Get Mystery Box with random crypto!

ኮተቤ ብርሃነ ህይወት ትምህርት ቤት

የቴሌግራም ቻናል አርማ kotebebirhanehiywotschool — ኮተቤ ብርሃነ ህይወት ትምህርት ቤት
የቴሌግራም ቻናል አርማ kotebebirhanehiywotschool — ኮተቤ ብርሃነ ህይወት ትምህርት ቤት
የሰርጥ አድራሻ: @kotebebirhanehiywotschool
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 481

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-01-05 06:44:45 ዉጤታማ የአጠናን ዘዴዎች 

ለነገ ዝግጁ ሁኑ!!!...ሁልጊዜም ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ነገ ለምትሰሩት ዕቅድ በማዉጣት ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል!
በየቀኑ የተማራችሁትን ማንበብ  ፤ከስር ከስር ማጥናት!
የተመጠነ የንባብ ጊዜ
መመደብ ፤መሠላቸት ሳይኖር በተነቃቃ መንፈስ ዉጤታማ ጥናት ለማካሄድ በቂ ሰዓት መጠቀም!
የምናጠናቸዉን የት/ት አይነቶች በጊዜ መከፋፈልና ቅደም ተከተል ማስያዝ!
በጥናት ወቅት ከጨዋታና ማህበራዊ ሚዲያ ራስን ማራቅ!
ምቹ እና ትኩረት ለማድረግ የሚረዳ የጥናት ቦታ መምረጥ!
ለጥናት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በቅድሚያ ማዘጋጀት!
ማስታወሻ በአጭር በአጭሩ መያዝ!
አይገባኝም ከሚል አስተሳሰብ መዉጣት!
በት/ቤት የጥናት ቡድን መፍጠር ፤ከትምህርት አቻ ጓደኞቻችን ጋር እዉቀትና ልምዶችን መጋራት!
በየጊዜው የሚሰጡ የክፍል ፈተና ጥያቄዎችን ደጋግሞ መስራትና ከስህተት መማር!
ስናነብ ግልጽ ያልሆኑልን ነጥቦች ካሉ ማስታወሻ ይዞ ከመምህራን ጋር መወያየት!

መልካም የጥናት ጊዜ!
103 views03:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 23:06:12
94 views20:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 23:04:23 26/04/15ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለ8ተኛ እና 6ተኛ ክፍል ለምታስተምሩ መምህራን በሙሉ
የተማሪዎቹ ውጤት በፎርሙ መሰረት ተተንትኖ ከ100% በመቀየር እስከ ማክሰኞ 1/05/15ዓ.ም ድርስ ለዲፓርትመንት ገቢ እንድታደረጉ በጥብቅ እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚፈጠረው የመልካም አስተዳደር ችግር መምህሩ ራሱ ሀላፊነት የሚወስድ ይሆናል፡፡
• ዲፓርትመንት ከመምህራን ውጤቱን በመሰብሰብ ጥቅል ትንተና በመስራት እስከ ማክሰኞ 2/05/15ዓ.ም ቢሮ ገቢ የሚደርግ ይሆናል፡፡
• መማር ማስተማር ጥቅል ትንተና በመስራት በ3/05/15 ዓ.ም ክ/ከተማ ይልካል፡፡
94 views20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-31 21:11:06 ውድ የትምህርት ቤታችን መምህራን፣ አስተዳደር ሰራተኞችና ተማሪዎች በሙሉ የትምህርት ቤታችን ተማሪ እዩኤል ዩሀንስ የ7D ክፍል የሆነው በድንገት ህይወቱ ስላለፈና የቀብር ስነ-ስረዓት የሚፈፀመው ነገ ማለትም እሁድ ከቀኑ 5፡30 በቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን ስለሆነ ሁላችንም ተሰባስበን ወደ ቀብሩ እንድንሄድ መምህራን፣አስተዳደር ሰራተኞችና ተማሪዎች ከጥዋቱ 3፡00 ላይ ትምህርት ቤት እንገናኝ ሲል ትምህርት ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
እንዲሁም ለወላጆቹ፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለመምህራንና ለጓደኞቹ በሙሉ እ/ር ያፅናችሁ፣ መፅናናትን ይስጣችሁ እያለ ነብሱን እግዚአብሔር በአፀደ ገነቱ ያኑርልን፡፡
105 views18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 21:12:50
122 views18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 21:12:50
122 views18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 21:10:04
110 views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-26 21:15:27 ሰላማዊ የመማር ማስተማሩን ሂዳትን ለማስፈን ቁርጠኛ መሆናቸውን መምህራን ገለጹ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

