Get Mystery Box with random crypto!

Amna Tadesse Ministry

የቴሌግራም ቻናል አርማ amnatadesseministry — Amna Tadesse Ministry A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amnatadesseministry — Amna Tadesse Ministry
የሰርጥ አድራሻ: @amnatadesseministry
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 190
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም ጥያቄ
📲 0917771886
📲 0932195208
መደወል ትችላላችሁ ።

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-08-13 08:41:38 Channel name was changed to «Amna Tadesse Ministry»
05:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-13 14:56:00 ሰርገኛ ነህ ወይስ ለቅሶኛ?
************************
ለአይሁድ ተሰጥቶ የነበረውን የሙሴ ሕግ ካልፈጸምኩ ብሎ መፍጨርጨር ለአሜሪካ መንግሥት ግብር ካልከፈልኩ ብሎ እንደመጨነቅ ነው!!

ለአሜሪካ መንግሥት ግብር ክፈል እንዳልተባልክ ሁሉ የሙሴንም ሕግ ጠብቅ አልተባልክም!!

የሙሴ ሕግ የተሰጠው ለአይሁዳውያን ብቻ እንጂ ለአለም ሁሉ አይደለም!!

የሙሴ ሕግ በራሱ የተመሰረተው የሌዊ ክሕነት ላይ ነው!!

በሙሴ ሕግ ሊቀካሕናቱ አሮን እንጂ ኢየሱስ አይደለም!!

ኢየሱስን ካሕን አድርጎ ያልሾመን የሙሴ ሕግ ጠብቂ የተባለች ቤተክርስቲያን የለችም!!

በሙሴ ሕግ ደመወዝ እንጂ ስጦታ የለም!!

በሙሴ ሕግ የራስ ጥረት እንጂ የጸጋ እርዳታ የለም!!

በሙሴ ሕግ መስራት እንጂ ማመን አይቻልም!!

በሙሴ ሕግ ባርነት እንጂ ልጅነት የለም!!

በሙሴ ሕግ መርከስ እንጂ መጽደቅ አይታወቅም!!

በሙሴ ሕግ ሞት እንጂ ሕይወት የለም!!

በሙሴ ሕግ ፍርሀት እንጂ ድፍረት የለም!!

በሙሴ ሕግ መቅሰፍት እንጂ ምህረት አይታወቅም!!

በሙሴ ሕግ ኩነኔ እንጂ ሰላም የለም!!

በሙሴ ሕግ ሀዘን እንጂ ደስታ የለም!!

በሙሴ ሕግ ለቅሶኛ እንጂ ሰርገኛ የለም!!


ጸጋ የተሰጠው ለአለም ሁሉ እንጂ ለአይሁዳውያን ብቻ አይደለም!!

በጸጋ ሊቀካሕናቱ ኢየሱስ እንጂ አሮን አይደለም!!

በጸጋ ጽድቅ እንጂ ኩነኔ የለም!!

በጸጋ ሰላም እንጂ መታወክ የለም!!

በጸጋ በረከት እንጂ እርግማን የለም!!

በጸጋ ሕይወት እንጂ ሞት የለም!!

በጸጋ ስጦታ እንጂ ደመወዝ የለም!!

በጸጋ እረፍት እንጂ መባከን የለም!!

በጸጋ መቻል እንጂ መዛል የለም!!

በጸጋ መርካት እንጂ መጠማት የለም!!

በጸጋ ልጅነት እንጂ ባርነት የለም!!

በጸጋ ደስታ እንጂ ሀዘን የለም!!

በጸጋ መቀደስ እንጂ መርከስ የለም!!

በጸጋ ድፍረት እንጂ ፍርሀት የለም!!

በጸጋ ድል እንጂ ሽንፈት የለም!!

በጸጋ ሰርገኛ እንጂ ለቅሶኛ የለም!!


እኔ በጸጋው አርፌአለሁና ሰርገኛ ነኝ!!

