Get Mystery Box with random crypto!

🇪🇹 ኢትዮ Students

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiostudents — 🇪🇹 ኢትዮ Students
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiostudents — 🇪🇹 ኢትዮ Students
የሰርጥ አድራሻ: @ethiostudents
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 56.17K
የሰርጥ መግለጫ

Our Bot :
@EthioExamBot
Contact : @ethioexamsupport
Or
@Etssupport

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-02-13 13:12:07
አስደሳች ዜና :
12ኛ ክፍል መልቀቅያ ፈተና ውጤትዎን የሚያገኙበት ፣ በተለያዩ የፈተና ጥያቄዎች ላይ ልምምድ የሚያደርጉበት ፣ የቴሌግራም ቦት አግኝተናል ፡፡

ቦቱ የሚከተሉትን ያጠቃልላል
የፈተና ውጤቶች (2010,2011,2012,2013)
የ12ኛ ክፍል መልቀቅያ ፈተና (የሁሉም ዓመታት)
የማትሪክ ፈተና (የሁሉም ዓመታት)
የመንጃ ፍቃድ ፈተና
የመማሪያ መጽሐፍት (8-12, Bsc.,Msc,PhD)

እዚህ ጠቅ ያድርጉ እና ይጀምሩ

t.me/Ethioexambot?start=r2112886803
4.4K views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-13 07:10:44 #Update

የሬሚዲያል ፕሮግራም መቁረጫ ነጥብ ነገ ይፋ ይደረጋል።


በሬሚዲያል ፕሮግራም የሚካተቱ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ ነገ የካቲት 06/2015 ዓ.ም ይፋ ይደረጋል።

በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላስመዘገቡና የተሻለ ውጤት ካላቸው ተማሪዎች መካከል 100 ሺህ የሚሆኑት ተማሪዎች በሬሚዲያል ፕሮግራም እንደሚካተቱ መገለጹ ይታወቃል።

የሬሚዲያል ፕሮግራሙን ለአራት ወራት ከየካቲት 15 እስከ ሰኔ 15/2015 ዓ.ም ለመስጠት ታቅዷል።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
7.2K views04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-13 07:06:07 #Update

የዩኒቨርሲቲዎች ምደባ ይፋ ተደርጓል።


በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ ተማሪዎች የተመደባችሁበትን ዩኒቨርሲቲ በተከታዮቹ አማራጮች ማየት ትችላላች

Website:  https://result.ethernet.edu.et

SMS: 9444

Telegram bot: @moestudentbot

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
6.9K views04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-12 15:20:47
ቱርካዊው ወጣት ህይወትን እና ጊዜያዊ ደስታን ጠቅለል አድርጎ እንዲ ገልጿል..!

ከቀናት በፊት ቤት ያከራየኝ ሰው ኪራይ ከሚገባው በላይ ጨምሮብኛ መክፈል ስላልቻልኩ ከቤቱ አባረረኝ፣ ካባረረኝ ከጥቂት ቀናት በኋላ የመሬት መንቀጥቀጡ ተከሰተ ታዲያ ዛሬ በመጠለያ ድንኳን ውስጥ አብረን እሳት እየሞቅን ነው ይላል ..!

Via Hijra Tube

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
4.7K viewsedited  12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-12 13:28:29 “የዩኒቨርስቲ ምደባ ከዛሬ ከየካቲት 05/2015 እኩለ ሌሊት ጀምሮ ይፋ ይደረጋል!” ትምህርት ሚኒስቴር

በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለመከታተል ላመለከታችሁ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ከየካቲት 05/2015 እኩለ ሌሊት ጀምሮ ይፋ ይደረጋል።

ስለሆነም ተማሪዎች ከታች በተገለጹት አማራጮች የተመደባችሁበትን ተቋም ማወቅ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ከየካቲት 15/2015 ዓ.ም ድረስ ተገቢዉን ዝግጅት አድርገው የመጀመሪያ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የቅበላ መርሃ ግብር የሚያሳዉቁ በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊዉን ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትቆዩ እናሳስባለን፡፡

የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች

Website:  https://result.ethernet.edu.et

SMS: 9444

Telegram bot: @moestudentbot

ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችሁ ማንኛውም ጥያቄ

result.ethernet.edu.et   ላይ በመግባት Complaint

የሚለውን በመጫን ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ምንም አይነት ጥያቄም ሆነ ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
969 views10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 12:30:38
በቱርክ እና በሶሪያ በተከሰተው ርዕደ መሬት የሟቾች ቁጥር ከ4 ሺህ 800 በላይ ደረሰ

በቱርክ እና በሶሪያ እና አካባቢው በተከሰተው ርዕደ መሬት የሟቾች ቁጥር ከ4 ሺህ 800 በላይ መድረሱን የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን እየዘገቡ ነው።

የዓለም ጤና ድርጅት በበኩሉ የሟቾች ቁጥር ከ20 ሺህ ሊሻገር ይችላል ማለቱን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል።

በቱርክ ብቻ ቢያንስ 3 ሺህ 381 ሰዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ የአደጋ እና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከል ባለሥልጣን አስታውቋል።

በአደጋው 13 ሺህ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱንም ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ጭምሮ ገልጿል።

በሶሪያም እንዲሁ እስካሁን ቢያንስ 1 ሺህ 444 ሰዎች ሲሞቱ 3 ሺህ 500 ያህሉ መቁሰላቸውን የደማስቆ መንግሥት እና የነፍስ አድን ሠራተኞች ገልጸዋል።

