Get Mystery Box with random crypto!

Amna Tadesse Ministry

የቴሌግራም ቻናል አርማ amnatadesseministry — Amna Tadesse Ministry A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amnatadesseministry — Amna Tadesse Ministry
የሰርጥ አድራሻ: @amnatadesseministry
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 190
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም ጥያቄ
📲 0917771886
📲 0932195208
መደወል ትችላላችሁ ።

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-06 07:35:38 #ሩት

የአህዛብ ሴት/ሞዓባዊት

ሩት 1 (Ruth)
4፤ እነርሱም #ከሞዓባውያን ሴቶች ሚስት አገቡ፤ የአንዲቱ ስም ዖርፋ የሁለተኛይቱም ስም #ሩት ነበረ። በዚያም አሥር ዓመት ያህል ተቀመጡ።

ሞዓብ ደግሞ ሎጥ ከመጀመሪያ ሴት ልጁ የወለደው

ዘፍጥረት 19 (Genesis)
36፤ የሎጥም ሁለቱ ሴቶች ልጆች ከአባታቸው ፀነሱ።
37፤ #ታላቂቱም ወንድ ልጅ ወለደች ስሙንም #ሞዓብ ብላ ጠራችው፤ እርሱም እስከ ዛሬ #የሞዓባውያን አባት ነው።

ሞዓባዊያን የእስራኤልን መብዛትና ሰላማቸውን የማይፈልጉ ጠላቶች ናቸው ሰለዚህም #እርግማን ሊያደረጉባቸው ፈለጉ

ዘኍልቍ 22 (Numbers)
16-17፤ ወደ በለዓምም መጥተው፡— የሴፎር ልጅ ባላቅ፡— ክብርህን እጅግ ታላቅ አደርገዋለሁና፥ የተናገርኸውንም ሁሉ አደርግልሃለሁና እባክህ፥ ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ ምንም አይከልክልህ፤ እባክህ፥ ና፥ ይህን ሕዝብ #ርገምልኝ አለ፡ ብለው ነገሩት።

የተወዳዳችሁ ወንድሞቼ #ሩት አህዛብ ነች ይህ ብቻ አይደለም የምትኖረው በርግማን የሚታወቅ ንጉስ በሚገዛበት ከተማ ነው።

በአንድ አጋጣሚ ከይሁዳ ቤተልሔም ወጥተው ወደ ሞዓብ የሄዱ ቤተሰቦች ነበሩ

ሩት 1 (Ruth)
1፤ እንዲህም ሆነ፤ መሳፍንት ይፈርዱ በነበረ ጊዜ በአገሩ ላይ ራብ ሆነ። አንድ ሰውም ከሚስቱና ከሁለቱ ልጆቹ ጋር #በሞዓብ ምድር ሊቀመጥ #ከቤተ ልሔም #ይሁዳ ተነሥቶ ሄደ።
2፤ የሰውዮውም ስም አቤሜሌክ፥ የሚስቱም ስም ኑኃሚን፥ የሁለቱም ልጆች ስም መሐሎንና ኬሌዎን ነበረ፤ #የቤተ ልሔም #ይሁዳም የኤፍራታ ሰዎች ነበሩ። ወደ #ሞዓብም ምድር መጡ በዚያም ተቀመጡ።

እነዚህ ቤተሰቦች ይኖሩበት የነበረው ከተማ የምስጋና/ይሁዳ እንዲሁም የእንጀራ ቤት/የሚበላ ያለበት/ቤቴልሔም ከተማ ውስጥ ነበር።

እንግዲህ ከምስጋናና ሁሉ ከሞላበት ከተማ ወጥተው ወደ እርግማን ከተማ ሞዓብ ሲሂዱ ያተረፉት ሞት ነበር።

ሩት 1 (Ruth)
3፤ የኑኃሚንም ባል አቤሜሌክ #ሞተ፤ እርስዋና ሁለቱ ልጆችዋ ቀሩ።
5፤ መሐሎንና ኬሌዎንም ሁለቱ #ሞቱ፤ ሴቲቱም ከሁለቱ ልጆችዋና ከባልዋ ተለይታ ቀረች።

የሩት መጽሐፍ ስናነብ ኑኃሚን እና ሩት ከዚህ ሁሉ በኋላ ከሞዓብ ወደ ይሁዳ ቤተልሔም ለመምጣት ተነሱ ፤ ወዳጆቼ ወደ ቤቴልሔም ቢመጡ ኑኃሚን የቀድሞ ከተማዋ ነወ፣ቤተሰብ አላት፣ ረስት ነበራት ነገር ግን #ሩት ወገን አልነበረችም፣ ለእስራኤል ቤት የተሰጠው ተስፋ የላትም፣በእነርሱ ዘንድ ርስት የላትም ፣ለከተማው እንግዳ ነች/ባለገር አይደለችም

