Get Mystery Box with random crypto!

Farankaa - ፈራንካ

የቴሌግራም ቻናል አርማ farankaa — Farankaa - ፈራንካ F
የቴሌግራም ቻናል አርማ farankaa — Farankaa - ፈራንካ
የሰርጥ አድራሻ: @farankaa
ምድቦች: ኢኮኖሚክስ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.92K
የሰርጥ መግለጫ

The ultimate objective of this page is to improve the financial literacy of Ethiopians by providing information regarding Investment, Banking, Insurance, Capital Market and Taxation

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-01-14 15:33:37 In addition, those of you who have graduated in the field of animal resource development and registered through the cooperative work commission are required to participate in the fourth round of training so we urge you to attend the branches of the Ethiopian development bank that are near you and register.
Those of you who are ready to take advantage of the interest free banking services offered by our bank and those who want to take training as small and medium enterprises, we inform you that you can attend the training by attending the branches of our bank near you and register.
Notice:
If you don't take the training for five consecutive days, you will not be eligible for the certificate.
We would like to inform you that you will get more information regarding the new stock options offered by the bank on our social media pages or the branches of the Ethiopian Development Bank.
Development Bank of Ethiopia
Your partner in development
331 views12:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-14 15:31:28 በአራተኛ ዙር የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች በሚሰጠው ስልጠና መሳተፍ ለምትፈልጉ በሙሉ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ተደራሽነቱን በማስፋት የዲስትሪክቶቹን ቁጥር ከ12 ወደ 24፤ የቅርንጫፎቹን ቁጥር ደግሞ ወደ 108 በማሳደግ ይበልጥ በማሳደግ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ በያዝነው የ2015 ግማሽ ዓመት ለአራተኛ ጊዜ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠና ለመስጠት ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
ባንካችን እያደገ የመጣውን የሰልጣኞችን ፍላጎት እና ቁጥርን ታሳቢ በማድረግ ስራዎች ሲሰራ የቆየ ሲሆን፣ ለአራተኛውን ዙር ስልጠና ምዝገባም በ24 ከተሞች ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ የባንኩ ቅርንጫፎች ለማካሄድ ባንካችን ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
ተሳታፊዎች ሥልጠናውን ለመውሰድ የሚያስችላችሁን ምዝገባ ለማድረግ ከጥር 06 እስከ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ ቅዳሜና እሁድ ጨምሮ በመላ የሀገሪቱ ከተሞች በሚገኙ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዲስትሪክቶች ስር በሚገኙ 108 ቅርንጫፎች ማለትም፡-
1. በአዲስ አበባ  
2. ጎንደር  
3. ባህርዳር  
4. ደሴ 
5. አሶሳ  
6. ደብረብርሃን 
7. ነቀምት 
8. ሁመራ 
9. ጅግጅጋ 
10. አዳማ  
11. ደብረማርቆስ 
12. ወላይታ ሶዶ 
13. ጅማ 
14. ድሬዳዋ 
15. ሻሸመኔ 
16. ጎባ 
17. መቐለ 
18. ሽረ 
19. ወልቂጤ 
20. አርባምንጭ 
21. ቦንጋ 
22. ሐዋሳ 
23. ሰመራ እና 
24. ጋምቤላ
25. ሰቆጣ ከተሞች በሚቀርባችሁ አካባቢ በመሄድ እንድትመዘገቡ በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡ 
በመሆኑም ተሳታፊዎች ከጥር 5 እስከ ጥር 15 ቀን 2015 ዓ.ም ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ ባሉት ቀናት ተገኝታችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
በስልጠናው ለመሳተፍ ብቁ የሚያደርጉ የመመዝገቢያ መስፈርቶች፡-
1ኛ. ማንኛውም ሰልጣኝ ማንነቱን የሚገልጽ ማስረጃ ይዞ ወይም ህጋዊ ወኪሉ በአካል በአቅራቢያው በሚገኝ የባንኩ ቅርንጫፍ በመቅረብ መመዝገብ ይኖርበታል፣
2ኛ. ሰልጣኞች የትምህርት ዝግጅታቸው ቢያንስ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ወይም በቀድሞው የ10ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ወይም በአሁኑ የ12ኛ ክፍልን ያጠናቀቁ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ ነገር ግን ቀደም ብሎ በንግድ ስራ ላይ ቢያንስ ሶስት ዓመት ሲሰሩ የቆዩ ሆነው ህጋዊ የንግድ ፍቃድ በማቅረብ ስልጠናውን መሳተፍ የሚችል፣
3ኛ. ሰልጣኙ በግል፣ በሽርክና ወይም በአክሲዮን ተደራጅቶ ለመስራት ፍላጎት፣
4ኛ. ሰልጣኙ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሳያቋርጥ መሰልጠን ይጠበቅበታል፣
በተጨማሪ ከአሁን ቀደም በእንስሳት ሃብት ልማት ዘርፍ ተመርቃችሁ በህብረት ስራ ኮሚሽን በኩል ምዝገባ ያካሄዳችሁ በሙሉ በአራተኛው ዙር ስልጠና መሳትፍ ስለሚጠበቅባቸው በአቅራቢያችሁ በሚገኙ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ቅርንጫፎች በመገኘት እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
ባንካችን በቀጣይ የሚሰጣቸውን ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ለመጠቀም የተዘጋጃችሁ እና የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ሆናችሁ ስልጠና መውሰድ የምትፈልጉ በሙሉ በአቅራቢያችሁ በሚገኙ የባንካችን ቅርንጫፎች በመገኘትና በመመዝገብ ስልጠናውን መሳተፍ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡ 
ማሳሳቢያ
ስልጠናውን ለአምስት ተከታታይ ቀናት ያልወሰደ ለሰርተፊኬት ብቁ አይሆንም፡፡
ባንኩ አዲስ ያቀረበውን የአክሲዎን አማራጭ በተመለከተ ዝርዝር መረጃዎችን በባንካችን የማህበራዊ ትስስር ገጾች አልያም በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ቅርንጫፎች በአካል በመቅረብ የምታገኙ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
           የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
               የልማት አጋርዎ!