በርዕደ መሬቱ ከሞቱት እና ጉዳት ከደረሰባቸው በተጨማሪ ከፍተኛ የመሠረተ ልማት ውድመት ማጋጠሙም የዓለም መገናኛ ብዙኃን እየዘገቡ ነው።

የቱርኩ ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን፣ ርዕደ መሬቱን “ታሪካዊ አደጋ” ብለውታል።

አሜሪካን ጨምሮ የተለያዩ የዓለም ሀገራት ለቱርክ የአደጋ ጊዜ ድጋፍ ለማድረግ ቃል እየገቡ ሲሆን ቻይና ከወዲሁ 6 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ እንደምታደርግ ገልጻለች።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
6.0K views09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 14:24:12
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀዋሳ ከተማ ያስገነባውን የአቪዬሽን ማሰልጠኛ ማዕከል አስመርቋል።

ለማሰልጠኛ ተቋሙ ግንባታ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉ ተገልጿል።

የስልጠና ማዕከሉ 320 ተማሪዎችን ለማስተናገድ የሚያስችሉ የመማሪያ፣ የማደሪያ እና የመመገቢያ ክፍሎች አሉት ተብሏል።

በሀዋሳ የተመረቀው ማዕከል በአዲስ አበባ ካለው የአቪዬሽን ማዕከል ቀጥሎ ሁለተኛው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማሰልጠኛ ማዕከል መሆኑ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ስልጠና ይሰጣል።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
5.2K viewsedited  11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-01 09:13:24
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር፤ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ50% በታች ያመጡና በዩቨርሲቱ የቅበላ አቅም " ዕጩ የመጀመሪያ አመት ተማሪዎች " በዕጩነት ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡበትን ነጥብ ከ10 እስከ 15 ቀናት ውስጥ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ለፋና ብሮድካስት በሰጡት ቃለ ምልልስ ፤ " ዕጩ የመጀመሪያ አመት ተማሪዎች " በዕጩነት ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡበትን ነጥብ በጥቂት ቀናት ለማሳወቅ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ፤ " 10 ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ይሄንን ለህዝቡ ይፋ እናደርጋለን።  በ10 ቀን ውስጥ የትኞቹ ተማሪዎች ዕጩ በመንግስት ተቋማት ሄደው እንደ ስኮላርሺፕ ተማሪ ዶርም ይዘው ምግብ ቀርቦላቸው በቅተው ለሚቀጥለው ዓመት ፌሬሽ ማን የመሆን ዕድል ይሰጣቸዋል፤ ሌሎች ደግሞ በሌሎች አማራጮች ይማራሉ የሚለውን ጉዳይ ቢገፋ በ10 ቀን ውስጥ ማወቅ አለብን በጣም ቢገፋ በ15 ቀን ውስጥ ማወቅ አለብን " ብለዋል።

" ዕጩ የመጀመሪያ አመት ተማሪዎች " ዩኒቨርሲቲ እንዲገቡ ተደርጎ ራሳቸውን የሚያበቃቸውን ትምህርት ተከታትለው በሚቀጥለው ዓመት የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች በመሆን ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ለማድረግ ነው የትምህርት ሚኒስቴር አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ የታወቀው።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
7.6K views06:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-29 15:00:56
ምን ያህል ተማሪዎች በማጠናከሪያ ፕሮግራም ወደ ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ?

በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 896,520 ተማሪዎች መካከል 29,909 ተማሪዎች ብቻ በቀጥታ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደሚገቡ የትምህርት ሚኒስቴር መግለጹ ይታወቃል።

የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላስመዘገቡና የተሻለ ውጤት ካመጡ ተማሪዎች መካከል 100 ሺህ የሚሆኑት ተማሪዎች በደከሙባቸው የትምህርት አይነቶች በልዩ ክትትል እንዲማሩ ከተደረገ በኋላ ድጋሜ እንዲፈተኑ በማድረግ ሁለተኛ ዙር ዕድል እንደሚሰጣቸው የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

ይህም እንደ ዩኒቨርሲቲዎቹ የመቀበለ አቅምና የተማሪዎቹን ውጤት መሠረት አድርጎ በሚፈጸም የምልመላ መስፈርት የሚከናወን ነው።

ውጤት ያላመጡ ተማሪዎቹ በደከሙባቸው የትምህርት ዓይነቶች የማጠናከሪያ ድጋፍ ተደርጎላቸው በድጋሜ ፈተና እንዲወስዱ ተደርጎ የሚያልፉ ብቻ የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ይደረጋል፡፡

በፈተናው ወቅት ለሴቶች እና በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ለሚገኙ ተማሪዎች የመግቢያ ነጥብ ላይ እገዛ ይደረግላቸዋል ተብሏል፡፡ 

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
9.5K viewsedited  12:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 20:09:30
#አሪፍ_ውሳኔ

በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው በመላ ሀገሪቱ ከ600 በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን የዩኒቨርሲቲ ወጪ እንደሚሸፍን አማራ ባንክ አሳውቋል።

ባንኩ በመላ ሀገሪቱ ከ600 በላይ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው በወር 750 ብር እየከፈለ እንደሚያስተምር የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሄኖክ ከበደ ገልጸዋል።

ውሳኔው የባንኩ የማኀበረሰባዊ አገልግሎት አካል መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ጠቁመዋል።

በመላ ሀገሪቱ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር እውቅናና ሽልማት ይሰጣቸዋል መባሉ ይታወሳል።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
12.1K views17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