈውንና ችግራችንን የሚያሳልፈውን እግዚአብሔርን መዘንጋት የለብንም፡፡ ለጠላቶቹ፣ ለምቀኞቹ ልብ ይስጣቸው፡፡ የድምጻዊ የማዲንጎን ነፍስ የሚወዳት፣ የሚያከብራት የበላዔ ሰብእ እመቤት እመቤታችን በምልጇዋ፣ በቃል-ኪዳኗ በገነት ታኑረው፡፡ ለመላ ቤተሰቦቹ ልዑል እግዚአብሔር መጽናናትን ያድልልን፡፡

መስከረም 24-1-2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
386 views05:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 08:51:03 #ድምጻዊ_ማዲንጎ_አፈወርቅ_የሰጠኝ_የእመቤታችን_ስዕል!

#_ማዲንጎን_ለሰባት_ቀን_አጥምቄው_ነበር!

#_ማዲንጎ_እመቤታችንን_እጅግ_በጣም_ይወዳታል!

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ተወዳጆች ሆይ እኔ እና ድምጻዊ ማዲንጎ የተዋወቅነው ከዛሬ አንድ ዓመት ከአምስት ወር በፊት እንጦጦ ማርያም በማገለግልበት ጊዜ ነው፡፡ የትውውቃችን ምክንያት የእርሱ ሕመም እና ፈተና ነው፡፡ የምወደው እና የማከብረው ዘማሪ ስልክ ደውሎልኝ ‹‹አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ሊያናግርህ እና ሊያማክርህ ይፈልጋል ስለዚህ ስልክህን ሰጥቼዋለሁ ይደውልልሃል›› አለኝ፡፡ እኔም እሺ አልኩ፡፡

በደቂቃ ልዩነት ማዲንጎ ደወለልኝ፡፡ በዛ በሚያስረቀርቀው ድምጹ እወራኝ፡፡ ተቀጣጠርን፡፡ እንጦጦ ማርያም በጠዋት መጣ አገኘሁት፡፡ ማዲንጎን ሳገኘው በስልክ አንዳንድ ነገሮች እንዳወራነው ሳይሆን ፍጹም ደስተኛ፣ ፊቱም በደስታ የተመላ ነበር፡፡ ሰው አክባሪነቱ እና የዋህነቱ በግልጽ ይታያል፡፡

ከአገልግሎት መልስ የማርፍበት እና እንግዶችን የማናግርበት ቢሮ ነበረኝ፡፡ ማዲንጎን ቢሮ አስገብቼው ቁጭ አለ፡፡ እኔም ‹‹ማዲንጎ እመቤታችንን አክብረህ፣ ከእሷ መፍትሔ ፈልገህ በመምጣትህ ደስ ብሎኛል እንኳን ተገናኘን፡፡ ለመሆኑ የገጠመህ ፈተና፣ ሕመም ምንድነው?›› አልኩት፡፡

የዚህን ጊዜ የማዲንጎ ፊት ዳመነ፣ አዘነ፡፡ ማዲንጎም ‹‹ቀሲስ ብዙ ጊዜ ሌሊት እንቅልፍ አልተኛም፡፡ እንቅልፍ ከራቀኝ ረጅም ጊዜ ሆኖኛል፡፡ እንቅልፍ እንቢ ሲለኝ ዩትዩብ ስለምጠቀም አንዳንዴ የእርሶን ቪዲዎች አያለሁ፡፡ በተለይ ስለ መተት እና ክፉ መንፈስ በሰዎች ላይ የሚያደርሰውን ችግር እመለከታለሁ፡፡ ቪዲዮች ላይ የማያቸው ነገሮች አንዳንዱ ከእኔ ችግር ጋር ስለሚመሳሰል በዚህ ጉዳይ እና ስለ ሕመሜ ላወራህ ነው›› አለኝ፡፡

እኔም ‹‹ምንድነው የሚያምህ?›› አልኩት፡፡ እሱም ‹‹ከጀመረኝ ቆየት ብሏል፡፡ ሌሊት አልተኛም፣ በተኛሁበት የሚያፍነኝ ነገር አለ፣ የመድረክ ሥራዬ ለተወሰነ ጊዜ አስጠልቶች ከመድረክ ርቄ ነበር፣ ዝም ብሎ ፍርሃት ፍርሃት ይለኛል፣ በፊት መድረክ ላይ ሆኜ ስዘፍን ፍርሃት የሚባል አላውቅም አሁን ግን አይደለም ማይኩን ስይዝ ቀርቶ ገና የመድረክ ሥራዬን ሳስብ ከፍተኛ ፍርሃት ይሰማኛል፡፡