For all those who want to participate in the fourth round of training for small and medium enterprises
The Ethiopian Development Bank is expanding its reach and increasing the number of districts from 12 to 24 and the number of branches to 108. It has completed its preparation to give training to enterprises for the fourth time in the half of the year 2015
Our bank has been working keeping in mind the growing number of trainees in mind. Our bank has completed its preparation to conduct registration for the fourth round of training in different branches of the bank found in 24 cities.
Participants to register to take the training from January 06 to 16 2015 E.C. In the coming days, including weekends, in all cities of the country, Ethiopia Development Bank's 108 branches found under districts.
1. In Addis Ababa
2. Gondar
3. Bahir Dar
4. Dessie
5. Assosa
6. Debre Birhan
7. Neqemt
8. Humera
9. Jigjiga
10. Adama
11. Debremarkos
12. Wolayta Sodo
13. Jimma
14. Dire Dawa
15. Shashemene
16. Goba
17. Mekelle
18. Share
19. Wolkite
20. Arba Minch
21. Bonga
22. Hawassa
23. Semera and her husband
24. Gambella
25. Sekota cities, we invite you to go and register.
Therefore, participants from January 5 to February 15, 2015 E.C. We invite you to register on the following days including Saturday and Sunday.
Registration requirements that make you eligible to participate in the training:-
1st. Every trainee should have to register with evidence that shows his identity or his legal agent in person at the nearest bank branch.
2nd. Trainees must have at least completed their high school education or have completed their previous 10th grade or current 12th grade. However, those who have been in business for three years and can participate in the training by providing a legal business license.
3rd. The trainee is willing to work individually, in partnership or in an organization.
4th. The trainer is supposed to train for five consecutive days.
328 views12:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-14 06:25:31 በፍጹም መሞከርህን/ሽን አታቁም/ሚ!


*

https://www.linkedin.com/posts/daily-link-129174211_never-every-give-up-ugcPost-7018236761101271041-zOJx?utm_source=share&utm_medium=member_android
428 viewsedited  03:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 07:07:34 ከዚህ አንጻር የኢትዮጵያ የንብረት ታክስ ህጎች ሁለት መሰረታዊ ውስንነቶች አሉባቸው፡፡ከእነዚህም ውስጥ በአሁኑ ጊዜ ባለው የሀገሪቱ የንብረት ታክስ አጣጣል መሰረት በከተማ መሬቶች ላይ የሚጠል ታክስ አለመኖሩ አንደኛው ነው፡፡ በአዋጅ ቁጥር 80/1968 መሰረት የከተማ መሬቶች ባለዞታዎች ከሚከፍሉት የመሬት መተቀሚያ ኪራይ ውጪ የመሬቶቹ ባለይዞታ በመሆናቸው የሚከፍሉት የንብረት ታክስ የለም፡፡
በሌላ በኩል በአዋጅ ቁጥር 80/1968 መሰረት ታክስ የሚጣልባቸው ንብረቶች የከተማ ቤቶች ሲሆኑ ይህም ሁኔታ በሌሎች ሀገራት ካለው እና ቤቶችን ጨምሮ በሁሉንም አይነት ግንባታዎች ወይም ህንጻዎች ላይ ከሚጣለው የንብረት ታክስ አንጻር ሲታይ ውስንነት አለው፡፡

በሀገሪቱ ካሉት የንብረት ታክስ ህጎች ውስንነት በተጨማሪ ያሉትን ህጎች ለማስፈጸም የሚረዱ የመሰረታዊ ሁኔታዎች አለመሟላት ችግርም ይስተዋላል፡፡በዚህ ረገድ የንብረቶች የንበረቶች ዋጋ ተመን አንዱ እና ዋነኛው ነው፡፡ከላይ እንደመለከትነው የንብት ታክስ ዋጋን መሰረት ያደረገ (ad valorem) የታክስ አየነት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ታክስ የሚጣልባቸው ንብረቶች ዋጋ መታወቁ አስፈላጊነት አለው፡፡ የእነዚህ ንብረቶች ዋጋ በየግዜው መተመን እና ወቅታዊ ዋጋቸውን ማወቅም ለንብረት ታክስ ፍትሀዊነት እና ውጤታማነት ጉልህ ሚና አለው፡፡

በአሁኑ ግዜ በሀገራችን ያለውን የንብረቶችን ዋጋ አተማመን ስንመለከት የወቅታዊነት ችግር ይስተዋልባቸዋል፡፡ ለአብነትም ያህል በመዲናችን በአዲስ አበባ ያለውን የንብረቶች ዋጋ አተማመን ስንመለከት ይህ ስራ የተሰራው ከሶስስት አስርት አመታት በፊት እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡ ይህም የንብረቶቹን ወቅታዊ ዋጋ ከማሳወቅ እንዲሁም የንብረት ታክስን በፍተሀዊነትእና በውጤታማነት በመተግበር ረገድ ችግር መፍጠራቸው አያጠራጥርም፡፡ ይህንንም በአሁኑ ግዜ የንብረት ታክስ ለከተማ መስተዳድረሩ ከሚያስገኘው ገቢ መረዳት ይቻላል፡፡ በአሁኑ ግዜ በከተማ መስተዳድሩ ያለው የዚህ ታክስ ሽፋን ከአጠቃላይ የከተማ መስተዳድሩ ገቢ ከሁለት በመቶ ያነሰ ነው፡፡

ይህም በሌሎች ሀገራ ካለው እና እስከ መቶ ፐርሰንት ሽፋን የከተሞች ገቢ ከሚያስገኘው የንብረት ታክስ አንጻር በእጅጉ አነስተኛ ነው፡፡


የንብረት ታክስ አጣጣል በኢትዮጵያ

አዋጅ ቁጥር 80/1968 የከተማ መሬት ኪራይን እና የከተማ ቤቶችን ታክስ ወይም ግብርን አስመልክቶ የተደነገገ ሲሆን በዚህ አዋጅ አንቀጽ 5 መሰረት በከተሞች የሚገኙ ቤቶች ባለቤት የሆኑ ግለሰቦች፣ ቤተሰቦች፣ ድርጅቶች፣ ወይም ህብረት ስራ ማህበራት ባለቤት በሆኑበት ቤት ላይ ግብር ወይም ታክስ መክፈል እንዳለባቸው ይደነግጋል፡፡ ከዚህ አዋጅ በመቀጠል የወጣው አዋጅ ቁጥር 161/1972 በፊተኛው አዋጅ ላይ መሰረታዊ መሻሻል ላደረገ በመሆኑ ይኸው አዋጅ ቁጠር 80/1968 የንብረት ታክስን በዋናነት ይገዛል፡፡
በዚህ አዋጅ መሰረት በከተማ የሚገኙ ቤቶች ባለቤቶች ግብር ወይም ታክስ መክፈል የለባቸው ሲሆን ይህንን ታክስ ለማስላትም የቤቶቹ አመታዊ ኪራይ ለንብረቶቹ ዋጋ አተማመን እንደሚያገለግል ተመልክቷል፡፡