#ሩት በይሁዳ ርስትን ታገኝ ዘንድ ርስትን ሊሰጣት ፈቃደኛ የሚሆን ቤዛ/የሚቤዣት ያስፈልጋት ነበር ለዚህም ቦዔዝ ርስትን ይስጣት ዘንድ ሩት ሚስቱ አድርጎ ወሰዳት/ተቤⶳት።

አማኝ ልክ እንደ ሩት ነው።

ኤፌሶን 2 (Ephesians)
11፤ ስለዚህ እናንተ አስቀድሞ #በሥጋ #አሕዛብ የነበራችሁ፥ በሥጋ በእጅ የተገረዙ በተባሉት ያልተገረዙ የተባላችሁ፥ ይህን አስቡ፤
12፤ በዚያ ዘመን #ከእስራኤል #መንግሥት #ርቃችሁ #ለተስፋውም #ቃል #ኪዳን #እንግዶች ሆናችሁ በዚህም ዓለም #ተስፋን #አጥታችሁ #ከእግዚአብሔርም #ተለይታችሁ ያለ ክርስቶስ ነበራችሁ።
13፤ #አሁን #ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል።

ቆላስይስ 2 (Colossians)
13፤ እናንተም በበደላችሁና ሥጋችሁን ባለመገረዝ ሙታን በሆናችሁ ጊዜ፥ ከእርሱ ጋር ሕይወትን ሰጣችሁ። በደላችሁን ሁሉ ይቅር አላችሁ።

ወንድሞች እኛ በክርስቶስ ቤዛነት ከእርግማን ወደ በረከት ከአንዳች ወደ ሙሉነት ከሞት ወደ ህይወት ከጨለማ ወደ ብርሃን መለኮታው ልውውጥ ተደርጎልናል!!!

ጸጋ ይብዛላችሁ
ወንድማችው አምና ታደስ

https://t.me/joinchat/AAAAAE5Veg3GlEdndwaGyw
128 viewsAMNA TADESSE, 04:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 06:19:37 በክርስቶስ ደም ወደ እግዚአብሔር ቀርበናል።

ኤፌሶን 2 (Ephesians)
11፤ ስለዚህ እናንተ አስቀድሞ በሥጋ አሕዛብ የነበራችሁ፥ በሥጋ በእጅ የተገረዙ በተባሉት ያልተገረዙ የተባላችሁ፥ ይህን አስቡ፤
12፤ በዚያ ዘመን ከእስራኤል መንግሥት ርቃችሁ ለተስፋውም ቃል ኪዳን እንግዶች ሆናችሁ በዚህም ዓለም ተስፋን አጥታችሁ ከእግዚአብሔርም ተለይታችሁ ያለ ክርስቶስ ነበራችሁ።
13፤ #አሁን #ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ #በክርስቶስ #ደም ቀርባችኋል።
123 viewsAMNA TADESSE, 03:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-30 11:23:31 Watch ""ግን ሳላስበው" ዘማሪ ሩሐማ ተክሌ "Ruhama Tekle" New Protestant Amharic Live | አምልኮ ለንጉስ" on YouTube


152 viewsAMNA TADESSE, 08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-20 15:35:08 Can a Christian loss Salivation????


First, the term Christian must be defined. A “Christian” is not a person who has said a prayer or walked down an aisle or been raised in a Christian family. While each of these things can be a part of the Christian experience, they are not what makes a Christian. A Christian is a person who has fully trusted in Jesus Christ as the only Savior and therefore possesses the Holy Spirit (John 3:16; Acts 16:31; Ephesians 2:8–9).

So, with this definition in mind, can a Christian lose salvation? It’s a crucially important question. Perhaps the best way to answer it is to examine what the Bible says occurs at salvation and to study what losing salvation would entail:

A Christian is a new creation. “Therefore, if anyone is in Christ, he is a new creation; the old has gone, the new has come!” (2 Corinthians 5:17). A Christian is not simply an “improved” version of a person; a Christian is an entirely new creature. He is “in Christ.” For a Christian to lose salvation, the new creation would have to be destroyed.

A Christian is redeemed. “For you know that it was not with perishable things such as silver or gold that you were redeemed from the empty way of life handed down to you from your forefathers, but with the precious blood of Christ, a lamb without blemish or defect” (1 Peter 1:18–19). The wordredeemed refers to a purchase being made, a price being paid. We were purchased at the cost of Christ’s death. For a Christian to lose salvation, God Himself would have to revoke His purchase of the individual for whom He paid with the precious blood of Christ.