መድረክ ላይ ስዘፍን ከፍርሃቴ የተነሳ ላብ ያጠምቀኛል፣ በራስ መተማመኔ ይጠፋብኛል፡፡ ጭንቅ ይለኛል በዚህ ምክንያት አእምሮዬ ሰላም የለውም፣ ቀንም ሌሊትም እንቅልፍ የለኝም፡፡ የሚገርምህ በውጭ አለም ብዙ ሀገር ሄጄ ታክምያለሁ በተለይ አሉ የሚባሉትን ስፔሻሊስቶች አግኝቼ አማክርያሉ፣ በሕክምናቸውም ታይቻለሁ ግን የረባ መፍትሔ አላገኘሁም›› አለኝ፡፡

ማዲንጎ ችግሩን አውቋል ግን መፍትሔ አጥቷል፡፡ ማዲንጎ ችግሩን አውቋል ግን ችግሩ ከክፉ መናፍስት ጋር እንደተያያዘ ወይም የችግሩ እና የሕመሙ ምክንያት ምን እንደ ሆነ አላወቀለም ግን ጠርጥሯል፡፡

እኔም አንዳንድ መንፈሳዊ ነገሮችን ከነገርኩት በኃላ ላጠምቀው ወደ መጠመቂያ ጸበል ቤት ይዤው ሄድኩ፡፡ ማዲንጎም ልብሱን አውልቆ አጠመኩት፡፡ ለነገሩ አጠመኩት ከማለት በትንሹ ታገልን ማለት ይቀላል፡፡ ጸበሉ ሲነካው በጣም ተቸገረ፡፡ ብቻ ተጠመቀ ቅብዓ ቅዱስም ቀብቼው የእመቤታችንንም ጸበል አጠጥቼው ወደ ቤቱ ሄደ፡፡

ማዲንጎን ሳጠምቀው ያየሁበት እና የሆነውን ነገር ለቤተሰቦቹ እና ለወዳጆቹ ስል በዚህ ገጽ ለመጻፍ እና ለመናገር ይከብደኛል፡፡
ማዲንጎ በማግስቱ በጠዋት እንጦጦ ማርያም መጥቶ ተገኛኘን፡፡ ደስታው እና ፈገግታው ከትላንቱ በጣም ተለይቷል፡፡ አቀፈኝና ‹‹እመቤታችንን አመሰግናለሁ›› አለኝ፡፡

‹‹በምን አልኩት›› እሱም ‹‹ትላንት ከተጠመኩ በኃላ ውስጤ ከፍተኛ ሰላም እና መረጋጋት ተሰማኝ፡፡ ማታ ደግሞ የት እንደወደኩ ሳላውቅ በስንት ጊዜዬ ተኝቼ አደርክ፡፡ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነሳ በጣም ደስ አለኝ በእውነት እመቤታችን እንቅልፌንና ሰላሜን በአንድ ቀን መለሰችልኝ፡፡ ደረቴ እና ልቤ ላይ የሚያፍነኝም አሁን የለም ቀለል ብሎኛል አለኝ፡፡

እኔም በእሱ ደስታ ተደስቼ አጠመኩት፣ ቅብዓ ቅዱስ ቀብቼ ሸኘሁት፡፡ በእንዲህ ሁኔታ ማዲንጎን ለሰባት ቀን አጠመኩት፣ ቅብዓ ቅዱስም ቀባሁት ፍጹም ጤነኛ ሆነ፡፡ በስምንተኛው ቀን እመቤታችንን ለማመስገን ከአንድ ከግጥም እና ከዜማ ደረሲ ከሆነው ከወዳጁ ጋር መጣ፡፡

ለእኔም ‹‹አንድ ማስታወሻ ስጦታ ልሰጥህ ነበር፡፡ ነገር ግን ምን እንደምሰጥህ ሳስብ፤ እኔም እመቤታችንን እወዳታለሁ፣ አንተም ትወዳታለህ ስለዚህ ስጦታዬ እመቤታችን ናት›› ብሎ የምትመለከቷትን የእመቤታችንን ስዕል ሰጠኝ፡፡ እኔም እጅግ በጣም ተደሰትኩ፡፡