የንብረቶችን የኪራይ ተመን መሰረት በማድረግ የተለያየ ዋጋ ያላቸው ንብረቶች በተለያየ የታክስ የማስከፈያ ልክ (tax rate) ግብር እነዲጠልባቸው የሚደረግ ሲሆን ይህንን ዋጋ ከግምት ውስጥ በማስገባትም አነስተኛ የኪራይ ዋጋ ግምት ያላቸው መኖሪያ ቤቶች ከንብረት ታክስ ክፍያ ነጻ ይሆናሉ፡፡

ከንብረት ታክስ ነጻ የሚሆኑ ንብረቶች በአዋጅ ቁጥር 80/1968 ውስጥ የተዘረዘሩ ሲሆን እነሱም የሚከተሉት ናቸው፡፡
• መንገዶች አደባባዮች ፣ መዝናኛ አና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና መካነመቃብሮች
• የአምልኮ ስፍራዎች እና ግቢዎቻቸው ለትርፍ ያልተቋቋሙ ትምህርት ቤቶች እና ትምህርት ቤቶች
• የመንግስት በጀት የሚንቀሳቀሱ መንገስታዊ መስርያ ቤቶች
• አመታዊ የኪራይ ተመናቸው ከ300 ብር በታች የሆኑ መኖሪያ ቤቶች
እነዚህ ከንብረት ታክስ ክፍያ ነጻ የሆኑ ንብረቶችን አስመልክቶ ግልጽ መሆን የለበት ነገር ንብረቶችን ከታክስ ክፍያ ነጻ የማድረግ አሰራር ለታሰበለት አላማ ብቻ መዋል ያለበት አሰራር መሆኑን ነው፡፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ገዢ የሆነ ውሳኔ ወስነኗል፡፡በየሰ/መ/ቁ. 66474 ላይ እንደተወሰነው በአዋጅ ቁጠር 80/1968 መሰረት ከ ንብረት ታክስ ነጻ የሚሆኑት በዚሁ ህግ በግልጽ የተመለከቱት የንብረት አይነቶች እንጂ እነዚህን ንብረቶች ሽፋን
በማድረግ ሌሎች ንብረቶችን ከዚህ ታክስ ነጻ ማድረግ አይቻልም፡፡በሀገራችን ስላለው የንብረት ታክስ እናንተስ ምን ትላላችሁ?
497 views04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 07:07:05 የንብረት ታክስ ፍተሀዊ የታክስ አይነት ነውን?

የአንድ ታክስ አይነት ፍተሀዊነት የሚለካው የታክስ አየነቱ ተግባራዊ በሚየደርጋቸው የተለያዩ መርሆች እና አሰራሮች ነው፡፡ ከዚህም አንጻር የንብረት ታክስን ፍተሀዊ ሊያደርጉ የሚችሉ እና እንደየአገሮች ነባራዊ ሁኔታ ተገባራዊ ሊሆኑ የሚችሉ የተለያዩ መርሆች እና አሰራሮች አሉ፡፡
እነዚህ የተለዩ መርሆች እና አሰራሮች እንዳሉ ሆነው የንብረት ታክስን መሰረታዊ ጽንሰሀሳብ በመመልከት ይህ የታክስ አይነት ፍተሀዊ ነው ወይንስ አይደለም የሚለውን ማየት ይቻላል፡፡ ይህንንም ለማድረግ ይህንን የታከስ አይነት ከተጠቃሚነት መርህ (Benefit principle) እና የመክፈል አቅም መርህ (Ability to pay principle) አንጻር መመልከት አሰፈላጊ ነው፡፡እነዚህ ሁለት መርሆች ወይም ጽንሰሀሳቦች የአንድን የታክስ አይነት ፍተሀዊነት ለመለካት የሚገለግሉ ሲሆን የንብረት ታክስ ከእነዚህ መርሆች አንጻር ምን እንደሚመስል በአጭሩ እነደሚከተለው መመልከት ይችላል፡፡

በተጠቃሚነት መርህ ውስጥ ያለው መሰረታዊ ጽነሰሀሳብ እንደሚያስገነዝበው ታክስን መክፈል ያለባቸው ከሚከፈለው ታክስ ተጠቃሚ የሚሆኑ ሰዎች ናቸው፡፡ ይህም በሚሆንበት ጊዜ የታክስ ፍተሀዊነት ይሰፍናል፡፡ ይህ የሰጥቶ መቀበል መርህ ሁሉም የታክስ አይነቶች የሚከፈሉበትን ጠቅላላ ምክንያት የሚያሳይ ነው፡፡የአንድ ሀገር ነዋሪዎች ማንኛውንም ታክስ ሲከፍሉ ታከስን የሚሰበስበው አካል ማለትም መንግስት በሚሰበስበው ታክስ ለነዋሪዎች ማቅረብ የሚገባውን አገልግሎት ማቅረብ እንዲያስችለው ነው፡፡
ይህ ጽንሰሀሳብ ሁሉም የታክስ አይቶች የሚከፈሉበትን ምክንያት የሚያሳይ ቢሆንም በንብረት ታክስ ውስጥ ስንመለከተው ቀጥተኛ የሆነ ግንኙነት ያለው ነው፡፡
ከላይ እንደተመለከትነው የንብረት ታክስ በዋናነት የከተማ መስተዳድሮች የሚጥሉት የታክስ አይነት ነው፡፡ ከዚህ ታከስ የሚሰበሰበውም ገንዘብ ስራ ላይ የሚውለው በከተማ መስተዳድሮቹ ውስጥ ለሚካሄዱ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እና ህዝባዊ አገልግሎቶች አቅርቦት ነው፡፡ በመሆኑም የየከተማዎቹ ነዋሪዎች የሚከፍሉት የንብረት ታክስ በሚኖሩበት ከተማ ስራ ላይ ስለሚውል የተጠቃሚነት መርህ በተለየ ሁኔታ በንብረት ታክስ ውስጥ ፍተሀዊነትን ያረጋግጣል፡፡

