Get Mystery Box with random crypto!

ብሩህ ወቅታዊ ዜና

የቴሌግራም ቻናል አርማ bruhdailynews — ብሩህ ወቅታዊ ዜና
የቴሌግራም ቻናል አርማ bruhdailynews — ብሩህ ወቅታዊ ዜና
የሰርጥ አድራሻ: @bruhdailynews
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.10K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-10-24 16:58:15 መቀሌ

የመቀሌዉ ኦፕሬሽን እንደቀጠለ ነው፣ ኩያ የተባለ መቀሌ አቅራቢያ የሚገኝ አዉሮፕላን ማረፊያ ዉጊያ እየተካሄደ ነው። በህወሓት ሰራዊት በኩል አብዛኛዉ እጅ እየሰጠ ነው። ነገር ግን ሰሜን ዕዝን የመቱ ወታደር የነበሩ እጅ አንሰጥም ብለዋል። እጅ እንስጥ የሚሉትን እየመቱዋቸዉ ከኋላ እየመቷቸው ነው። እጅ ለመስጠት የሚመጡትን መከላከያ ሰራዊት በቻለው መጠን ከለላ እያደረገ እየተቀበላቸው ነው። ትናንት አዲግራት ዙሪያ በርካታ ታጣቂዎች እጅ ሰጥተዋል።

@BruhDailyNews
5.6K views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 11:55:57
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቁልፍ የሚባሉ የትግራይ ከተሞችን መቆጣጠሩን ቀጥሏል።

ይህንን ሲያደርግም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በከተሞች ውጊያ ሳይደረግ የህወሓትን ወታደራዊ ዐቅም ለማሽመድመድ የሚያስችል ስልት ተጠቅሟል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ከሰብአዊ የርዳታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ሰብአዊ ርዳታ እንዲደርስ እየሠራ ይገኛል።

የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በእነዚህአካባቢዎች አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እንዲያፋጥኑ እያደረገ ነው።

ከየአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር በመነጋገር ሕዝባዊ አስተዳደር የሚቋቋምበትንና ማኅበራዊ አገልግሎቶች የሚጀምሩበትን መንገድ እያመቻቸ ይገኛል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአፍሪካ ኅብረት በኩል በደቡብ አፍሪካ በሚደረገው የሰላም ንግግር የሚሳተፍ ይሆናል።

አጋጣሚውንም የሰላም ንግግሩን ግጭቱን በሰላም ለመፍታት የሚቻልበት ዕድል አድርጎ ይመለከተዋል። በመከላከያ ኃይላችን መሥዋዕትነት እየተስተካከለ የመጣውን ሁኔታ የበለጠ ለማጠናከር ምቹ አጋጣሚ የሚፈጥሮ አድርጎ ይወስደዋል።

በሰላም ንግግሩ ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ የልኡካን ቡድን ዛሬ ጠዋት ወደ ደቡብ አፍሪካ አምርቷል።

ጥቅምት 14 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ

@BruhDailyNews
5.7K views08:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 11:52:10 ተደራዳሪዎቹ እነማን ናቸው?

ይህ ተደራዳሪ ቡድን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን የሚመራ ሲሆን ሰባት አባላትን ያካተተ ነው።

1/ አቶ ደመቀ መኮንን
2/ የፍትሕ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር)
3/ ብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ተመስገን ጥሩነህ
4/ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንት ጉዳዮች አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን
5/ የመከላከያ ሠራዊት የመረጃ ደኅንነት ኃላፊ ሌ/ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ
6/ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ጌታቸው ጀምበር (ዶ/ር)
7/በብልጽግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ማዕከል ዘርፍ ውስጥ በከፍተኛ ኃላፊነት እየሰሩ የሚገኙት አምባሳደር ሐሰን አብዱልቃድር ናቸው።

የትግራይ ኃይሎች በበኩላቸው ሁለት ተወካዮቻቸውን ለድርድር እንደሚልኩ ከዚህ ቀደም ገልጸው ነበር።

የመጀመሪያው የህወሓት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል እና የፓርቲው ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ የትግራይ ኃይሎችን ከሚመሩት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች መካከል አንዱ የሆኑት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳይ ናቸው።
ወደ ደቡብ አፍሪካ ግን ያቀኑት በቁጥር 9 መሆናቸዉንና ደቡብ አፍሪካ መድረሳቸዉን መረጃዎች አመላክተዋል፡፡
ኢትዮ ኤፍ ኤም

