Get Mystery Box with random crypto!

🇪🇹 ኢትዮ Students

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiostudents — 🇪🇹 ኢትዮ Students
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiostudents — 🇪🇹 ኢትዮ Students
የሰርጥ አድራሻ: @ethiostudents
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 56.80K
የሰርጥ መግለጫ

Our Bot :
@EthioExamBot
Contact : @ethioexamsupport
Or
@Etssupport

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-03-21 12:41:14
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በአንድ አካል ሁለት ጭንቅላት ያላቸው ልጆች ተወለዱ

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በንግሥት እሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮንፕረሲቪ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአንድ አካል ጭንቅላታቸው የተያያዙ መንታ ልጆች አንዲት እናት መገላገሏን የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር አዳነ ደስታ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡

በትላንትናው እለት ከምሽቱ 3፡30 ገደማ የወለደችው እናት እድሜዋ 40 ዓመት ሲሆን የአምስት ልጆች እናት መሆኗ ተገልፆል፡፡

ጭንቅላታቸው ተጣብቆ የተወለዱት ህፃናቶቹ እና እናትየው በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ተብሏል

በሆስፒታሉ ቀዶ ጥገና ለማድረግ ከባድ እንደሆነ እና ወደ አዲስ አበባ ሪፈር እንደሚደረጉ ነገር ግን ቀዶ ጥገና ለማድረግ ከባድ መሆኑን  በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በንግሥት እሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮንፕረሲቨ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር አዳነ ደስታ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡

በሆስፒታሉ ከዚህ ቀደም ሁለት እና ሦስት መንትያ ልጆች ተወልደው ቢታወቅም ይህ ክስተት  የመጀመሪያ ነው ሲሉ ዶክተሩ ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በደምቢ ዶሎ ዩንቨርስቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ሁለት ጭንቅላት ያለላቸው ልጆች መወለዳቸው ይታወሳል፡፡

በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
13.2K views09:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 13:02:12
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአንድ ለሊት ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ኪሳራ ሳይደርስበት እንደቀረ ተገለፀ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መጋቢት 6, ለሊት የሞባይል ባንኪንግ ሲስተም ችግር ያጋጠመው ሲሆን የችግሩ መንስኤ በሞባይል አፕሊኬሽኑ update ምክንያት እንደሆነ ተገልጿል።

የሞባይል ባንኪንጉ ተጠቃሚዎች ገንዘብ በሚያዘዋውሩበት ጊዜ ከአካውንታቸው ተቀናሽ ባለማድረጉ ምክንያት ባንኩን ከፍተኛ ኪሳራ ላይ ሊጥል ችሏል።

በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎች አጋጣሚውን በመጠቀም በነፃ ወደ ሌሎች ባንኮች ገንዘብ ሲያዘዋውሩ አድረዋል።

ይህ ዜና እስከተሰራበት ጊዜ ድረስ የዚህ ባንክ የሞባይል ባንኪንግ ሲስተም አገልግሎት መስጠት ያቆመ ሲሆን ባንኩ የደረሰውን ችግር ወደነበረበት ለመመለስ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
13.5K viewsedited  10:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-23 20:07:14
"ሰውን እኩል በማታይ ሀገር ውስጥ መኖር አልፈልግም" ያለው የሜድስን ተማሪ ከሞት ተርፏል

እምሩ ሙስጠፋ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ የሜዲስን ተማሪ ሲሆን በማህበራዊ ትስስር ገፁ "ቤተሰቦቼን አደራ፣ እኔ ሰውን እኩል በማታይ ሀገር ውስጥ መኖር አልፈልግም፣ እኔ መኖር እፈልጋለው መኖር ግን አልተፈቀደልኝም፣ ባልፈጠር ይሻለኝ ነበር ባልፈጠር እኔንም ቤተሰቤንም አላስቸግርም" በማለት ራሱን እንደሚያጠፋ ከገለፀ በኋላ በጓደኞቹ፣ በፖሊስ እና በዩኒቨርሲቲው ጥረት ራሱ ላይ ጉዳት ሳያደርስ ተይዟል። ቤተሰብ እስኪመጣ በነቀምት ከተማ ፖሊስ እንደሚቆይ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ሃሰን ዩሱፍ (PHD) ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
12.6K viewsedited  17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-20 12:14:08 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአገልግሎት መቋረጥ እንዳጋጠመው ገለፀ በባንኩ መረጃ ማስተላለፊያ የፋይበር ኦፕቲክስ ገመድ ላይ በደረሰ ጉዳት በባንኩ አገልግሎቶች ላይ ማለትም በቅርንጫፎች፥ በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ በሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሟል። አገልግሎቱን መልሶ ለማስጀመር ከሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት በከፍተኛ እርብርብ እየተሰራ ያለው ባንኩ ለተፈጠረው…
12.6K views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-20 10:53:22 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአገልግሎት መቋረጥ እንዳጋጠመው ገለፀ

