2022-12-15 14:39:17
ያገለገሉ የተለያዩ አይነት ተሽከርካሪዎችን በጨረታ ለመሸጥ የወጣ ማስታወቂያ (የአገር መከላከያ ሚ / ር የመከላከያ ንብረት ማስወገድ ኮሚቴ )
Deadline: ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4፡00 (2022-12-21)
አዲስ ዘመን ቅዳሜ ህዳር 24 ቀን 2015 ዓ . ም
ያገለገሉ የተለያዩ አይነት ተሽከርካሪዎችን በጨረታ
ለመሸጥ የወጣ ማስታወቂያ
በአገር መከላከያ ሚ / ር የመከላከያ ንብረት ማስወገድ ኮሚቴ ያገለገሉ የተለያዩ አይነት ተሽከርካሪዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሽጥ ይፈልጋል።
ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከህዳር 27 ቀን 2015 ዓ . ም . እስከ ታህሳስ 11 ቀን 2015 ዓ . ም . ባሉት ቀናቶች ከጠዋቱ 3 ፡ 00 እስከ 10 ፡ 00 ሰዓት ድረስ በኢፌዲሪ አገር መከላከያ ሚ / ር አዲስ አበባ ምድር ኃይል ግቢ ፋይናንስ ስራ አመራር ዘርፍ ህንፃ ቢሮ ቁጥር 01 በመገኘት የማይመለስ ብር 200 ( ሁለት መቶ ) ብር ብቻ በመክፈል መግዛት ይኖርባቸዋል።
ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ተሽከርካሪ ለመሸጥ የተቀመጠውን የጨረታ መነሻ ዋጋ 20 በመቶ (20%) Ministry of National Defense Property Sales Saving Account/ አገር መከላከያ ሚኒስቴር ንብረት ሽያጭ ማጠራቀሚያ ስም የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ በሲፒኦ ብቻ ተሞልቶ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት በጨረታ ሳጥኑ ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
ተጫራቾች ከህዳር 27 ቀን 2015 ዓ . ም እስከ ታህሳስ 11 ቀን 2015 ዓ . ም . ባሉት ቀናቶች የሚሸጡትን ተሽከርካሪዎች ኮፈን ተከፍቶ ስለሚቆይ ዘወትር በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 3 ፡ 00 እስከ 10 ፡ 00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎቹን ደ / ዘይት ( ቢሾፍቱ ) አውቶሞቲቭ ካምፕ ጀርባ በመሄድ ሙያተኛ ይዞ መመልከት ይቻላል።
ተጫራቾች ከጨረታ ሰነዱ ጋር በተያያዘው የዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ ላይ ብቻ ተጫራቾች የሚገዙበትን ዋጋ፣ ስማቸውን ክ / ከተማ፣ወረዳ የቤት ቁጥርና ስልከ ቁጥራቸውን በመግለፅና በመፈረም ማቅረብ አለባቸው።
ከጨረታ መዝጊያ ሰዓት በኋላ የሚደርሱ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም።
ጨረታው ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ . ም . ከጠዋቱ 4 ፡ 00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን 4:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሲሆን የሁሉም ተሽከርካሪዎች ጨረታ ምድር ኃይል ግቢ ፋይናንስ ስራ አመራር ዘርፍ ህንፃ ቢሮ ቁጥር 01 ይከፈታል።
አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ገንዘብ አጠቃለው ከከፈሉ በኋላ ተሽከርካሪውን በ 20 የስራ ቀናት ውስጥ የማንሳት ግዴታ አለባቸው።
የስም ማዛወሪያ ወጪዎች ሙሉ በሙሉ በገዥው ይሸፈናል።
መ / ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡ _ አድራሻ አዲስ አበባ ምድር ኃይል ግቢ ፋይናንስ ስራ አመራር ዘርፍ
ስልክ ቁጥር፡ - 011 372 2860/ 011 372 2887 መደወል ይቻላል።
የአገር መከላከያ ሚ / ር የመከላከያ ንብረት ማስወገድ ኮሚቴ
ሙሉ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚወጡ ጨረታዎችን በየቀኑ ለማግኘት ድረ-ገጻችንን ይጎብኙ
http://www.habeshatender.com
በየቀኑ ጨረታዎችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/habeshatender
ነጻ እና ሁሉንም ጨረታዎች በቀላሉ ለመከታተል አፕልኬሽኑን አውርደው ይጠቀሙ።
ለማውረድ ይህንን ሊንክ ይንኩት
http://www.habeshatender.com/m/apkdownload.php?file=habeshatender.apk
ሐበሻ ቴንደር የኢትዮጵያ ጨረታዎች የመረጃ ምንጭ
739 views11:39