@BruhDailyNews
5.3K views08:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 09:15:26
ድርድር

ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል፣ ጌታቸው ረዳን እና ጄኔራል ፃድቃንን ጨምሮ ዘጠኝ የህወሓት ተደራዳሪ አባላት ደቡብ አፍሪካ ገብተዋል።

@BruhDailyNews
5.4K viewsedited  06:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-23 18:33:43
መቀሌ —

@BruhDailyNews
6.0K viewsedited  15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-23 12:13:45 መረጃ

ሽሬን፣አክሱምን እና አድዋን የተቆጣጠረው መከላከያ ሰራዊት ወደ አዲግራት እየተቃረበ ሲሆን፣በራያ ግንባር ወደ መሆኒ መስመር ባሉ አካባቢዎች ግን ውጊያው እንደቀጠለ ነው።

@BruhDailyNews
6.2K viewsedited  09:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 12:43:50 ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ይፈተናሉ ተብሎ ከተጠበቀው 17,114 የተፈተኑት 9,964(58%) ብቻ ናቸው

@BruhDailyNews
1.8K views09:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 11:15:46 ለ 13000 ቁጥር የተጠጋ ተማሪ በሙሉ ኮራጅ ነው ብሎ ብይን ሰጥቶ እነኚህን ተማሪዎች በሙሉ በ slanders and insult ከዚያ አለፍ ሲልም ከማህበረሰብ ስነ ልቦና ጋ ለማማያዝ የሚደረገው ጥረት በጣም የሚያሳዝን ነው።
ተማሪዎቹ ፈተና አንወስድም ብለው ማቋረጣቸው ስህተት የመሆኑን ያክል ወደዚህ ውሳኔ የገፋቸውን ሰበብ ከመርመርና ከማጥናት ይልቅ ለምን ፈተናውን አልኮረጅንም በሚል ሰበብ ነው ፈተና ያቋረጡት በሚል ስላቅ፣ስድብና ዘለፋ ጉዳዩን ከማጣጣል ይልቅ መንስኤውን ለማወቅ መጣርም ግዴታ ነበር።
በዚህ መካከል ፈተናውን ባቋረጡ ተማሪዎች ዙሪያ ችግሩን ከመውቀስና ልክ እንዳልሆነ ከመግለፅና ከመገሰፅ ባሻገር ዘለፋ፣ስድብ፣ማበሻቀጥና ራስን መስደብ የተስተዋለው በኛው ወገን መሆኑ በጣም አሳሳቢ ነው። ተማሪዎቹ ፈተናውን ላለመውሰድ ጥለው መውጣታቸውን መውቀስ የሞራል ልእልና ተደርጎ ሊወሰድ ቢችልም ከዚያ ባለፈ በተማሪዎች የማህበራዊ ስብእና ላይ ለመቀለድና ለመዝለፍ ይሄን ያክል መቁነጥነጥ የሞራል ልእልናን ማሳያ ልክም አይደለም።
በዚህ መካካል የአማራ ምሁራን ይሄን አጋጣሚ ተጠቅመው በአማራ ክልል የተጠቂነት ፖለቲካ (victimhood politics) ሰለባ
መሆንና ይህም አዋጪ አለመሆኑን ለማጉላት አንዱ በአንዱ ላይ ሆኖ ነጥብ ለማስቆጠር እየተላፉ ነው። ለነኚህ ሰዎች የምንጠይቀው ጥያቄ:–
> ይሄን ጉዳይ በመገንዘብ ለህዝብ የሚሆን ፖለቲካዊ መፍትሄ ከማምጣት ይልቅ በአማራ ህዝብ ላይ መከራ እያደረሱ ያሉ አካላቶችን የልብ ልብ እየሠጠ ያለው የብልፅግና መንግስት ስር አድራችሁ እናንተ ራሳችሁ ለአማራ ህዝብ መከራ መሳሪያ እያቀበላችሁ አይደለም ወይ?
> ህዝባችን የ victimhood politics ሰለባ ሆኗል ካላችሁ መፍትሄው ለህዝባችን የ victimhood politics ሰለባ መሆን አስተዋፅኦ እያደረገ ካለው መንግስት ስር መርመጥመጥ ነው መፍትሄው ወይስ የጠራ የፖለቲካ ሪፎርም ይዞ ህዝብን ማታገል?
> ልትነግሩን የፈለጋችሁት ከብልፅግና ጋ ወንድማማች በመሆን የአማራ ህዝብን መሰረታዊ የፖለቲካ ችግር መቅረፍና መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ይቻላል ከሆነ ብአዴን 27 አመት፣ አዴፓ በአምስት አመት ውስጥ ምንም የቀየሩት ነገር የለም። We can't count on you for the reason that you won't be any different than #ADP.