የመክፈል አቅም መርህን በተመለከተ የንብረት ታክስ ያለው ገጽታ ምን ይመስላል የሚለውን ስንመለከት የንብረት ታክስ ከፋዮች እነማን ናቸው የሚለውን ማየት ይኖርብናል፡፡ የንብረት ታክስ የንብረቶችን ዋጋ መሰረት ያደረገ የታክስ አይነት እንደመሆኑ ከፍ ያለ ዋጋ ያላቸው ንብረቶች ባለቤት የሆኑ ሰዎች ከፍ ያለ የንብረት ታክስ የመክፈል ግዴታ ይኖርባቸዋል፡፡አነስተኛ ዋጋ ያላቸው ንብረቶች ባለቤት የሆኑ ሰዎችም አነስተኛ የሆነ የንብረት ታክስ የመክስል ግዴታ ስለሚኖርባቸው ይህ የታክስ አይነት የመክፈል አቅምን ያገናዘበ ፍተሀዊ የታክስ አይነት ነው ሊባል ይችላል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በአብዛኛዎቹ የንብረት ታክስ ስርአቶች ከታከስ ነጻ የሚደረጉ የንብረት አይነቶች አሉ፡፡ንብረቶችን ከታክስ ነጻ የማድረግ ስርአቶችም ተፈጻሚ ከሚሆኑበት ዋነኛ ሁኔታዎች ውስጥ የንብረቶቹን ባለቤቶች ታክስ የመክፈል አቅም ከግምት በማስገባት የሚደረገው አንዱ ነው፡፡ ይህም የንብረት ታክስን ፍተሀዊነት ለማስፈን ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡

የንብረት ታክስ ውጤታማ የታክስ አይነት ነውን?
የታክሶች ውጤታማነት የሚለካው ታክሶቹ የሚያስገኙትን ገቢ እና ታክሶቹን ለመሰብሰብ የሚያስፈልገውን የገንዘብ መጠን ከግምት በማስገባት ነው፡፡ በዚህም መሰረት ውጤታማ ታክስ የሚባሉት አነስተኛ ወጪ የሚያስፈልጋቸው እና በተነጻጻሪነት ከፍተኛ ገቢ የሚያስገኙ የታክስ አይነቶች ናቸው፡፡ በሌላ በኩል አነድ የታክስ አይነት በአጠቀላይ ኢኮኖሚ ውስጥ ከሚፈጥሩት የኢኮኖሚ ማዛባት(distortion) አንጻር ሊታይ ይችላል፡፡

የንብረት ታክስን ውጤታማነት ከሚያስገኘው ወጪ እና ከሚያስገኘው ገቢ አንጻር የሚወሰነው ታክሱ በሚጠቀመው የንብረት ዋጋ አሰላል ዘዴዎች እንዲሁም በሌሎች በታከስ ህጉ በተግባር ላይ በሚውሉ አሰራሮች ነው፡፡ የንብረት ታክስን ለመጠል ሲባል የንብረቶች ዋጋ በተለያዩ መንገዶች ሊተመን ይችላል፡፡ ከእነዚህም መንገዶች ውስጥ የንብረቶች የገበያ ዋጋ፣(capital value system) የንብረቶች የኪራይ ዋጋ (rental value system)፣ የመሬት ዋጋ (site value system) እና ንብረቶች ያላቸው የይዞታ ስፋት (area based system) በዋናነት በስራ ላይ ይውላሉ፡፡ እነዚህ የአተማመን ስልቶች የተለያየ ወጪ የሚያስወጡ ሲሆን እነደየሀገራት ነባራዊ ሁኔታ በስራ ላይ ይውላሉ፡፡

የንብረቶች የገበያ ዋጋን የሚከተለው የአተማመን ስልት ከፍተኛ ወጪ የሚያስወጣ በመሆኑ ዝቅተኛ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ በሚገኙ ሀገራት ተግባራዊ ለማድረግ አስቸጋሪ ነው፡፡ በሌላ በኩል የንብረቶችን የይዞታ ስፋትን መሰረት የሚየደርገው ስልት በአሰነስተኛ ወጪ ተጋባራዊ ሊሆን የሚችል ቢሆንም በቂ ገቢ ለማስገኘት ከፍተኛ የታክስ የማስከፈያ ልክ (tax rate) የሚያስፈልገው በመሆኑ ብዙውን ጊዜ ተመራጭ አይሆንም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ይህ የአተማመን ስልት በተለያየ የጥራት ደረጃ ላይ የሚገኙ ንብረቶችን በተመሳሳይ ሁኔታ የዋጋ ተመን ስለሚያወጣላቸው የታከስ ፍተሀዊነት ይጎድለዋል፡፡ በመሆኑም የንብረቶች የኪራይ ዋጋ እና ንብረቶች ያላቸው የይዞታ ስፋትን የሚጠቀሙት የአተማመን ስልቶች የንብረት ታክክን ውጤታማነት ከፍተሀዊነት ጋር ለማስፈን ያገለግላሉ፡፡

የንብረት ታክስን ውጤታማነት ታክስ በኢኮኖሚ ውስጥ ከሚያስከትለው መዛባት አንጽር ስንመለከት የንብረት ታክስ ይልቁንም የመሮት ዋጋ የተካተተበት የንብረት ታክስ በገበያውስጥ የሚፈጥረው መዛባት አነስተኛ በመሆኑ ውጤታማ የታክስ አይነት ነው ሊባል ይችላል፡፡ ይህም የሚሆንበት ዋነና ምክንያት በዚህ የታክስ አይነት መጣል የተነሳ ታክስ ከፋዮች ወይም የንብረት ባለቤቶች ከንብረት ባለቤትነታቸው ጋር በተያያዘ ባህሪያቸውን ብዙም ስለማይቀይሩ ነው፡፡


