2021-06-27 10:58:05
ግሥ በአሥርቱ መራሕያን ሲዘረዘር
አንድን ግሥ በመራሕያን ለማርባት የሚከተለውን ሕግ እንጠቀማለን።
ምሳሌ የተሰጠን ግሥ ፣ ቀደሰ = አመሰገነ
የሦስተኛ መደብ መራሕያን
#ውእቱ ሲሆን ቅጥያ የለውም። ግሡ እንዳለ ይቀመጣል።
ምሳሌ፦ ውእቱ ቀደሰ= እርሱ አመሰገነ
#በይእቲ ጊዜ ግሡ ምንም ሳይቀየር #ት መጨመር ብቻ ነው። በአማርኛው ደግሞ #ች
ምሳሌ፦ ይእቲ ቀደሰት = እርሷ አመሰገነች
#በውእቶሙ ጊዜ የመጨረሻውን ፊደል ወደ #ካብዕ (ሁለተኛ) ፊደል መቀየር ነው።
ምሳሌ፦ ውእቶሙ ቀደሱ = እነርሱ ቀደሱ። (#ሰ ወደ #ሱ ይቀየራል)
#በውእቱን ጊዜ የመጨረሻ ፊደሉ ወደ #ራብዕ (አራተኛ) ፊደል ይሸየራል።
ምሳሌ፦ ውእቶን ቀደሳ = እነርሱ አመሰገኑ(ለሴቶች) (ሰ ወደ ሳ)
በእንደኛና ሁለተኛ መራሕያን መደብ መራሕያን ጊዜ የተሰጠንን ግስ የመጨረሻውን ፊደል ወደ ሳድስ ከቀየርን በኋላ ቅጥያዎችን እንደመራሕያኑ አይነት እንጨምራለን።
#በአነ ጊዜ የመጨረሻው ፊደል ወደ #ስድስተኛ (ሳድስ) ፊደል ይቀየርና #ኩ ቅጥያ ይጨመራል። የአማርኛ ቅጥያ አቻው #ሁ
ምሳሌ፦ አነ ቀደስኩ = እኔ አመሰገንሁ ( ሰ ወደ ስ፣ መጨረሳ ኩ መጨመር)
#በንሕነ ጊዜ የመጨረሻው ፊደል ወደ ስድስተኛ (ሳድስ) ፊደል ይቀየርና #ነ ቅጥያ ይጨመራል። የአማርኛ አቻ ቅጥያው #ን
ንሕነ ቀደስነ = እኛ አመሰገን
#በአንተ ጊዜ የመጨረሻው ፊደል ወደ ስድስተኛ (ሳድስ) ፊደል ይቀየርና #ከ ቅጥያ ይጨመራል። የአማርኛ አቻ ቅጥያው #ህ
ምሳሌ፦ አንተ ቀደስከ = አንተ ቀደስህ
#በአንቲ ጊዜ የመጨረሻው ፊደል ወደ ስድስተኛ (ሳድስ) ፊደል ይቀየርና #ኪ ቅጥያ ይጨመራል። የአማርኛ አቻ ቅጥያው #ሽ
ምሳሌ፦ አንቲ ቀደስኪ = አንቺ አመሰገንሽ።
#በአንትሙ ጊዜ የመጨረሻው ፊደል ወደ ስድስተኛ (ሳድስ) ፊደል ይቀየርና #ክሙ ቅጥያ ይጨመራል።
ምሳሌ፦ አንትሙ ቀደስክሙ = እናንተ አመሰገናችሁ (ለብዙ ወንዶች)
#በአንትን ጊዜ የመጨረሻው ፊደል ወደ ስድስተኛ (ሳድስ) ፊደል ይቀየርና #ክን ቅጥያ ይጨመራል። የአማርኛ አቻ ቅጥያው #ችሁ
ምሳሌ፦ አንትን ቀደስክን= እናንተ አመሰገናችሁ (ለብዙ ሴቶች)
ምሳሌ ፩) ቀተለ = ገደለ
በ ፲ መራሕያን ሲረባ፦
በአንደኛና ሁለተኛ መደብ መራሕያን ጊዚ "ቀተለ" ከሚለው የመጨረሻ ፊደል #ለ ወደ #ል ትቀየራለች
፩) አነ ቀተልኩ= አኔ ገደልሁ
፪) ንሕነ ቀተልነ=እኛ ገደልን
፫) አንተ ቀተልከ=አንተ ገደልህ
፬) አንቲ ቀተልኪ=አንቺ ገደልሽ
፭) አንትሙ ቀተልክሙ= እናንተ ገደላችሁ
፮) አንትን ቀተልክን= እናንተ ገደላችሁ
በሦስተኛ መደብ መራሕያን
፯) ውእቱ ቀተለ= እርሱ ገደለ
፰) ይእቲ ቀተለት=እርሷ ገደለቺ
፱) ውእቶሙ ቀተሉ=እነርሱ ገደሉ
፲) ውእቶን ቀተላ= እነርሱ ገደሉ
በዚህ መሰረት የሚከተሉትን ግሶች በአሥሩ መራሕያን ዘርዝሩ።
ሀ) ወደሰ = አመሰገነ
ለ) ነበረ = ተቀመጠ
ሐ) ሀለወ = አለ፣ ኖረ
929 views07:58