@BruhDailyNews
2.3K viewsedited  08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 08:06:16 13 ሺ ገደማ ተማሪ ፈተና አልፈተንም ለማለቱ እየተሰጠው ያለው ሰበብ "አትኮራረጅም" ስለተባለ ነው የሚል አሳፋሪ ብቻ ሳይሆን በአማራ ማህበረሰብ ላይ ትኩረት ያደረገ ነውረኛ ማሸማቀቂያን "አማራ ነኝ" ባዩም እየተቀባበለ በልጆቹ ላይ የፍርድ አለንጋውን ሲያሳርፍ ከርሟል።
ነገ ከነገ ወዲያ እነዚህ ልጆች በትክክል የተፈጠረውን ነገር መንገር የሚችሉበት አጋጣሚ ሲያገኙ እና በጅምላ ፈተናውን ለመቃወም የገፋቸውን አብረዋቸው ለፈተና የተቀመጡ ተማሪዎች ላይ የደረሰን ግፍ ሲናገሩ ዛሬ ለፍረጃ የፈጠነ አንደበት እና ጭንቅላት ነገ ወይ እንደለመዱት ልጆቹን "ሀሰተኞች" በማለት በቁስላቸው ላይ እንጨት ይሰዳሉ አልያም "አልሰማንም፣ አላየንም" ብለው ወደ ስንዴ ፖለቲካ ይዞራሉ።
የልጆቹ አንፈተንም ብለው ከአንድም አራት ዩኒቨርስቲ ውስጥ የተቋቋመ የፈተና ጣቢያን ጥለው መውጣትን ጉዳይ በተመለከተ ከቀን ወደ ቀን እየሰማን እየመጣን ያለው መረጃ በጣም አስደንጋጭም እጅግ አሳዛኝም ነው። መነሻው ምንም ይሁን ምን በእነዚህ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በተሰራጨ መረጃ መነሻነት ረብሻ እና ግርግር እንዲፈጠር ሆኗል። ይሄንንም ተከትሎ "በፀጥታ ሀይል" ተብዬዎቹ የተደበደቡ፣ የተደፈሩ እና አለፍ ሲልም የተገደሉ ተማሪዎች እንዳሉ እየሰማን ነው።
ከግቢ ውጪ ካለው ማህበረሰብ ጋር በምንም መንገድ መገናኘት እንዳይችል አድርገህ የያዝከውን ተማሪ ለየትኛውም ችግር መነሻ ነው ብሎ ከፊት ለማስቀመጥ መታተር ለጥፋቱ ቀጥተኛ ተጠያቂዎችን መከላከል ብሎም ለነገ ተመሳሳይ ችግር መንገድ መጥረግ ከሁሉም በላይ ደግሞ በድርጊታቸው መተባበር ነው።
ብርሀኑ ነጋ ሚዲያው በእጁ እንዲሆን ስለተደረገለት "አትኮርጁም" ስለተባሉ ነው ያለውን ሰምተናል። የልጆቹን ምክንያት ቀርቦ የጠየቀ አለ? መደፈር አለመደፈራቸውን ያረጋገጠ አለ? ከቤተሰብ ርቆ በዚህ መንገድ እንዲቀመጥ በተደረገ ታዳጊ አይምሮ አብሮት ለረጅም ጊዜ የተማረ ጓደኛው ተደብድቦ አለፍ ሲልም ሞቶ እያየ በየትኛው የስነልቦና ደረጃ ነው ቀጣይ ፈተና እንዲፈተን የሚጠበቅበት?
አዲስ አበባ ላይ የኦሮሚያን መዝሙር ተማሪ አልዘምርም ባንዲራውንም አልሰቅልም ለማለቱ ተጠያቂ የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር እና ምክትል ዳይሬክተሮች ናቸው በሚል መምህራንን ወደዘብጥያ መወርወር ተጀምሯል። ብርሀኑ ነጋን ስለዚህ ጉዳይ ብትጠይቁት ወይ አልሰማም አልያም ተማሪዎቹ አንዘምርም ያሉት መዝሙሩ ስለ ኩረጃ መጥፎነት ስለሚያስተምር ነው ከማለት አይመለስም
ፍትህ ምክንያታቸውን እንኳን ጠያቂ ላጡት ልጆች
@BruhDailyNews
2.7K viewsedited  05:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 21:37:51 $ሚልዮን ዶላሮች ለህወሃት