የንብረት ታክስ በኢትዮጵያ

በአሁኑ ግዜ በሀገራችን ያለው የንብረት ታክስ በተለምዶ የጣሪያ እና ግብር በመባል የሚታወቅ ነው፡፡ በሀገራችን ያለውን የንብረት ታክስ የሚገዙ ዋና ዋና የህግ ድንጋጌዎች አራት አስርት አመታት ያስቆጠሩ ሲሆኑ በአሁኑ ጊዜ ያለው የንብረት ታክስ በዋናነት የሚመራው በአዋጅ ቁጥር 80/1968 ነው፡፡ይህ አዋጅ የከተማ መሬት ኪራይን እና የከተማ ቤቶችን ታክስ ወይም ግብርን አስመልክቶ የተደነገገ ሲሆን በዚህ አዋጅ አንቀጽ 5 መሰረት በከተሞች የሚገኙ ቤቶች ባለቤት የሆኑ ግለሰቦች፣ ቤተሰቦች፣ ድርጅቶች፣ ወይም ህብረት ስራ ማህበራት ባለቤት በሆኑበት ቤት ላይ ግብር ወይም ታክስ መክፈል እንዳለባቸው ይደነግጋል፡፡
ከአዋጅ ቁጥር 80/1968 እንደምንረዳው በሀገራችን ያለው የንብረት ታክስ በከተማ ቤቶች ላይ የተገደበ ነው፡፡ የንብረት ታክስን በሚጠቀሙ በሌሎች ሀገራት ይህ ታክስ ሰፊ ሽፋን ያለው ነው፡፡ በአብዛኛዎቹ ሀገራት የከተማ መሬቶች እና ህንጻዎች በመርህ ደረጃ የንብረት ታክስ የሚጣልባቸው ሲሆን የከተማ መሬቶች የንብረት ታክስ የሚጣልባቸው በተነጻጻሪነት ከፍ ያለ ታክስ ይጣልባቸዋል፡፡
436 views04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 07:06:29

የንብረት ታክስ ምንነት እና ባህሪያት

የንብረት ታክስን ምንነት በተመለከተ የተለያዩ እና አከራካሪ አመለካከቶች በመኖራቸው ወጥ እና ተመሳሳይ የሆነ ትርጉም ማስቀመጥ አስቸጋሪ ነው፡፡ ነገር ግን ይህንን የታክስ አይነት ተግባራዊ በሚየደርጉ አገሮች እና የዚህን የታክስ አይነት አጠቃላይ የህግ ፍልስፍና በመመልከት መሰረታዊ የሆኑ እና የታክስ ህግ ምንነትን ሊያሳዩ የሚችሉ የጋራ ትርጉሞችን ማስቀመጥ እንችላለን ፡፡
በአጠቃላይ የንብረት ታክስን ታሪክ ስንመለከት ይህ የታክስ አይነት የረጅም ግዜ ታሪክ ያለው ነው፡፡ ይህ የታክስ አይነት በተለያዩ አገራት ከ3000 አመታት በላይ ለሆነነ ግዜ አየተተገበረ ያለ ሲሆን ተግባራዊ የሚደረገውም ይዞታን መሰረት ባደረገ መልኩ ነው፡፡የዚህ ታክስ ከፋዎች የሚሆኑትም የንብረቶች ባለቤቶች ወይም ባለ ይዞትዎች ናቸው፡፡

ከሌሎች የታክስ አይነቶች ለምሳሌ ከ ተጨማሪ እሴት ታክስ እና ከገቢ ግብር በተለየ መልኩ ይህ የታክስ የሚጣለው ግብየትን መሰረት ባላደረገ መልኩ ነው ፡፡ ይህም በመሆኑ በተነጻጻሪንነት የማይቀያየር (static) የሆነነ ባህሪ ይኖረዋል፡፡በአንጻሩ እነደተጨማሪ እሴት ታክስ አይነት ያሉ ታክሶች በየግብየቱ ስለሚጣሉ የተለዋዋጭነት ባህሪ ይኖራቸዋል፡፡

የንብረት ታከስ የንብረቶችን ዋጋ መሰረት በማድረግ የሚጣል የታክስ አይነት መሆኑ ሌላኛው መለያው ሲሆን ከሌሎች ንብረቶች በተለየ መልኩ ይህ ታክስ በማየንቀሳቀሱ ንብረቶች (real properties) ላይ በአብዛኛው ተፈጻሚ ሚደረግ ነው፡፡ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች በመባል የሚታወቁት መሬት እና ህንጻዎች ሲሆኑ በእነዚህ ንብረቶች ላይ የንብረት ታክስ የሚጣልበት ሁኔታ እና ታክሱ የሚጣልበት መጠን እንደየአገራቱ የታክስ አጣጣል ስርአት የሚለያይ ነው፡፡

ከሌሎች የታክስ አይቶች ጋር ሲነጻር የንብረት ታክስ በቀላሉ በከፋዮች እይታ ውስጥ የሚገባ (visible) የታክስ አይነት ሲሆን ይህም ከአከፋፈል ስርአቱ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ለአብነት ያህል የገቢ ግብርን እና የሽያጭ ታክስን ስንመለከት የገቢ ግብር በመሰረታዊነት ከምንጩ ተቀናሽ በመደረግ የሚከፈል ሲሆን የሽያጭ የታክስ ደግሞ በየግዜው በሚደረጉ ግብይቶች በአነስተኛ መጠን የሚከፈል ነው፡፡ በአንጻሩ የንብረት ታክስ ከፋዮች የሚከፍሉትን ታክስ በቀጥታ ለታክስ ባለስልጣን የሚከፍሉ በመሆኑ እና ይህም አብዛኛውን ግዜ በአመት አንድ ጊዜ ስለሚከፈል በቀላሉ በእይታ ውስጥ የሚገባ ነው፡፡

ከዚህም በተጨማሪ የንብረት ታክስ በዋናነት የሚከፈለው የከተማ መስተዳድሮች የመሰረተ ልማት እና ሌሎች አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ በሚያቀርቡበት ግዜ የሚያስፈልጋቸውን ወጪ ለመሸፈን ነው፡፡ ከዚህ ታክስ የሚሰበው ገነዘብም ለዚህ አገልግሎቶች የሚውል በመሆኑ ታክስ ከፋዮች በአካቢያችው የሚገነቡትን የመሰረተልማት ግንባታዎች እና የሚቀርቡትን አገልግለቶች በመመልከት የከፈሉት ታክስ ለተገቢው አላማ መዋል አለመዋሉን መመልከት ይችላሉ፡፡
የንብረት ታክስ ጠቀሜታዎችበአጠቃላይ የንብረት ታክስ የታችኛው የአስተዳድር እርክን የሚያስፈልጉትን ወጪዎች ለመሸፈን የሚያገለግል ሲሆን የአብዛኛዎቹ አገራት ከተማ መስተዳድራት አብዛኛው ገቢያቸውን ከዚህ የታክስ አይነት ያገኛሉ፡፡ የዚህ ታክስ ገቢ ሽፋን ድርሻ በአደጉት አገራት እስከ 100% የሚደርስ ሲሆን ይህ የታክስ አይነት በታዳጊ አገራት ትኩረት ካለማግኘቱ ጋር ተያይዞ በከተማ መስተዳድሮች ያለው ድርሻ አነስተኛ ነው ፡፡