በባንኩ መረጃ ማስተላለፊያ የፋይበር ኦፕቲክስ ገመድ ላይ በደረሰ ጉዳት በባንኩ አገልግሎቶች ላይ ማለትም በቅርንጫፎች፥ በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ በሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሟል።

አገልግሎቱን መልሶ ለማስጀመር ከሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት በከፍተኛ እርብርብ እየተሰራ ያለው ባንኩ ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቋል።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
12.8K views07:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-19 20:30:59
ኢየሱስ ወደ ኢትዮጲያ መልዕክት ልኳል፦ Pastor Tee

አንድ ዓመት ብቻ ነው የቀራቹም ብሏል

የጌታ ታናሽ ወንድም ነኝ ,እናቴ ማርያም ናት አባቴ ዮሴፍ ነው ሲል የሰነበተው ኬንያዊ ናይሮቢ እና ዋንጅራ ከተሰኙት ሁለት የኬንያ ከተሞች ተልዕኮዬን ጨርሼ አዲስ አበባ ልመጣ ነውም ብሏል

ይህ ኬንያዊ ከኢየሱስ ለኢትዮጲያዊያን መልዕክት ይዤያለው ያለ ሲሆን ፤ይህንንም መልዕክት በቀጣይ ወር ይዞ እንደሚቀርብና እስከዛው ግን ምዕመኑ ፀሎት እንዲያደርግ አሳስባለው ሲል በx ገፁ አጋርቷል።

ከዚህም በተጨማሪ ኢየሱስ በቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት ማለትም 2025 ማርች ወር ላይ ወደ ዓለም እንደሚመጣ'ና የዓለም ፍፃሜም እንደሚያደርግ
ገልጿል።

ከዚያህ በፊት ግን አንድ ዓመት ብቻ ለቀራቸው ሀበሾች መልዕክት አድርስ ተብያለው ብሏል።


@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
12.6K viewsedited  17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-30 21:31:08
ከዓለማችን ትልቁ መርከብ አንዱ ወደ ካሪቢያን ደሴቶች ጉዞ ጀምሯል።

መርከቡ ከታይታኒክ መርከብ በ5 እጥፍ የሚበልጥ ሲሆን ዋጋውም 2 ቢሊዮን ዶላር ነው።

7,600 መንገደኞችን የሚያስተናግድ ሲሆን 20 ጋቢናዎች ፣ ከ40 በላይ ሬስቶራንቶች፣ ካፌዎችና ቡና ቤቶች፣ ሞቃታማ ዕፅዋት ያሉት መናፈሻ፣ ቲያትር ቤተረ ፣ የስፖርት ሜዳዎች፣ የውሃ ፓርክ አሉት።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
14.8K viewsedited  18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-28 13:23:06
ጋዜጠኘ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) የራሱን ህይወት ማጥፋቱ ተረጋገጠ
__

ባሳለፍነው ሳምንት በሞት ያጣነው ተወዳጀ ጋዜጠኘ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ራሱን በገመድ አንቆ ህይወቱን እንዳጠፋ ኢትዮጲካሊንክ የሬዲዮ ኘሮግራም ዘገበ።

የዛሬ 6 ወር ገደማ ስኳር ህመም ያለበት ይህ ጀግና ሰው ገነን አንድ እግሩን ይቆረጣል ከዛ በኅላ ህይወት እንዳስጠላው ና ወዲህ ወዲያ ሲል ባለቤቱ እሷ መኪና እየነዳች እንደምታደርሰው ኢትዮጲካሊንክ አሳውቆ አንድ ቀን ግን ባለቤቱን ግዬን ሆቴል ስራ አለብኝ አድርሺኝ ብሏት አድርሳው ወደ ቤት ብትመለስም እሱ ግን ወደ ሌላ ቦታ በመሄድ ስልኩን በማጥፋት ሆቴል ይዞ ተደብቆ ትንሽ ቀናትን ቆይቷል::