አንተስ.....ሰርገኛ ነህ ወይስ ለቅሶኛ?
384 viewsAMNA TEMESGEN, 11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-13 14:05:57 ሕግ እና ጸጋ
***********
❝እንግዲህ ምን እንላለን? ሕግ ኃጢአት ነውን? አይደለም፤ ነገር ግን በሕግ ባይሆን ኃጢአትን ባላወቅሁም ነበር፤ ሕጉ፦ አትመኝ ባላለ ምኞትን ባላወቅሁም ነበርና።❞
— ሮሜ 7 ፥ 7

★ ታድያ ሕግ ምንድን ነው?

ሕግ የኃጢአት እውቀት መጋቢ ነው!!

ሕግ ለሰው ልጅ ሁሉ የኃጢአት የኔታ ነው!!

ሕግ ነቀፋ የሌለው ግን ነቀፋን የሚያመጣ፣ ቅዱስ የሆነ ነገር ግን ኃጢአተኛ ተፈጥሮ ያለውን ሰው የሚኮንን ኮናኝ ነው!!

ሕግ ሰውን ለማጽደቅ ያልቻለ ድኩም ነው!!

ሕግ በኢየሱስ የመስቀል ስራ በአዲሱ ኪዳን ውራጅ የሆነ ነው!!

ሕግ ነቀፋ የተገኘበት አሮጌ ኪዳን ነው!!

ሕግ ሰው የሚወደውን እንዳያደርግ የማይወደውን እንዲያደርግ ባሪያ የሚያደርግ የኃጢአት መተንፈሻ ነው!!

ሕግ ለመግደል ሀይልን የሚሰጥ የኃጢአት ምክንያት ነው!!

ሕግ የኃጢአት ማሰራጫ ጣቢያ ነው!!

ሕግ የኃጢአት ብቸኛ ህልውና ነው!!

ሕግ የኃጢአት ማዳበሪያ የሰው ማጎሳቆያ ፊደል ነው!!

ሕግ የኃጢአት ሕጋዊ መታወቂያ ነው!!

ሕግ የኃጢአት መረጃ ክፍል ነው!!

ሕግ በተሰበከበት ጊዜ ሁሉ ያለ ርኅራሄ ገዳይ ነው!!

ሕግ በክብር የሆነ የሞት አገልግሎት ነው!!

ሕግ ሰውን ገድሎ ኃጢአትን ሕያው የሚያደርግ የኃጢአት ጉልበት ነው!!

ሕግ ኃጢአትን ሕያው ያደረገ የኃጢአት ትንሳዔ ነው!!


❝ኃጢአት ግን ምክንያት አግኝቶ ምኞትን ሁሉ በትእዛዝ ሠራብኝ፤ ኃጢአት ያለ ሕግ ምውት ነውና።❞
— ሮሜ 7 ፥ 8

የሞት መውጊያ ኃጢአት ~ የኃጢአት ሀይል ሕግ ነው!!

ሞት ያለ ኃጢአት ኃጢአትም ያለ ሕግ አይሆንም!!

እንዲሁ ደግሞ..............

የህይወት መንገድ ጽድቅ ~ የጽድቅ ሀይል ጸጋ ነው!!

ህይወት ያለ ጽድቅ ጽድቅም ያለ ጸጋ አይሆንም!!

ጸጋ አድርግ አታድርግ የማይል ተደርጎልሀል ብሎ የሚያሳርፍ ኢየሱስ የሚባል ሰው ነው!!

ጸጋ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት ያወጣን የሕይወት መንፈስ ሕግ ነው!!

ጸጋ እንደ ኃጢአታችን የተከፈለን ደመወዝ ሳይሆን እንደ ቸርነቱ የተሰጠን ስጦታ ነው!!



★ ታድያ በሕግ የሚኖር ሰው በዚህ ስቃይ ውስጥ ሲኖር ምን ይላል?


❝እኔ ምንኛ ጎስቋላ ሰው ነኝ! ለዚህ ሞት ከተሰጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?❞
— ሮሜ 7 ፥ 24

★ መጽሐፍ ቅዱሳችንስ እንዲህ አይነቱን ሰው ምን በማለት እረፍት ይሰጠዋል?

❝እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም።❞
— ሮሜ 8 ፥ 1

★ ሰውዬው ግራ በመጋባት እንዴት ቢልስ?