ነገር ግን ማዲንጎን አንድ ነገር አስጠነከኩት እንዲሁም አደራ አልኩት፡፡ ያስጠነከኩት ‹‹የመጣህ ቀን እንደ ችግር እና ሕመም የነገርከኝ ነገር በዚህ በመናፍስቱ ውጊያ አንድ ሰው በምቀኞቹ፣ በጠላቶቹ፣ ውድቀቱንና ሞቱን በሚፈልጉ ሰዎች መተት እና ጥላ ወጊ ሲላክበት የሚያየው ምልክት ነው፡፡

ለዚህም ነው በውጭ ሀገር ታክመህ መፍትሔ ያጣኸው፡፡ ለዚህም ነው በጸበል መፍትሔ ያገኘኸው፡፡ በሥራህ፣ በጤናህ፣ በሰላምህ ብሎም በእንቅልፍህ የሚፈትን፣ የሚላክብህ መተት አለ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ በምትበላው፣ በምትጠጣው እና በውሎህ ተጠንቀቅ፡፡ ሰውን ውደድ እንጂ አትመን፡፡ ማንም ሰው የሚጎዳው በተለይ በመተት የሚሰቃየው የእኔ በሚላቸው ሰዎች ስለሆነ የሚጠብቅ እግዚአብሔር ቢሆንም አንተም እንዳቅምህ እራስህ ጠብቅ፡፡

አደራ የምልህ እመቤታችንን ስለምትወዳት ማታ የዕለት ውዳሴ ማርያም አድርስ ወይም ጸልይ፡፡ ጠዋት ሰይፈ ሥላሴን ጸልይ፡፡ እመቤታችንን እና ቅድስት ሥላሴን ከያዝክ የክፉ ሰዎች እና የክፉ መናፍስት ውጊያ ይቀልልሃል፡፡ ስለዚህ አሁን ድነሃል ነገር ግን ፈተናው እንዳይበዛብህ እንዳቅምህ ጸልይ›› ብዬው ተሰነባበትን፡፡

ከሳምንት በኃላ ማዲንጎ ጋር ደወልኩ፡፡ ባሕር ዳር እና ጎንደር ለሥራ እንደሄደ ነገርኝ፡፡ ወደ ቀደመ ሥራውም በመመለሱ ተደሰተ። አልፎ አልፎ እንደዋወል ነበር፡፡ ሥራውም ጤናው ጥሩ እንደሆነና ችግር እንደሌለ ይነገርኝ ነበር፡፡ ቆየት ብዬ ስደውል ሥራው እንደቀድሞ በሚፈልገው ደረጃ ጥሩ እንደሆነለት እና ጤናውም በመልካም ሁኔታ እንደሚገኝ ይነገረኝ ነበር፡፡

እኔም ከእንጦጦ ማርያም ለቅቄ ወይም አምባ ማርያም ስገባ አገልግሎቱ እየበዛብኝ ጠዋት ወጥቼ ማምሻዬን ወደ ቤቴ ስለምሄድ በተለይ አገልግሎት ላይ ስለምውል ብዙ ጊዜ ስልኬ ዝግ ነበር፡፡ ማዲንጎም በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ብዙ የበረከት ሥራ መሥራት እንደሚፈልግ ቢነግረኝም ሳንገናኝ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ሰማሁ፡፡ ማዲንጎ ሩቅ አሳቢ ቅርብ አዳሪ ሆነ፡፡ ማንም ሰው ወደማይቀረው ዓለም ላይመለስ ሄደ፡፡

እጅግ የሚያሳዝነው ግን አንዳንዶች ማዲንጎ ሲሞት ‹‹ዘፋኝ መንግሥተ ሰማያት አይገባም›› እያሉ እሱን የሲዖል ሰው እራሳቸውን የገነት ሰው ያደርጋሉ፡፡ የባሰባቸው ደግሞ በእግዚአብሔር ፍርድ ጣልቃ ገብተው ይፈርዳሉ፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ ማዲንጎ እመቤታችንን እጅግ በጣም ይወዳታል፡፡ ስለሚወዳትም ነው ለእኔ የእመቤታችንን ስዕል ከሚያምር መጋረጃ ጋር አሳምሮ የሰጠኝ፡፡

በእውነት ሰባ ስምንት ሰው በልቶ፣ በእመቤታችን ስም ጥረኝ ውኃ ሰጥቶ በእመቤታችን ቃል ኪዳን የዳነው ስምዖን/በላዔ ሰብእ/ በነፍሱ እንደዳነ ማዲንጎ አይድንም? የበላዔ ሰብእ እመቤት እመቤታችን ለሚወዳት ለማዲንጎ ለነፍሱ መዳኛ አትሆንም? በምልጃዋ በቃል-ኪዳኗ አታድነውም?
356 views05:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