የንብረት ታክስ ከገጠር አካባቢዎች ይልቅ በከተሞች ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ ነው፡፡ የዚህ ታክስ አይነት ተቀሜታ በከተሞች አካባቢ ከፍተኛ የሆነበት ዋነኛ ምክንያቶች በከተሞች አካባቢ ካለው ከፍተኛ የመሬት ዋጋ እና በእነዚሁ አካባቢዎች ካለው የህንጻዎች ብዛት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የንብረት ታክስ በከተሞች የሚጣል የታክስ አይነት እነደሆነ ተደርጎ ይታሰባል፡፡

የንብረት ታክስ በአንድ በኩል የመስተዳድሮችን ራስን ማስተዳደርን ሲያጎለብት በሌላ በኩል መስተዳድሮች ለነዋሪዎቻቸው ያላቸውን ተጠያቂነት ያሳድጋል፡፡ ከንብረት ታክስ የሚሰበሰበው ገንዘብ መስተዳድሮቹ ለሚያቀርቧቸው አገልግሎቶች የሚውል በመሆኑ ከዚሁ ታክስ የሚሰበሰበው ገንዘብ መስተዳድሮቹ ለሚያቀርቡት አገልግሎት በቂ በሆነ ግዜ መስተዳድሮቹ በማዕከላዊ መንግስት ያላቸውን ጥገኝነት ይቀንሳል፡፡

ከንብረት ታክስ የሚሰበሰበው ገንዘብ ጠቅም ላይ የሚውልበት ሁኔታ በታክሱ ከፋዎች በቀላሉ በእየታ ውስጥ የሚገባ በመሆኑ መስተዳድሮች ለነዋሪዎቻቸው ያላቸውን ተጠያቂነት ይጎለብታል፡፡ የመስተዳድሮቹ ተጠያቂነት በሚያድግበት ግዜም ባለስልጣናት እንደሙስና ወደመሳሰሉ ህገወጥ ተግባራት አንዳይገቡ ያደርጋል፡፡

የንብረት ታክስ ጠቀሜታ ፍትሀዊ እና ውጤታማ የመሬት አስተዳደርን ከማስፈን አንጻርም ሊታይ ይችላል፡፡የመሬት አጠቃቀምን አስመልክቶ ሊከሰቱ ከሚችሉ አላስፈላጊ ነገሮች ወይም ተግባራት ውስጥ አንዱ የመሬት ዋጋ መጨመርን መጠባበቅ (land speculation) ነው፡፡ የመሬትን ዋጋ መጨመርን መጠባበቅ የሚከሰተው የመሬት ባለይዞታዎች በያዙት መሬት ላይ በቂ የሆነ ግንባታወይም ኢንቨስትመንት ሳያደርጉ በግዜ ቆይታ በያዙት መሬት ላይ የሚከሰተውን የመሬት ዋጋ ጭማሪ ለማግኘት በማሰብ መሬት ሲይዙ ነው፡፡ ይህንን ችግር ከመቅረፍ አኳያ የንብረት ታክስ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡

የንብረት ታክስ በተለይም በመሬት ላይ የሚጣል የንብረት ታክስ በሚኖርበት ግዜ መሬትን ሳያለሙ ዋጋው ይጨምራል በሚል እሳቤ መሬትን የመያዝ ሁኔታ (land speculation) ይቀንሳል፡፡ ይህም የሚሆነው የመሬት ባለይዞታዎች የያዙትን መሬት ሳያለሙ እና ከመሬቱ ጥቅም ሳያገኙ በመሬቱ ላይ ታክስ ብቻ እየከፈሉ ለመቆየት ኢኮኖሚያዊ ምክንያት ስለማይኖራቸው ነው፡፡ ከዚህም የተነሳ መሬትን በአግባቡ የሚያለሙ ሰዎች ብቻ የመሬት ባለይዞታ የሚሆኑበት ሁኔታ ይፈጠራል፡፡ ይህም ውጤታማ የመሬት አስተዳደር እንዲኖር ያደርጋል፡፡

መሬትን በአግባቡ የሚያለሙ ሰዎች ብቻ የመሬት ባለይዞታ በሚሆኑበት ግዜ ፍትሀዊ የመሬት ባለቤትነት ይፈጠራል፡፡የመሬት ዋጋ መጨመርን መጠባበቅ (land speculation) በሚስፋፋበት ግዜ የመሬት ዋጋ በእጅጉ ይንራል፡፡ ይህ የመሬት ዋጋ መጨመር በትክክለኛ ወይም ጤናም በሆነ ሁኔታ የሚመጣ ባለመሆኑ በኢኮኖሚ ውስጥ ኢ-ፍተሀዊነትን ይፈጠራል፡፡ በመሬት ላይ የሚጣል የንብረት ታክስ በሚኖርበት ግዜ መሬትን ለመያዝ ያለው ፍላጎት (demand) ስለሚቀንስ የመሬት ዋጋ ተመጣጣኝ ይሆናል፡፡ ይህም አብዛኛውን የህብረተሰብ ክፍል የመሬት ባለይዞታ እንዲሆን ስለሚያደርግ በመሬት ይዞታ ዙሪያ ፍተሀዊነትን ይፈጥራል፡፡


የንብረት ታክስ እና ጠቅላላ የታክስ መርሆች

ማንኛውም አይነት ታክስ በሚጣልበት ግዜ ሊከተላቸው የሚገቡ ጠቅላላ የታክስ መርሆች አሉ፡፡ አዳም ስሚዝ የተባለ ሊቅ wealth of nations በተባለ መጽፉ ላይ እንዳሰፈረው ውጤታማነት (efficiency)፣ ፍትሀዊነት (equitablity)፣ ቀላልነት (simplicity) እና አመቺነት (convenience) ዋነኛ የታክስ መርሆች ናቸው፡፡ አንደማንኛውም የታክስ አይነት የንብረት ታክስ አጣጣልን ከእነዚህ መርሆች አንጻር ማየት አስፈላጊ ነው፡፡ ከእነዚህም መርሆች ውስጥ ፍተሀዊነት እና ውጤታማነት በዚህ ጽሁፍ የሚዳሰሱ ይሆናል፡፡
347 views04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 07:06:10 ***
በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በንብረት ላይ የሚጣለውን ግብር ለመወሰን የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ የፌደሬሽን ምክር ቤት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አጽድቀውታል።