የካ ወረዳ12 ኮሙኒኬሽን፦ ታህሳስ17/2015ዓም

በየካ የወረዳ12 አስተዳደር የሚገኙ ት/ቤቶች መምህራን ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በወረዳው የሚገኙ የመንግስት ት/ቤቶች ከመምህራን ጋር በተደረገው ውይይት ትምህርት ቤቶች የዕውቀትና የክህሎት ማበልጸጊያ ተቋማት መሆናቸውን የገለፁት መምህራኑ ሰሞኑን ተፈጥሮ የነበረው የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማወክ የተደረጉ ሙከራዎች መምህራንና ተማሪዎችን የማይወክሉ የጽንፈኞች ተልኮ የነበረና በሁሉም ርብርብ መክሸፋን ተናግረዋል።

በዚህም መምህራን ትምህርት ቤቶችን የዕውቀት፣ የስነምግባርና የክህሎት ማበልጸጊያ ተቋማት በማድረግ የነገ አገር ተረካቢ ትውልድን የሚፈጠርበት በመሆናቸው በቀጣይ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስቀጠል በሙሉ ዝግጅትና ሁኔታ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመድረኩ ላይ የክ/ከተማና የወረዳው አመራሮች የተገኙ ሲሆን በየካ ክ/ከተማ የወረዳ12 የዲሞክራሲ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አድስ ዘውዴ ሰላማዊ መማር ማስተማር ሂደት አስጠብቆ ማስቀጠል ለማንም የማይተው የሁላችንም ድርሻ ነዉ ሲሉ በውይይቱ ላይ ለተሳተፋ በወረዳው ከሚገኙ ሁሉም የመንግስት ት/ቤቶች መምህራን አሳስበዋል። በመቀጠልም ሰላም የሁሉንም ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ ሁላችንም የየግል ሚናችንን በመወጣት ሰላማዊ መማር ማስተማር ሂደቱ ሳይቆራረጥ ማስቀጠል ይኖርብናል ብለዋል።

በውይይቱ ተሳታፊ የሆኑ መምህራንም ተልኳቸውና ስራቸው ትውልድን መቅረጽ በመሆኑ የፖለቲካ ነጋዴዎችን ሴራ ባለማስተናገድ ት/ቤቶች የዕውቀት ማዕከላት እንዲሆነ እንሰራለን ብለዋል። ለዚህም ሰላማዊ የመማር ማስተማር ስርዓቱን ለማስቀጠል ከመቼውም ጊዜ በላቀ ሁኔታ ዝግጁ ነን ሲሉ ገልጸዋል።

በመጨረሻም ህብረብሔራዊ ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን መሰረት ያደረገ አንድነትን በማጎልበት መምህራን ለተማሪዎቻቸው ምሳሌ በመሆን ት/ቤቶች ያላቸውን ድርሻና ሀላፊነት መወጣት እንደሚገባቸው አጠቃላይ መግባባት ላይ ተደርሷል።
69 views18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-25 18:59:40 ውድ መምህራን የነገው ስልጠና በካራሎ የመ/ደ/ት/ቤት የሚካሄድ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ከጥዋቱ 2፡00 ላይ ስልጠናው የሚጀመርበት ሲሆን ሳታረፍዱ ቀድማችሁ ተገኙ ሲል ትምህርት ቤቱ ያሳስባል፡፡ ስልጠናው የሚያበቃው 11፡30 ነው፡፡ የሻይ ቡናና የምሳ ፕሮግራም ትምህርት ቤቱ ያመቻቻ መሆኑን ያሳውቃል፡፡
ስልክ ይዞ መምጣት አይቻልም
118 views15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 21:26:50 14/04/15ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለመምህራን በሙሉ
ሰኞ 17/04/15ዓ.ም በከተማ ደረጃ በሚመጡ አመራሮች በካራሎ የመ/ደ/ትምህርት ቤት ስልጠና ስለሚሰጥ ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ በተመደባችሁበት ክፍል እንድትገኙ ት/ቤቱ በጥብቅ ያሳስባል፡፡
• ማሳሰቢያ፡-መምህራን በተመደባችሁበት ክፍል ብቻ አቴንደስ የሚያዝ ይሆናል
• ሁሉም መምህራን ሞባይል ስልክ ይዞ መምጣት የተከለከለ ነው፡፡
• በሰአቱ በመገኘት ስልጠናውን በጥብቅ ዲሲፕሊን እንድትከታተሉ ትምህርት ቤቱ ያሳውቃል፡፡
104 views18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