ከዛ ግን ለጋዜጠኛ ሰይድ ኪያር ደውሎ ያለበትን ቦታ ነግሮት ሰይድም ወዲያው መጥቶ ስኳሩ በጣም እንደወረደና ባለቤቱ ጋር ደውሎ ስኳሩ በጣም ወርዷል ሲላት ባለቤቱም " በቃ ሚሪንዳ " ይጠጣበት ብላ እንደመለሰች ከዛ ግን ሄዳ እንኳን እንዳላየችው ታውቋል::

ብቻውን እዛ ክፍል ውስጥ የከረመው ይህ ታላቅ ሰው ገነነ ምን እንደሆነ ለምን እንደዚህ ውሳኔ እንደወሰነ ባይታወቅም ራሱን በገመድ አንቆ እንደገለ በምርምራ ታውቋል።

በጣም የሚያሳዝነው ግን ባለቤቱ ሞቱን ስትሰማ ወደ አረፈበት ሆቴል በመሄድ ለፖሊስ መናገር ና ማሳወቅ ሲገባት ሬሳውን ወደ ቤቷ አምጥታ ስታለቅስ የጎረቤት ሰዎች ለፖሊስ አመልክቺ እንጂ ብለው ሲጠይቋት ለፖሊስ ያመለከተች ሲሆን ፖሊስም እንዴትት የሞተ ሰውን አስክሬን ለፖሊስ መናገር ና ማሳወቅ ሲጋባሽ አስክሬኑን ይዘሽ ወደ መኖሪያ ቤትሽ ትሄጃለሽ ብሎ አንድ ቀን እስር ቤት አውሏት እንደነበር ኢትዮጲካሊንክ ዘግቧል።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
13.6K viewsedited  10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-25 20:50:43
#ኢትዮጵያ

በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ዘንድሮ በመላ ሀገሪቱ የ " ኬጂ " ተማሪዎች እንግሊዝኛ ቋንቋ እየተማሩ አይደለም።

የመዋዕለ ህጻናት ተማሪዎች " ኤ፣ ቢ፣ ሲ፣ ዲ… " ን በዜማ መቁጠር፣ " ኤ ፎር አፕል፣ ቢ ፎር ቦል… " እያሉ ቃላት መመሥረትም አቁመዋል።

ከዚህ ዓመት ጀምሮ " ስፖክን ኢንግሊሽ " እና " ኢንግሊሽ ሊትሬቸር " ከ " ኬጂ " ተማሪዎች የትምህርት ዓይነቶች ውስጥ ተሰርዘዋል።

እንደ ቀድሞው በአማርኛ ሂሳብ፤ በእንግሊዝኛ " ማትስ " እያሉ የቁጥሮችን አጠራር በሁለት ቋንቋ መሸምደድም ቀርቷል።

የዘንድሮ የ " ኬጂ " ተማሪዎች ለአካባቢ ሳይንስ እና ለ " ጄኔራል ሳይንስ " ሁለት ደብተር አይዙም።

በአራት ዓመታቸው " ነርሰሪ " የሚገቡት ህጻናት፣ በ6 ዓመታቸው ከ " ዩ ኬጂ " ሲመረቁ የሚያውቁት ብቸኛ የፊደል ገበታ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸውን እንዲሆን ተደርጓል።

ልጆችን እንግሊዝኛ በማስተማር ተመራጭ የሆኑት የግል መዋለ ህጻናት ከዚህ ዓመት ጀምሮ ሁሉንም ትምህርት የሚሰጡት በአካባቢው የአፍ መፍቻ ቋንቋ ብቻ ነው።

በአዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር አሠራር መሠረት ተማሪዎች እንግሊዝኛ ቋንቋን እንደ አንድ ትምህርት መማር የሚጀምሩት #አንደኛ_ክፍል ሲደርሱ ነው።

ከዚህ ዓመት ጀምሮ መተግበር የጀመረው ሥርዓተ ትምህርት ህጻናት የሚማሩትን ትምህርት በተለያዩ የትምህርት ዓይነቶች (ሰብጀክት) አይከፋፍልም።

የኬጂ ተማሪዎች እንደ ቀድሞው ሂሳብ፣ አማርኛ ወይም አካባቢ ሳይንስ የሚባሉ የትምህርት ዓይነቶች አይኖሯቸውም። በትምህርት አይነቶች ፋንታ ህጻናቱ የሚማሩት " ጭብጦችን " ነው።

ለምሳሌ፤ የመጀመሪያ ዓመት የመዋለ ህጻናት ተማሪዎች ስድስት ጭብጦችን ይማራሉ። ከእነዚህ ጭብጦች ውስጥ፦
* ስለ እኔ፣ ስለ ቤቴ እና ስለ ቤተሰቦቼ
* ትምህርት ቤቴ እና አካባቢዬ የሚሉት ይገኙበታል።