በንብረት ላይ የሚጣለውን ግብር ባለቤትነት ለመወሰን የፀደቀው ሀሳብ በሀገሪቱ ዘመናዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓትን ለመገንባትና ጠንካራ ኢኮኖሚ እንዲኖር ለማድረግ ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው ተብሏል።
እንደ ሀገር አራት መሰረታዊ ችግሮችን የሚፈታ ነው የተባለለት ውሳኔ በንብረት ላይ የሚጣለው ግብር ኢ-ፍትሀዊነትንና ሌብነትን ለመከላከል አቅም የሚፈጥር እንደሆነም ተጠቅሷል።
ውሳኔው በተጨማሪም የታክስ ስርዓቱን ለማስፋትና የከተሞችን አቅም ለማጠናከር ዕድል ያለው መሆኑም ተመልክቷል።

በፌደራል ፍ/ሕ ምርምር እና ሥልጠና ኢኒስቲቲዩት የንብረት ታክስ ምንነት እና ባሕርያት በሚል ርዕስ ከሶስት ዓመት በፊት ያጋራውን ጽሁፍ ለአጠቃላይ ግንዛቤ ከዚህ እንደሚከተለው አጋርተናችኋል ።
ፅሁፉ ረጅም ቢሆንም ጥሩ ግንዛቤ የሚሰጥ በመሆኑ በትዕግስት አንብቡት ።
336 views04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 07:02:52 ለሊዝ ፋይናንሲንግ ብድር ስታመለክቱ ቢዝነስ ፕላን ወይም የአዋጪነት ጥናት ብቻ አቅርባችሁ ሳይሆን ሙሉ አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችን ጭምር አያይዛችሁ መሆን ስላለበት ለማመልከት ስትመጡ ቀጥሎ በተቀመጠው ዝርዝር መሠረት አሟልታችሁ መሆን እንዳለበት እናሳውቃለን፡፡

የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ለማግኘት መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ዝርዝር (በስራ ላይ ያለው)

ክፍል አንድ፡- አስገዳጅ መስፈርቶች (Mandatory Requirements)
1.1 ማመልከቻ፡-
1.1.1 የሊዝ ማመልከቻ

የባንኩ የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት የሚፈልጉ አመልካቾች ጥያቄያቸውን የሊዝ መጠኑንና ሊገለገሉበት ያቀዱትን የካፒታል ዕቃዓይነት በመጥቀስ በጽሁፍ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
1.1.2 በባንኩ የተዘጋጀውን የሊዝ ማመልከቻ ቅጽ መሙላት ይኖርባቸዋል፡፡

1.2 ፈቃድ ( በስራ ላይ ያለ ድርጅት ከሆነ)
1.2.1 የንግድ ሥራ ፈቃድ
1.2.2 የዋና ምዝገባ የምስክር ወረቀት
1.2.3 የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር

1.3 መሬት /የማምረቻ ቦታ/
1.4 ዋጋ ማሳወቂያ ሰነድ /Pro-forma Invoice/

ለሊዝ አገልግሎት ለሚቀርብ ጥያቄ ከሶስት አስመጪ ወይንም አቅራቢ ድርጅቶች የተሟላ የዋጋ ማሳወቂያ ሰነድ መቅረብ ያለበት ሲሆን ለሊዝ አገልግሎት ለሚቀርብ ጥያቄ የአዋጭነት ጥናት ለማከናወን አመልካቹ አንድ የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ካቀረቡ በቂ ይሆናል፡፡

1.5 የተሳትፎ የምስክር ወረቀት፡- በባንኩ የተዘጋጀ ስልጠና የወሰደ መሆኑን የሚያረጋግጥ የተሳትፎ የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለበት፡፡

1.6 የንግድ ዕቅድ ወይም የአዋጭነት ጥናት ማቅረብ አለበት፡፡
1.7 የድርጅቱ /የግለሰቡ መዋጮ፡
1.7.1 ለስራ ማስኬጃ ወጪ መሸፈኛ የሚውል የ20% መዋጮ በጥሬ ገንዘብ የሊዝ ዕቃ ጥያቄ እንደተፈቀደ በባንኩ በሚከፈት ዝግ ሂሳብ ገቢ ለማድረግ ሰለመስማማታቸው በጽሁፍ ማረጋገጥ፡፡
1.7.2 የመዋጮ ገንዘብ አጠቃቀምን በተመለከተ ባንኩ በሚያስቀምጠው ዕቅድ መሠረት ስራ ላይ ለማዋል መስማማታቸው የጽሁፍ ማረጋገጫ፡፡
ክፍል ሁለት፡- እንደ አስፈላጊነቱ /እንደሁኔታው (Optional Requirements) ተያይዘው የሚቀርቡ ተጨማሪ ሰነዶች፡-
2.1 ውክልና (ስልጣን)
በሶስተኛ ወገን የሚቀርብ የሊዝ ፋይናንስ ጥያቄ /ማመልከቻ ከሆነ አግባብ ካለው አካል የተረጋገጠ የውክልና ማስረጃ ባላቸው ወኪሎች መቅረብ ይኖርበታል፡፡
2.2 የቅድመ ሥራ ታሪክ መዝገብ (Track Record)
2.2.1 ሊዝ ጥያቄአቅራቢው
በስራ ላይ የሚገኝ
አዲስ ስራ ጀማሪ
አመልካች በስራ ላይ ከሆነ ፡-
 የግብር ግዴታ ማስረጃ
 የሂሳብ መግለጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
2.2.2 የሂሳብ መግለጫ፡- ከሶስት ዓመት ያልበለጠ ጊዜያዊ /ያልተረጋገጠ የሂሳብ መግለጫ (Provisional Financial Statements) ወይም በተፈቀደላቸው የሂሳብ መርማሪዎች የታየ (የተጣራ) የሂሳብ መግለጫዎች (Audited Financial Stateme\ \nts) ማቅረብ አለበት፡፡ ነገር ግን አዲስ ሆኖ የንግድ ስራ ላይ ካልሆነ ግን የግብር ግዴታና የሂሳብ መግለጫ ማቅረብ አይመለከተውም፡፡
2.3 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ፡
አመልካች በግል ይዞታ ላይ የሚሰራ ከሆነ እንደ ኘሬጀክቱ ዓይነት እና ሁኔታ ከሚመለከተው አካል የማረጋገጫ ድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ አለበት፡፡
ነገር ግን የሚሰራው በመንግስት ማምረቻ ቦታ ላይ ከሆነ ተከራዩ ይህ የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ማስረጃ ማቅረብ አይገደድም ሆኖም የማምረቻ ቦታውን የገነባው የክልሉ መንግስት ተገቢውን የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ስራን ያከናውናል፡፡
428 views04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 17:25:28 Fully Funded Scholarships 2023/2024 For International Students (Master’s/PhD)