ይቀጥላል!!
134 viewsAMNA TADESSE, 12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-14 19:41:38 2. ክርስቲያን በእግዚአብሔር የጸደቀ ነው::
ሮሜ 8 (Romans)
33፤ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል? የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው፥ የሚኰንንስ ማን ነው?

መጽደቅ ይቅርታን ከመቀበል ይበልጣል::

ለአማኝ ጏጥያት የሚያሰከፈለወን መስዋት ሁሉ ኢየሱስ ከፍሏል::ኢየሱስ ሙሉን ክፈያ ስለከፈለ እግዚአብሔር የአማኙን ጏጢአት ይቅር ብሎታል ይህ ብቻ አይደለም አማኝ ሀጢአተኝነት እንዳይሰማው ጻድቅ አድርጎታል።

አማኝ የበደሉን ሰርየት አግኝቷል።
ኤፌሶን 1
7፤ በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።

የአማኙን የሀጢአት ደሞዝ ኢየሱስ በሞቱ ከፍሏል።
ሮሜ 6
23፤ የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የዘላለም ሕይወት ነው።

አማኝ ስለ ጸደቀ ወደ ፍርድ በፍፁም አይመጣም።
ዮሐንስ 5
24፤ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።

አማኝ ወንድሜ ጻድቅ ነህ ማለት እግዚአብሔር ተቀብሎሀል ማለት ነው።እግዚአብሔር የተቀበለክ በልጁ ስራ ነው። አሁን እግዚአብሔር አንተን የሚያይ ልክ ከዚህ ቀደም ጏጢአት እንዳልሰራ አድርጎ ነው።


ጸጋ ይብዛላችሁ
ወንድማችሁ አምና

https://t.me/joinchat/AAAAAE5Veg3GlEdndwaGyw
139 viewsAMNA TADESSE, 16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 14:24:42 #ክርስቲያናዊ_ኑሮ

የተወደዳችሁ ወንድሞች ከጌታ ከኢየሱስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን

አንድ ዳግም የተወለደ ሰው ማወቅ ያለበትንና ዳግም በመወለዱ ያገኛቸውን የዳግም ልደት ውጤቶች አብረን እናያለን፦

1. የእግዚአብሔር ልጅ መሆን

ዮሐንስ 1 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ለተቀበሉትና በስሙ ላመኑት ሁሉ ግን የእግዚአብሔር ልጆች የመሆን መብት ሰጣቸው።
¹³ እነዚህም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ፣ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።

አማኝ ኢየሱስን በማመኑ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን መወቅ አለበት የእግዚአብሔር ልጅነት በዳግም ልደት የሚገኝ መለኮታዊ በረከት ነው።

እግዚአብሔር ልጁን ኢየሱስን በተቀበለበት ልክ አማኙን ተቀብሏል።

እግዚአብሔር ኢየሱስን ሊጠላ ሰለማይችል ኢየሱስን በማመን ለራሱ ልጅ የሆኑትን አማኞችን በፍጹም አይጠላቸውም።

በኢየሱስ ያመነን አማኝ እግዚአብሔር በዘላለም ፍቅሩ ይወደዋል።

አማኝ ወንድሜ እንኳን ደስ ያለክ አሁን አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ከእግዚአብሔር ጋር በክርስቶስ ደም ቤተሰብነትን ፈጥረሀል ልጅ ወዳለመሆን በፍጹም አትመለስም።

“በኢየሱስ ክርስቶስ ልጆቹ እንሆን ዘንድ፣ እንደ በጎ ፈቃዱ አስቀድሞ ወሰነን፤”
— ኤፌሶን 1፥5 (አዲሱ መ.ት)

ይቀጥላል.....

ጸጋ ይብዛላችሁ
እኔ ወንድማችሁ አምና ነኝ

ለሌሎች ሼር አድርጉት

https://t.me/joinchat/AAAAAE5Veg3GlEdndwaGyw
176 viewsAMNA TADESSE, 11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-04 03:19:37
“በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
— ሐዋርያት 20፥28
178 viewsAMNA TADESSE, 00:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-22 21:55:51 ቆላስይስ 3 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፣ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ በተቀመጠበት በላይ ያሉ ነገሮችን እሹ፤
² አሳባችሁም በላይ ባለው ላይ እንጂ በምድራዊ ነገር ላይ አይሁን።
³ ሞታችኋልና፤ ሕይወታችሁም ከክርስቶስ ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ተሰውሮአልና፤
⁴ ሕይወታችሁ የሆነው ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ እናንተም በዚያን ጊዜ ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ።(አ.መ.ት)
297 viewsAMNA TADESSE, 18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-14 10:19:56 #ከባርነት_ወደ_ልጅነት


“ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።”
— ኤፌሶን 1፥2

በጌታ የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶች በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የተደረገልንን የማንነት ለወጥ አብረን እንመለከታለን።

ወደ አማኝ ሆይ በክርስቶስ ኢየሱስ ስታምን የተደረገልህንና አሁን በክርስቶስ ያለህን ማንነትህን መረዳትን የመሰለ መታደል አለ በዬ አላምንም።በክርስቶስ ኢየሱስ የተደረገለትን የማንነት ለውጥ ያልተረዳ አማኝ ማንነትን ባለማወቅ ቀውስ ውስጥ ያለ ምስኪን እርሱ ነው።

መጽሐፍ ቅዱሳችን በክርስቶስ ሰለተደረገልን አዲሱ መንነታችን እነደዚህ ይለናል

ገላትያ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
1“ነገር ግን እላለሁ፥ ወራሹ ሕፃን ሆኖ ባለበት ዘመን ሁሉ፥ ምንም የሁሉ ጌታ ቢሆን ከቶ ከባሪያ አይለይም፥”
² ነገር ግን አባቱ እስከ ቀጠረለት ቀን ድረስ ከጠባቂዎችና ከመጋቢዎች በታች ነው።
³ እንዲሁ እኛ ደግሞ ሕፃናት ሆነን ሳለን #ከዓለም #መጀመሪያ #ትምህርት #በታች #ተገዝተን #ባሪያዎች #ነበርን፤
⁴ ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤
⁵ #እንደ #ልጆች #እንሆን #ዘንድ፥ #ከሕግ #በታች #ያሉትን #ይዋጅ #ዘንድ።
⁶ ልጆችም ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባት ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ውስጥ ላከ።
⁷ ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም፤ ልጅም ከሆንህ ደግሞ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ወራሽ ነህ።

አማኝ ወንድሜ አሰቀደመህ አንተ ለመጀመሪያው ትምህርት (ለህግ) ባሪያ ሆነ ከእግዚአብሔር የአባትነት አቅርቦት እረቀ እግዚአብሔርን አባቴ ብለ የመጥራት ደፈረት የሌለ ነበረህ፤

አሁን ግን የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ከህግ በታች ሆኖ ከሴት ተወለደ ይህም የመሆኑ ምከንያት እንደ ባሪያ ሳይሆን እንደ ልጅ ትሆን ዘንድ ነው።


አሁን እግዚአብሔርን አባ ብለ የመጥረት ደፍረት ተሰቶሃል በፍጹም ልብህ እንዳይፈራ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ እንደዚህ ይላልና

“አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት #የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።”
— ሮሜ 8፥15

ይህ ቃል የታመነ ነው እግዚአብሔር አባታችን ነው እኛም ደግሞ ልጆቹ ነን በክርስቶስ ኢየሱስ መንፈስ ከሆነው አባታችን ተወልደናል፤በአባታችን ውስጥ ያለው የህይወት ስርዓት በእኛም ውስጥ አለ ።
ዮሐንስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤
¹³ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።

“ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው።”
— ዮሐንስ 3፥6

ወንድሜ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን በድፍረት ተናገረው ምክንያቱም እውነተኛ ማንነትህ ሰለሆነ።

የእግዚአብሔር ልጅ ሰለሆነህ የእግዚአብሔር ወራሽ ነህ።

“ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም፤ ልጅም ከሆንህ ደግሞ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ወራሽ ነህ።”
— ገላትያ 4፥7

“ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፥ አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።”
— ሮሜ 8፥17

ከእግዚአብሔር የተወለደ ወደ አለመወለድ አይመለስም እግዚአብሔር ዘለዓለማዊና የማይጠፋ ስለሆነ ከእግዚአብሔር የተወለደም አይጠፋም ።

“በዚህም እጅግ ደስ ይላችኋል፥ ነገር ግን በእሳት ምንም ቢፈተን ከሚጠፋው ወርቅ ይልቅ አብልጦ የሚከብር የተፈተነ እምነታችሁ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ፥ ለምስጋናና ለክብር ለውዳሴም ይገኝ ዘንድ አሁን ለጥቂት ጊዜ ቢያስፈልግ በልዩ ልዩ ፈተና አዝናችኋል።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 1፥6-7

“ዳግመኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም፥ በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ነው እንጂ።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 1፥23

ጸጋ ይብዛላችሁ
ወንድማችሁ አምና

@amnatadesseministry

https://t.me/joinchat/AAAAAE5Veg3GlEdndwaGyw
314 viewsAMNA TADESSE, 07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