የኬጂ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ከሚማሯቸው ጭብጦች ውስጥ ደግሞ ፦
* ዋሊያ
* ህዋ
* ተክሎች እና መጓጓዣ ተጠቃሽ ናቸው።

በአዲሱ ካሪኩለም መሠረት ህጻናቱ እንደ ቀድሞው አብዛኛውን ጊዜያቸውን ክፍል ውስጥ ቁጭ ብለው ከሰሌዳ እና ከደብተር ጋር እንዲፋጠጡ አይደረግም።

ዘንድሮ የኬጂ ተማሪዎች የሚማሩባቸው ዋነኛ መንገዶች ጨዋታ፣ መዝሙር እና ተረት ናቸው።

በአዲሱ ካሪኩለም የኬጂ ተማሪዎች እንግሊዝኛ እንዲማሩ አይደርግም። በእንግሊዝኛ ምንም ነገር የለም። ሁሉም ነገር በአፍ መፍቻ ቋንቋ ይሰጣል።

የኬጂ ትምህርት ይዘት መቀነስ ያላስደሰታቸው ወላጆችም ያሉ ሲሆን ተማሪዎች ከአቅማቸው በታች እንዲማሩ እያደረገ ነው ብለዋል።

በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የግል ትምህርት ቤቶችም ከወላጆች ቅሬታ እየተቀበሉ መሆኑን የአዲስ አበባ የግል ትምህርት ቤቶች አሠሪዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት አቶ አበራ ጣሰው አሳውቀዋል።

የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ካሪኩለሙ በዝግጅት ላይ በነበረበት ወቅት የትምህርት ይዘቱ መቀነሱን እና የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት መውጣቱን በተመለከተ ማኅበሩ ተቃውሞ አስተያየት መስጠቱንም አስታውሰዋል።

የቅድመ አንደኛ ሥርዓተ ትምህርትን ካዘጋጁ ባለሙያዎች አንዱ የሆኑት ዶ/ር ታደሰ ጃለታ ፤ " ቤተሰብ ልጁ እንግሊዝኛ ከቻለ፣ ፊደል ከቆጠረ ወይም መደመር ከቻለ ተምሯል፣ አድጓል ብሎ ያስባል። በህጻናት ደረጃ ትምህርት እርሱ አይደለም " ብለዋል።

ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/BBC-AMAHRIC-01-24

Credit - #BBCAMAHRIC

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
13.2K views17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-16 15:28:21
እንደ ፎርብስ ዘገባ ከ180 ሚሊየን ዶላር በላይ ንብረት ያፈራው ፡ የ25 አመቱ ፈረንሳዊው የእግር ኳስ ኮከብ Kylian Mbappe አሁን የናፈቀው ወጣትነቱን በነጻነት መኖር ነው ።

ፈርምልኝ ፡ አብረን ፎቶ እንነሳ ሳይባል ፡ መጣ ሄደ ፡ በዚህ አለፈ ፡ ሳይባል በነጻነት መንቀሳቀስና ፡ መኖር ናፍቆታል ዝና እና እውቅናው ፡ ከምቾት ይልቅ ሰላሙን ነስቶታል ። " እንደ ማንም ሰው ዳቦ ቤት ሄጄ መግዛት እፈልጋለሁ ።

በምፈልገው ሬስቶራንት በፀጥታ መመገብ መቻል ናፍቆኛል ። ከጓደኞቼ ጋር ማንም መጥቶ ሳይረብሸኝ ፓርቲ ወጥቶ መዝናናት ፡ ይህንና ይህን መሰል ለሰው ቀላል የሚመስሉ ሰውኛ ነገሮችን ማድረግ ብፈልግም በዚህ ወቅት ይህ ነገር ለኔ ምኞት ብቻ ሆኗል ። በርግጥ ይህ ነገር ለአብዛኛዎቹ ሰወች ቀላል ወይም ተራ ነገሮች ቢሆኑም ለኔ ግን ምኞት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ። እናም እንደ ማንም ሰው መንቀሳቀስ የምችልበት ነገር ቢኖር ምንም አይነት ገንዘብ ብከፍል አይቆጨኝም ። ሲል ተናግሯል ።
......
የአንዱ ትልቅ ምኞት ፡ ለአንዱ ተራ ነገር ነው

Wasihune Tesfaye

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS
12.6K viewsedited  12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