2023-11-09 16:53:32
በ24 ሰአት ፊንፍኔ መግባት እንደማይቻል የተረዳው ጃንዳዊዱ ፋኖ ፊቱን ወደ ክልሉ በመመለስ ሌላ አደገኛ እልቂት እየሰነቀ ይገኛል።
የአማራው ገዳይ ቡድን ፋኖ ወደ ፊንፍኔ ያደርሰኛል በማለት የያዘውን መንገድ ተገድዶ ቢያቋርጥም ፊቱን ወደራሱ ክልል መልሶ "አማራ አይደለሁም" ያሉ የራሳቸው ማንነት ባላቸው ብሄረሰቦች ላይ ተከታታይ ዘመቻ በማድግ ላይ ይገኛሉ።
ይህ ቡድን የወሎ ኦሮሞ ተወላጆች ላይ የሞከራቸው ተከታታይ ጥቃቶች መሪዎቹን ጭምር የህይወት ዋጋ ስላስከፈላቸው ወደ ወሎ ኦሮሞ የሚያደርጉትን ወረራ በማቋረጥ ከጎንደር እና ከጎጃም የተሰባሰበው ወሮበላው ቡድን ፊቱን ወደ አገው ምድር ህዝብ ላይ መልሶ
"አገው ነኝ" ያለውን እና ባልታጠቀው ህዝብ ላይ ድምጻቸውን አጥፍተው በተከታታይ እየጨፈጨፉት ይገኛል።
ሶስት ወረዳዎችን ዘልቆ የገባው የፋኖ ታጣቂ ሀይል ግምጃቤት ከተማ ላይ ገብቶ የሚገድለውን ገድሎ አቅሙ የቻለለትን እየዘረፈ ይገኛል።
የጃዊ (ቋራ አከባቢ) የሚገኘው የአገው ህዝብ በፋኖ ሀይሎች እጅ ከወደቁ አንድ ሳምንት የሞላቸው ሲሆን ገበያ ሲገበያይ የነበረውን ህዝብ ሴት ወንድ ሳይሉ 36 ሰዎችን በጥይት ደብድበው የገደሉ ሲሆን በጃዊ የሚኖረው የአራት ቀበሌ ህዝብ ቤት ንብረቱን ጥሎ ተፈኖቅሎ ያገኛል ።
በዚህ ወረራ ውስጥ በክልሉ የመንግስት የስልጣን እርከን ላይ የሚገኙ አመራሮች ጭምር ከገዳዩ የፋኖ ቡድን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት በማድረግ አገውን የማጥፋት ዘመቻ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በአሁኑ ሰአት ቁጥሩ የበዛ የዚህ ወራሪ ሀይል እንጅባራ ከተማ ለመግባት እየሞከረ ሲሆን ጥቂት የሚባሉ የአገው ወጣቶች ከተማቸውን ከዚህ ወንበዴ ቡድን ለመከላከል እየሞከሩ ቢሆንም ከትጥቅ እና ከቁጥር ብዛት አንጻር ከአቅማቸው በላይ እየሆነባቸው በመሆኑ ለሚመለከተው አካል ጥሪያቸውን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
16.6K viewsGumaa Saaqataa, 13:53