Get Mystery Box with random crypto!

HabeshaNet.

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiocoronainfo — HabeshaNet. H
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiocoronainfo — HabeshaNet.
የሰርጥ አድራሻ: @ethiocoronainfo
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 1.69K
የሰርጥ መግለጫ

We will provide Coronavirus updates about Ethiopia and the globe!
ይደግፉን | ያስተዋውቁን!
For any questions contact us http://t.me/EthioCoronavirusInfobot
https://www.youtube.com/c/TheNewEthiopiaTube?sub_confirmation=1

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2020-08-12 19:42:57
በኢትዮጵያ በአንድ ቀን 943 ሰዎች በኮቪድ-19 ተያዙ!

ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 14,540 የላብራቶሪ ምርመራ 943 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ23 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 338 ሰዎች አገግመዋል።

በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 25,118 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 463 ደርሷል ፤ እንዲሁም አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 11,034 ደርሰዋል።

HabeshaNet.
We will provide Coronavirus updates about Ethiopia and the globe!

ይደግፉን | ያስተዋውቁን!

For any questions contact us http://t.me/EthioCoronavirusInfobot

https://www.youtube.com/c/TheNewEthiopiaTube?sub_confirmation=1
https://t.me/ethiocoronainfo
1.0K viewsedited  16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-08-12 16:58:43
#ATTENTION

ነቀምቴ፣ አዳማ፣ ቢሾፍቱ፣ ሞጆ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ!

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 2,272 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ አንድ መቶ ስምንት (108) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

ከነዚህ መካከል፦

- 27 ከአዳማ
- 20 ከነቀምቴ
- 16 ከሞጆ
- 12 ከቢሾፍቱ
- 7 ከቡራዩ ይገኙበታል።

በኦሮሚያ ያለው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በእጅጉ እየጨመረ በመሆኑ ወረርሽኙ ከቁጥጥር ውጭ ወጥቶ ለመቆጣጠር ፈተናው እንዳይበረታ ጥንቃቄ ይደረግ።

HabeshaNet.
We will provide Coronavirus updates about Ethiopia and the globe!

ይደግፉን | ያስተዋውቁን!

For any questions contact us http://t.me/EthioCoronavirusInfobot

https://www.youtube.com/c/TheNewEthiopiaTube?sub_confirmation=1
https://t.me/ethiocoronainfo
1.2K viewsedited  13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-08-12 11:14:11
MASK AND COVID19
1.7K views08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-08-12 11:04:45
ኦነግ 6 አመራሮቹን ማገዱን አስታውቋል!

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር በፌስቡክ ገጹ ባወጣው መግለጫ አቶ አራርሶ ቢቂላ፣ አቶ ቶሌራ አደባና አቶ ቀጄላ መርዳሳን ጨምሮ ስድስት ከፍተኛ አመራሮቹን ለጊዜው ማገዱን አስታውቋል፡፡

በእግዱ ተካተዋል የተባሉ አመራሮች ነሐሴ 4 ቀን የድርጅቱ አመራሮች ጋዜጣዊ መግለጫ በሂልተን ሆቴል መስጠታቸው ይታወሳል፡፡

የድርጅቱ ሊቀ መንበር አቶ ዳዎድ ኢብሳ በበኩላቸው የተሰጠው መግለጫ የፓርቲያቸው እውቅና እንደሌለውና እርሳቸውም ስለ መግለጫው መረጃ እንደሌላቸው #ለቢቢሲ ተናግረው ነበር።

ከዚህም አስቀድሞ የፓርቲው ምክትል ሊቀ መንበር በአቶ አራርሶ ቢቂላ የተመራው ስብሰባ በኀላ በተነሱ ጉዳዮችና ልዩነቶች ላይ የፓርቲው የህግና ቁጥጥር ኮሚቴ እንዲያጣራ መወሰኑን አመራሮቹ ገልጸው ነበር።
890 views08:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-08-12 10:57:24
ችሎት!

