2022-08-24 00:36:06
#እንደምን_ቆያችሁ የEthio_fiction ተከታታዮች እኔ
#CR7 ነኝ
አንድ በእድሜው የጎለመሰ የሸገር ሰው እንዲህ አጫወተኝ ... ጉዳዩ የቀብሯ ቀን ምሽት የአንዲትን 15 አመት ታዳጊ ልጅ እሬሳ አውጥተው ሳጥኑን ይዘው ስለተሰወሩ ሰዎች ጠይቄው ያጫወተኝ ነበር።
"..በጣም ያሳዝናል ገና ማየቴ ነው:: ገርጂ አካባቢ በጣም አውቀዋለው ድሮ ድሮ እነ በልጌ, አህመድ. ጦይብ የሚባሉ ከኤርትራ ተፈናቅለው የመጡ ልጆች እሬሳ እየፈነቀሉ የሬሳ ሳጥን ይፖሽሩ ነበር::
ከዛም እሬሳውን እንደነበረ በማስቀመጥ ሳይታወቅ ሳጥኑን ለባለ ተራ ይሸጡታል:: የዚች ልጅ ግን በጣም ያስገርማል:: ከልጅቷ እድሜ ማነስና አንዳንድ ሁኔታዎች ጋር ተደምሮ አንድ የሆነ ነገር ልቤ ክፉኛ ጠርጥሯል ቢሆንም ግን ሳያረጋግጡ ወሬ እንዳይሆንብኝ ግን ፈራው ይቅር ብቻ::
ድምፅ ሰማን የሚሉት ነገር ግን የተለመደና በተለያዩ ቦታዎች የተደጋገመ ነገር ነው:: እንዲያውም በመቃብር አጠገብ የሚኖሩ ሰዎች ይሄ ነገር ለነሱ አዲስ አደለም::
ሁል ግዜ መቃብር አካባቢ ኡ ኡ ታና ዋይታ መስማት የተለመደ ነው:: የትኛው መቃብር እንደሚጮህ ግን ለማወቅ ያስቸግራል:: እኔም ገጥሞኛል::
ገርጂ ብዙ ትዝታ አለኝ:: ቤተክርስትያኗ ያኔ ባረንጓዴ ቢጫ ቀይ ያጌጠች ትንሽዬ ጎጆ ነበረች:: በኋላ ከአከባቢው ልወጣ ስል መስራት ጀመሩ መሰለኝ::
ብቻ እንደው ያ አካባቢ እንዴት እንደምወደው አትጠይቁኝ:: ከቤ/ክርስትያኑ ጀርባ ያለው መቃብር ካጠገቡ እልም ያለ ጫካ ነበር:: ፀሀይ ከረር ሲል ያቺ ዛፏ ስር አረፍ ያሉ እንደሆነ ፀጥ ካለው ጫካ ውስጥ የዛፎቹ ሽብሽቦና የወፎቹ ዝማሬ ብቻ ነበር የሚሰማው:: ብዙ ግዜ ታዲያ በጀርባዬ ትንጋልዬ ሰማዩን ስመለከተው አንድም ዳመና የሌለው ፍፁም ሰማያዊ ሆኖ ይታየኝ ነበር:: አይ ጦቢያ አገር እኮ ነው ከልቡ::
እና ይሄውላችሁ ሀይለኛ የሆነ የጠላ ሱስ ነበረብኝ ስንት ኪሎ ሜትር አቋርጠን ከሰፈር ልጆች ጋር፣ ያቺን ዳገቷን ቁልቁል ተንደርድረን ስናበቃ የኦሮሞዎቹ መንደር የረር ጭልጥ ብለን እንገባለን:: መቼም ዘመዶቼም አይደሉ ብቻ ኦሮምኛ በምናውቃት ስንተባተብ በሳቅ ይሞቱና ለጨዋታ አጠገባችን ይሰበሰባሉ:: ይወዱናል ከተማ የተገናኝን እንደሆነ ያኔ ገርጂ ኮንስትራክሽን ብቻ ስለነበረ ውሏችን እዛ ነውና ይሄንን ብሎኬት ከኛ ጋር እስኪበቃቸው አውርደው ሲጨርሱ ገርጂ ገበያ እህላቸውን ሸጠው እየዘፈኑ ሰፈራቸው ይከትማሉ:: ገርጂና የካ ሚካኤልም ታቦት ሲወጣ በጭፈራ መሬቱን ያንቀጠቅጡት ነበር::
ዘፈን ሲወዱ ለጉድ ነው:: የነሱን እርጎ የመሰለውን ጠላ ታዲያ ገልብጠን ገልብጠን ያን ዳገት እፍ ብለን እንወጣትና ጎርጊስ ጫካ ጋር ስንደርስ ትንፋሻችንን መለስ ለማድረግ ጫካዋ ውስጥ ገብተን አረፍ እንላለን:: ከዚያም ታክሲያችንን ይዘን ወደ ሰፈራችን እንመርሻለን::
ውይ የኔ ነገር የልጅቷን ነገር ትቼ የድሮ ትዝታ መጥቶ ብዙ ቀባጠርኩኝ:: እስቲ እንግዲህ ነብሷን ይማረው ብለን እንለፈዋ እንግዲህ ምን ይደረጋል::"
ለተከታታይ ጽሁፎች በሃሳብ አስተያየታችሁ አትርሱን
Inbox @Cr7_reunited
2.5K viewsCr 7, 21:36