2022-05-13 15:54:55
ክሎፕ ከነገው ጨዋታ በፊት የሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ።
ክሎፕ የኤፍኤ ካፕ ዋንጫን በማሸነፍ ላይ፦
"ያለ ጥርጥር የኤፍኤ ካፕ ዋንጫን ማሸነፍ እንፈልጋለን። ይህንን ክብር ከ2006 ጀምሮ አላሳካነውም ቼልሲ 3-4 ጊዜ አሳክቶታል ስለዚህ እኛ ዋንጫውን እንፈልገዋለን። ለማሸነፍ በጣም እንሞክራለን"
ክሎፕ ስለ ኤፍኤ ካፕ ዋንጫ ትልቅነት፦
"ኤፍኤ ካፕ የአለማችን ትልቁ የቤት ውስጥ ውድድር ነው። ይህ ውድድር ምን ያህል ግዙፍ እንደሆነ መረዳት ይቻላል"
ክሎፕ ኤፍኤ ካፕ ለእነሱ ምን ማለት እንደሆነ፦
"የኤፍኤ ካፕ ፍፃሜ ለእኔ ልዩ ግጥሚያ እና ለአንዳንዶች ደግሞ በስራው ትልቅ ውድድር ነው። እየተዝናናን ለደጋፊዎቻችን ድሉን ማብሰር እንፈልጋለን"
ክሎፕ፦ "ይህንን እድል በጉጉት እየጠበቅን ነው። እናም ለእኛ በጣም ትልቅ ፍፃሜ ነው የዚህ ውድድር አካል በመሆኔ ደስተኛ ነኝ"
ክሎፕ፦ "ከዚህ በፊት ለፍፃሜ ለመድረስ ያለንን ሁሉ ሰጥተን ነበር ግን አልተሳካልንም። በግልፅ ስትጓዝ ሁሉም ነገር በአንድ ጊዜ ሊኖርህ አይችልም"
ክሎፕ ስለ ቼልሲ፦
"ይህ ከቼልሲ ጋር የሚደረግ ጨዋታ እና ግጥሚያ ፍፁም የተለየ ነው። ቼልሲ የተደራጀ እና በሁሉም ሜዳ የጠራ ሀሳብ ያለው ምርጥ ቡድን ነው። እነሱ በተከላካይ የተደራጁ ቡድኖች ናቸው። እና ቼልሲ እንዴት እንደሚጫወት የምናውቀው ትክክለኛ ነገር የለንም። ብዙ አማራጮች አሉን አንዳድ ጊዜ ሲጫወቱ ከአንዳድ ክለቦች ጋር ተመሳሳይ ስታይ አላቸው። ግን እነሱ በተለየ ጥራት ነው ሚጫወቱት"
@liverpool4321 @liverpool4321
1.1K viewsMOHAMMED LIVERPOOL, 12:54