❝በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው የሕይወት መንፈስ ሕግ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛልና።❞
— ሮሜ 8 ፥ 2

ሀ.......ሌ........ሉ........ያ!!

በክርስቶስ ነኝ ስል አሁን ኩነኔ የለብኝም ማለቴ ነው ፤ አሁን ኩነኔ የለብኝም ስል ደግሞ በክርስቶስ ነኝ ማለቴ ነው!!


from heni
289 viewsAMNA TEMESGEN, 11:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-03 17:50:44 ኢየሱስ ሲደመር

ኢየሱስ + የውኃ ጥምቀት = ሞት

ኢየሱስ + የጌታ እራት/ቅዱስ ቀርባን/ = ሞት

ኢየሱስ + እግር መተጣጠብ = ሞት

ኢየሱስ + የህግ ስራ = ሞት

ኢየሱስ + ስርአት = ሞት

ኢየሱስ + ሰመአታት = ሞት

ኢየሱስ + መለአክት = ሞት

ኢየሱስ + ማሪያም = ሞት

ኢየሱስ + ሀይማኖት = ሞት

 ወዳጄ የዘላለም ህያወት ያገኘከው በኢየሱስ ስራ እንጂ አንተ በምታደርገው በአዳራሽ ስርአት እንዳይመስልህ!! ጸጋን የምትካፈለው በኢየሱስ ደም ብቻ ነው፡፡ በውኃ፣ በጌታ እራት እንዳይመስልህ!! አነዚህ ሁሉ የሚመጡት ከኢየሱስ ደም በኋላ ነው፡፡ ኢየሱስ ላይ ከደመርክ በርግጠኝነት አነግርሀለው ይገድልሀል፤ በማሰናከያው ዲንጋይ እንዳትሰናከል፡፡ አደራ፡፡ አይሁድም በዚህ ማሰናከያ ዲንጋይ ተሰናክለዋል፡፡ ጸጋውበ እምነት ብቻ ነው ያዳነን፡፡ በኢየሱስ ከዳንክ በኋላ የምትኖረውም በኢየሱስ ጸጋ ብቻ እንጂ በራስህ ስራና ስርአት አይደለም፡፡ ኢየሱስ ብቻ በቂ ነው፡፡ ኢየሱስ + ምንም = ሁሉም!!! ሀ…ሌ…ሉ…ያ!!!!!


https://t.me/joinchat/AAAAAE5Veg3GlEdndwaGyw
319 viewsAMNA TEMESGEN, 14:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-17 21:28:50 የእግዚአብሔር ክብር
*******
እስጢፋኖስ...........❝መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት #የእግዚአብሔርን_ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፦እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ።❞

— ሐዋርያት 7 ፥ 55-56

የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ነው!!

❝በመንፈስም ወደ ታላቅና ወደ ረጅም ተራራ ወሰደኝ፥ #የእግዚአብሔርም_ክብር ያለባትን ቅድስቲቱን ከተማ ኢየሩሳሌምን ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አሳየኝ፤ ብርሃንዋም እጅግ እንደ ከበረ ድንጋይ እንደ ኢያሰጲድ ድንጋይ ሆኖ እንደ ብርሌ የጠራ ነበረ፤❞
— ራእይ 21 ፥ 10-11

የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ነው!!

❝ለከተማይቱም #የእግዚአብሔር_ክብር ስለሚያበራላት መብራትዋም በጉ ስለ ሆነ፥ ፀሐይ ወይም ጨረቃ እንዲያበሩላት አያስፈልጓትም ነበር።❞
— ራእይ 21 ፥ 23

የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ነው!!


የእግዚአብሔር ክብር ሁሌም በእኔ ውስጥ ይኖራል፡፡ላፍታ እንኳን አይለየኝም!!

የእግዚአብሔር ክብር ተአምራቱ አይደለም ፤ አጋንንት መጮሁ አይደለም፡፡የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ነው!!
ሙሴ ብዙ ተአምራትን ካደረገ በሗላ እግዚአብሔርን እባክህ ክብርህን አሳየኝ አለው፡፡

እግዚአብሔር እንዲህ መለሰለት፦❝ደግሞም፦ ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻልህም አለ።❞
— ዘጸአት 33 ፥ 20

የእግዚአብሔር ክብር የሆነው ኢየሱስ በሙሴ ውስጥ አላደረም!!በእኛ ውስጥ ግን አድሯል!!በደሙ ቀድሶን ማደሪያዎቹ ሆነናል!!

እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው?


ኢየሱስን ይዞ እባክህ ክብርህን አሳየኝ ፈጽሞ አይባልም!!

ሙሴ እግዚአብሔርን ክብርህን አሳየኝ ብሎ የጠየቀው ኢየሱስን ለማየት ነው፡፡

መጽሐፍ እንደሚል.........

ዕብራውያን 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁴ ሙሴ ካደገ በኋላ የፈርዖን የልጅ ልጅ እንዳይባል በእምነት እምቢ አለ፤
²⁵-²⁶ ከግብፅም ብዙ ገንዘብ ይልቅ #ስለ_ክርስቶስ_መነቀፍ እጅግ የሚበልጥ ባለ ጠግነት እንዲሆን አስቦአልና ለጊዜው በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ፤ ብድራቱን ትኵር ብሎ ተመልክቶአልና።

ሙሴ ከግብፅ ብዙ ገንዘብ ይልቅ እጅግ የሚበልጥ ባለጠግነት እንደሆነ ያሰበው #ስለ_ክርስቶስ መነቀፍን ነው!!

እኛ እንደሙሴ አይደለንም!!

መጽሐፍ እንደሚል.............

❝ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተሞልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው #ክብሩን_አየን።❞
— ዮሐንስ 1 ፥ 14


ክብርህን አሳየኝ = ኢየሱስን አሳየኝ!!

★የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ነው!! ሀ ሌ ሉ ያ !!


Henok Ashever

https://t.me/joinchat/AAAAAE5Veg3GlEdndwaGyw
302 viewsAMNA TEMESGEN, 18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-17 07:23:59 ይስሐቅ እና ኢየሱስ