የግብፅ የመረጃ ተቋም ህወሓት ጦርነቱን እንዲገፋበትና ሦስተኛውን ዙር የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት እንዲያስተጓጉል 2 ሚልዮን ዶላር እንዳበረከተለትና በየ 45 ቀኑም 500 ሺ ዶላር ድጋፍ ሲያደርግለት እንደቆየ ምስጢራዊ ሰነዶች አጋለጡ

የግብፅ ጠቅላላ የመረጃ አገልግልት (General Intelligence Service- GIS) ህወሓት ጦርነቱን እንዲገፋበት እንዲሁም የህዳሴ ግድቡ 3ኛው ዙር የውሃ ሙሌት ከመጀመሩ በፊት የተለያዩ የሀገር ውስጥ ታጣቂ ኃይሎችን ስምሪት በመስጠት ሂደቱ እንዲስተጓጎል ከሀገሪቱ መንግሥት ተልዕኮ ተሰጥቶት ሲንቀሳቀስ እንደነበር ምስጢራዊ ሰነዶች አጋልጠዋል፡፡

የግብፅ ጠቅላላ የመረጃ አገልግልት (General Intelligence Service- GIS) ቦርድ ኃላፊ ብ/ጀነራል ሙታዝ ሙስጠፋ እና የአፍሪካ ላይዘን ኃላፊ ብ/ጀነራል ሙስጠፋ ማርዋን 2 ሚልዮን የአሜሪካ ዶላር በዲፕሎማሲያዊ ሂደት ወደ ሱዳን ካስገቡ በኋላ በካርቱም ለሚገኙ የሽብር ቡድኑ ተወካዮች ማስረከባቸውን የሚያጋልጡ የሰነድ ማስረጃዎች የተገኙ ሲሆን፤ ህወሓት ጦርነቱን እንዲገፋበትና በኢትዮጵያ አለመረጋጋቱ እንዲቀጥል በየ45 ቀኑ 500 ሺ የአሜሪካ ድላር ድጋፍ ሲደረግለት እንደነበረም ተረጋግጧል፡፡

ሱዳን እና ግብፅ ህወሓትን በመጠቀም የኢትዮጵያን ማዕከላዊ መንግሥትና አጠቃላይ ፖለቲካዊ ሁኔታውን ለመቀየር ያላቸውን ፍላጎት ለማሳካት ለአሸባሪ ቡድኑ የፋይናንስ፣ የሎጀስቲክ፣ የስልጠናና ሌሎችም የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡ በተለይም ግብፅ የሽብር ቡድኑ የመንግሥት ለውጥ ማምጣት ባይቻል እንኳን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎችን በማቀናጀት የህዳሴ ድግቡን የ3ኛው ዙር የውሃ ሙሌት እንዲያስተጓጉል ከፍተኛ ተስፋ አድርጋ የነበረ ሲሆን፤ የትግራይ ክልል ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮችም የገንዘብ ድጋፍ ከተደረገላቸው የተሰጣቸውን ተልዕኮ እንደሚያከናውኑ ተስማምተው እንደነበር ታውቋል፡፡
(ሱሌማን አብደላ)

@BruhDailyNews
2.9K views18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