እነ አቶ ጃዋር መሀመድ ዳኛ ይቀየርልን ሲሉ ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ተደረገ፡፡ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እነ አቶ ጃዋር ባቀረቡት አቤቱታ ላይ መርምሮ ብይን ሰጥቷል፡፡

በዚህም አቤቱታው በማስረጃ የተደገፈ አይደለም በሚል ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጎታል፡፡ ይህን ተከትሎም ችሎቱ ከዚህ በፊት በነበረው ዳኛ የሚታይ ይሆናል ተብሏል፡፡

በእነ አቶ ጃዋር መሃመድ መዝገብ አስራ አራት (14) ሰዎች ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡ ቢሆንም ዳዊት አብደታ የተባለው ተጠርጣሪ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ተጠርጥሮ ችሎት አልቀረበም፡፡

Via Tarik Adugna (FBC)
855 views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-08-12 10:56:41 የመከላከያ ሚኒስትሩ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸው ተነሱ።

የኦሮሚያ ክልልን በመወከል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል የነበሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ መገርሳ ከአባልነታቸው መነሳታቸው ተጠቁሟል።

ሰሞኑን ደግሞ ከኦሮሚያ የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው መታገዳቸው ይታወሳል።

ከአቶ ለማ በተጨማሪ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት የማኅበራዊ ጉዳይ አማካሪ ሆነው እያገለገሉ የነበሩት ወ/ሮ ጠይባ ሐሰንና እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የኦሮሚያ የመሬት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ የነበሩት ሚልኬሳ ሚደጋ (ዶ/ር) ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸው መነሳታቸውን ሪፖርተር ያገኘው መረጃ አመልክቷል።

ጨፌ ኦሮሚያ ክልሉን በመወከል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ ለማ፣ ወ/ሮ ጠይባና ሚልኬሳ (ዶ/ር) ከአባልነታቸው እንዲነሱ የወሰነው ከሁለት ሳምንት በፊት ባካሄደው ስብሰባ እንደሆነም ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ጨፌ ኦሮሚያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በተለያዩ ምክንያቶች ተጓድለዋል በሚል ምክንያት ሦስቱ አመራሮች በሌሎች እንዲተኩ ማድረጉን መረጃዎቹ አመልክተዋል

በመሆኑም ጨፌው በሦስቱ አመራሮች ምትክ አዲስ አባላትን መርጦ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ያስታወቀ ሲሆን፣ አቶ ለማን ተክተው የተመረጡትም በአሁኑ ወቅት የኦሮሚያ የብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና በጨፌ ኦሮሚያ የክልሉ መንግሥት ተጠሪ ሆነው እያገለገሉ የሚገኙት አቶ ፍቃዱ ተሰማ ናቸው።

በሌሎቹ ሁለት አባላት ምትክ ደግሞ የክልሉ ፓርቲ አደረጃጀት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሳዳት ነሻና አቶ አብዱል ሐኪም መመረጣቸው ታውቋል። የአገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር የሆኑት አቶ ለማ ሰሞኑን በተካሄደ የፓርቲ ስብሰባ ከኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው መታገዳቸውም ይፋ ሆኗል።

የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ በአዲስ አበባ በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት አዳራሽ ለሁለት ቀናት ያካሄደውን ስብስባ ነሐሴ 3 ቀን 2012 ዓ.ም. አጠናቆ ባወጣው መግለጫ፣ አቶ ለማን ጨምሮ ሦስቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ላልተወሰነ ጊዜ መታገዳቸውን አስታውቋል።

የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ለሁለት ቀናት የተካሄደውን ስብሰባና ውሳኔዎቹን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፣ ስብሰባው በፓርቲው ክልላዊ መዋቅር ላይ የተስተዋሉ ድክመቶች ላይ በስፋት ተወያይቶ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን የተመለከቱ ውሳኔዎችን እንዳሳለፈ ገልጸዋል።

በፓርቲው የክልል መዋቅር ከፍተኛ አመራሮች ላይ ባደረገው ግምገማም በማዕከላዊ አባልነት ሲያገለግሉ የነበሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ፣ ወ/ሮ ጠይባና ሚልኬሳ (ዶ/ር) ላልተወሰነ ጊዜ ከማዕከላዊ አባልነታቸው እንዲታገዱ መወሰኑን አስታውቀዋል።

አቶ ለማ መገርሳ ከማዕከላዊ አባልነታቸው እንዲታገዱ ምክንያት ከሆኑት ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ በፓርቲው የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባዎች ላይ በተደጋጋሚ አለመገኘታቸው መሆኑን አመልክተዋል።

በተጨማሪም የመከላከያ ሚኒስትር ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ በተጣሉባቸው መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ላይም በተደጋጋሚ አለመገኘታቸውን አቶ ፍቃዱ በምክንያትነት አንስተዋል።

Via Ethio Fm
949 viewsedited  07:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-08-12 10:53:00
ጅማ አባጅፋር እግር ኳስ ክለብ በፊፋ ተቀጣ። ለሶስት አመት ተጨዋች እንዳያስፈርም ታግዷል።
1.3K views07:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