1. ሁለቱም የተስፋ ልጆች ናቸው፡፡
ይስሐቅ፡- ለሳራ ና ለአብርሀም የተገባላቸው፡፡/ ዘፍ. 18፡10 ፤ ዘፍ. 15/
ኢየሱስ፡- ለእስራኤል ተስፋ/ኢሳ. 7፡14/ ለማሪያም/ሉቃ. 1፡31/ ለሁላችንም/ዘፍ.12፡3፤ ዮሀ. 3፡16/
2. ሁለቱም የመለኮት /የእግዚአብሔር/ እቅድ ነበረባቸው፡፡
ይስሐቅ፡- የክርስቶስን/የመሲሁን/ ዘር ተሸክሟል፡፡/ዘፍ.12፡3፤ ዘፍ. 14/
ኢየሱስ፡- የመሲሁን ዘር ፈጽምታል፡፡/ገላ. 4፡4/
3. ሁለቱም የተወለዱት በተአምራት ነው፡፡
ይስሐቅ፡- አብርሀም ና ሳራ አርጅተው፡፡/ዘፍ. 17፡ 19፤ ዘፍ. 21፡2/
ኢየሱስ፡- ከድንግል ማሪያም፡፡/ኢሳ. 7፡14፤ ሉቃ. 1፡34/
4. ሁለቱም ብቸኛ ልጅ ናቸው፡፡
ይስሐቅ፡- ብቸኛው የቃልኪዳን ልጅ፡፡ (አብርሀም ግን ሰባት ልጅ አለው፡፡ ዘፍ.16፡15፤ 22፡2፤ 25፡1)
ኢየሱስ፡- ብቸኛ የእግዚአብሔር ልጅ፡፡/ዮሀ. 3፡16/
5. ሁለቱም ባባታቸው ይወደዳሉ፡፡
ይስሐቅ፡- በአብርሀም/ዘፍ. 22፡2/
ኢየሱስ፡- በአብ/ዮሀ.3፡16/
6. ሁለቱም በወንድሞቻቸው ተጠሉ፡፡
ይስሐቅ፡- በኢስማኤል/ዘፍ.21፡9/ ና በሌሎች በአብርሀም ልጆች/ዘፍ.25፡6/
ኢየሱስ፡- በዘመዶቹ እብድ ተብሏል፡፡/ማር. 3፡21/፤ እግዚአብሄርን መርጠናል በሚሉ፡፡/ዮሀ.15፡25/
7. ሁለቱም ተሰውተዋል፡፡
ይስሐቅ፡- በእግዚአብሄር ትዕዛዝ አብርሀም ብቸኛ ልጁን፡፡/ዘፍ.22፡2/
ኢየሱስ፡- በእግዚአብሄር ትዕዛዝ ለሀጢአት ስርየት፡፡/ሉቃ.24፡7፤ 1ዮሐ.2፡2፣ 4፡8
8. ሁለቱም እንደ በግ ጠቦት፡፡
ይስሐቅ፡- አብርሀም የሚሰዋው የእግዚአብሄር በግ፡፡/ዘፍ. 22፡7/
ኢየሱስ፡- የእግዚአብሔር በግ እግዚአብሔር የሚሰዋው፡፡/ዮሀ.1፡36/
9. የሁለቱም መሰዊያ ተራራ ተመሳሳይ ነው፡፡ ሞሪያም፣ ጎልጎታና ካልቫሪ ተመሳሳይ ና አንድ አይነት ቦታ ናቸው፡፡/ዘፍ. 22፡2፣14፤ ሉቃ. 23፡33/
10. ሊሰዉ ሲሉ ሁለት ሰው ተከትሏቸዋል፡፡
ይስሐቅ፡- ሁለቱ ሎሌዎች፡፡/ዘፍ.22፡3/
ኢየሱስ፡- ሁለቱ ወንበዴዎች፡፡/ሉቃ.23፡32/
11. ሁለቱም የሚሰውበትን እንጨት ተሸክመዋል፡፡
ይስሐቅ፡- የሚሰዋበትን እንጨት፡፡/ዘፍ.22፡6/
ኢየሱስ፡- የሚሰዋበትን መስቀል፡፡/ሉቃ.23፡26/
12. ሁለቱም የተሸከሙትን እንጨት ታግዘዋል፡፡
ይስሐቅ፡- ሎሌዎቹ/ዘፍ. 22፡6/
ኢየሱስ፡- ስምኦን/ማቴ.27፡32/
13. ሁለቱም ነብሳቸውን ለመሰዋት ፍቃዳቸውን ሰተዋል፡፡
ይስሀቅ፡- ዘፍ. 22፡9
ኢየሱስ፡- ዮሀ.10፡18
14. ሁለቱም ከሞት ተነስተዋል፡፡
ይስሐቅ፡- በምሳሌ/ዕብ.11፡19/
ኢየሱስ፡- በአካል/1ቆሮ.15፡4/

መጽሀፍት ሁሉ ስለ ኢየሱስ ይናገራሉ፡፡ ሁሌም መጽሀፍ ቅዱስ ስናጠና ኢየሱስን እንፈልገው፡፡
341 viewsAMNA TEMESGEN, 04:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-13 08:34:27 የበጉ ሰርግ /ራዕ. 19፡7፤ ራዕ. 19፡9/

አሁን በኢትዮጵያውያን አቆጣጠርና በሃል ወቅቱ የሰርግ ወቅት ነው፡፡ እናት አባት የሚድርበት ልጅ የሚዳርበት ወቅት ነው፡፡ ታዲያ በዚህ ወቅት አንድ ሰርግ ትዝ ይለኛል እርሱም የበጉ ሰርግ ይባላል፡፡ ይህ ሰርግ ላይ የሚታደሙትና ሙሽሪት የሚሆኑት በክርስቶስ የሚያምኑ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ ሙሽራውም በጉ ኢየሱስ ነው፡፡ ታዲያ አንድ ነገር ትዝ እንዲላቹ እፈልጋለው!! የበጉ ሰርግና የምድራዊው ሰርግ…..