1. Oxford Pershing Square Scholarship
Closing: Jan 2023
https://lnkd.in/gijaMgqt
2. World Bank Scholarships Program
Closing: Jan 2023
https://lnkd.in/gwgEiawf
3. Danish Government Scholarship
Closing: Jan 2023
https://lnkd.in/ghyRUVeX
4. Swedish Institute for Global Professionals
Closing: Jan 2023
https://lnkd.in/gZ85NzXM
5. Eiffel Scholarship Program Of Excellence
Closing: Jan 2023
https://lnkd.in/g3fUVRyy
6. President’s Scholarship 2019-20 at The Imperial College London
Closing: Jan/Mar/May 2023
https://lnkd.in/gQguKeAq
7. Chalmers IPOET Scholarships
Closing: Jan 2023
https://lnkd.in/gFeHFbqP
8. Orange Tulip Scholarship
Closing: Feb 2023
https://lnkd.in/g7cUJAJj
9. Rotary Peace Fellowship
Closing: Feb 2023
https://lnkd.in/g_7BYKdg
10. Lund University Global Scholarship
Closing: Feb 2023
https://lnkd.in/gnJ2xAnv
11. Uppsala University IPK Scholarship & Uppsala University President’s Club Scholarship
Closing: Feb 2023
https://lnkd.in/g4KyNJdm
12. Manaaki New Zealand Scholarship
Closing: Mar 2023
https://lnkd.in/gD7EArh7
13. Erasmus Mundus Joint Masters scholarships
Closing: Mar 2023
https://lnkd.in/gK3KFe2n
14. Commonwealth Shared Scholarship
Closing: Mar 2023
https://lnkd.in/gdpxFtnc
15. Australia Awards Scholarships
Closing: Mar 2023
https://lnkd.in/gZHa4Q6Z
16. Government of Romania Scholarship
Closing: Mar 2023
https://lnkd.in/g-ebTZsj
17. Fulbright Vietnamese Student Scholarship Program
Closing: Apr 2023
https://lnkd.in/gJsfcDKf
18. British Council scholarships for women in STEM
Closing: Apr 2023
https://lnkd.in/g6_wNKkd
19. Harvard University MBA Scholarship
Closing: May 2023
https://lnkd.in/gHxCdswj
20. MEXT Scholarships
Closing: May 2023
https://lnkd.in/g89s7AjB
21. GREAT Scholarships
Closing: May 2023
https://lnkd.in/gsbZD_F5
22. Scholarships of the Government of the Slovak Republic
Closing: May 2023
https://lnkd.in/gbXzwAH4
23. The Ignacy Lukasiewicz Scholarship Programme – Poland
Closing: May 2023
https://lnkd.in/gaYyUbR3
24. Italian Government Scholarship
Closing: Jun 2023
https://lnkd.in/gR434_yx
25. Helmut-Schmidt-Programme PPGG
Closing: Jul 2023
https://lnkd.in/gn-nUuaE
26. Orange Knowledge Programme
Closing: Aug 2023
https://lnkd.in/gDZAhP7E
27. Hubert H. Humphrey Fellowship Program
Closing: Aug 2023*
https://lnkd.in/gEqDgJ45
28. DAAD Scholarship
Closing: Sep 2023
https://lnkd.in/gjNec6BU
29. Cambridge University Scholarships
Closing: Oct 2023
https://lnkd.in/gSQA98N9
30. Gates Cambridge Scholarship
Closing: Oct 2023
https://lnkd.in/gCB6nsJp
31. Graduate Research Scholarships
Closing: Oct 2023
https://lnkd.in/gS_-d4xM
32. Government of Ireland Postgraduate Scholarships
Closing: Oct 2023
https://lnkd.in/g6KM_Xjs
33. Chevening Scholarship
Closing: Nov 2023
https://lnkd.in/gHpybbQ9
34. Swiss Government Excellence Scholarships
Closing: Nov 2023
https://lnkd.in/gJBWQdKS
35. Canada Graduate Scholarships
Closing: Dec 2023
https://lnkd.in/gSWR2M29
689 views14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 08:57:56 According to Psychologists, there are four types of Intelligence:

1) Intelligence Quotient (IQ)
2) Emotional Quotient (EQ)
3) Social Quotient (SQ)
4) Adversity Quotient (AQ)

1. Intelligence Quotient (IQ): this is the measure of your level of comprehension. You need IQ to solve maths, memorize things, and recall lessons.

2. Emotional Quotient (EQ): this is the measure of your ability to maintain peace with others, keep to time, be responsible, be honest, respect boundaries, be humble, genuine and considerate.

3. Social Quotient (SQ): this is the measure of your ability to build a network of friends and maintain it over a long period of time.

People that have higher EQ and SQ tend to go farther in life than those with a high IQ but low EQ and SQ.
Most schools capitalize on improving IQ levels while EQ and SQ are played down.

A man of high IQ can end up being employed by a man of high EQ and SQ even though he has an average IQ.

Your EQ represents your Character, while your SQ represents your Charisma.

Give in to habits that will improve these three Qs, especially your EQ and SQ.

Now there is a 4th one, a new paradigm:

4. The Adversity Quotient (AQ): The measure of your ability to go through a rough patch in life, and come out of it without losing your mind.

When faced with troubles, AQ determines who will give up, who will abandon their family, and who will consider suicide.

Parents please expose your children to other areas of life than just Academics.

They should adore manual labour (never use work as a form of punishment), Sports and Arts.

Develop their IQ, as well as their EQ, SQ and AQ. They should become multifaceted human beings able to do things independently of their parents.

Finally, do not prepare the road for your children. Prepare your children for the road.
740 views05:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