የበጉ ሰርግ፡- ፍጹም ሰላም ያለበት፡፡
ምድራዊው ሰርግ፡- የስሜት ሰለም ያለበት፡፡

የበጉ ሰርግ፡- ፉክክር የሌለበት፡፡
ምድራዊው ሰርግ፡- በፉክክር የታጀበ፡፡

የበጉ ሰርግ፡- ሁሉ እውነት የሆነ፡፡
ምድራዊው ሰርግ፡- ባርቴፍሻል ነገር ያሸበረቀ፡፡

የበጉ ሰርግ፡- አስመሳይነት የሌለበት፡፡
ምድራዊው ሰርግ፡- ግብዝነት የነገሰበት፡፡

የበጉ ሰርግ፡- ያመኑ ብቻ የሚታደሙበት፡፡/ከአንድ ወገን የሆኑ/
ምድራዊ ሰርግ፡- ሁሉ የሚታደሙበት፡፡/ከአንድ ወገን ያልሆኑ/

የበጉ ሰርግ፡- ድካም የሌለበት፡፡
ምዳራዊ ሰርግ፡- ድካም ያለበት፡፡
.
.
.
.
የበጉ ሰርግ፡- የሚጎለው ነገር የሌለበት፡፡
ምድራዊው ሰርግ፡- ብዙ ነገር የሚጎልበት፡፡

ወዳጄ ልንታደምበት፤ ምን መታደም ብቻ የሰርጉ ባለቤት ልንሆንበት የምንጠብቀው ሰርግ ግሩም እና ድንቅ ነው፡፡ እንዲ ያለ ሰርግ ነው የሚጠብቀን፡፡ ያጨን ሙሽራችን ኢየሱስ ይመጣል ይወስደናል!!!! ማራናታ ጌታ ኢየሱስ ሆያ በቶሎ ናና ውሰደን፡፡/ኤፌ. 5፡21-33/
252 viewsAMNA TEMESGEN, 05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-09 13:28:30 #ጌታችን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #በታህሳሥ #ወር #አለመወለዱን #ያውቃሉ???
===============================

#መንፈሳዊ #ሰው #ግን #ሁሉን #ይመረምራል
1ቆሮ 2፡15

ዮሐንስ 8
32፤ እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል፡ አላቸው።

ቆላስይስ 2
16፤ እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ።
17፤ እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮች ጥላ ናቸውና፥ አካሉ ግን የክርስቶስ ነው።

ኢሳይያስ 34
16፤ በእግዚአብሔር መጽሐፍ ፈልጉ አንብቡም፤ አፌ አዝዞአልና፥

1) በእውነት ኢየሱስ ክርስቶስ በታህሳስ ወር ተወልዷልን???
2) የሚደረገው ስርዓትስ ከክርስትና ጋር ግንኙነት አለው??
3) የገና ዛፉስ ከየት መጣ???
4) መብራቱ እና አፉፋውስ ከየት መጣ???
5) ቅዱስ ኒቆላዎስ ( የገና አባት ) የተባሉትስ ከየት መጡ???

መንፈሳዊ ሰው ግን ሁሉን ይመረምራል 1ቆሮ 2:15
መፅሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደው በታህሳስ ወር እንዳልሆነ ይናገራል።

መፅሐፍ ቅዱስ ምን ይላል !!!

1ዜና 24፡7-19 ንጉሥ ዳዊት ካህናትን በተራቸው ወደ እግዚአብሔር መቅደስ ገብተው ያጥኑ ዘንድ መደባቸው 24 ካህናት ነበሩና በወር 2 ካህን ማለትም( ከ 1-15 እና ከ 16-30) በ 12 ወር 24 ካህናትን አደረገ ።

በእስራኤላዊያን ቀን አቆጣጠር መሰረት ደግሞ የመጀመሪያ ወራቸው ኒሳን (Nisan) ይባላል።
ዘፀ 12:1- አስቴር 3፡7 , 8፡9
የእስራኤል የመጀመሪያ ወር ኒሳን በኢትዮጵያውያን ቀን አቆጣጠር ሚያዚያ መሆኑ ነው።

፨ በምድቡም መሰረት
በአንደኛው ወር (ኒሳን)
ከ 1-15 ቀን== ዮአሪም
ከ 16-30 ቀን== ዮዳኤ

በሁለተኛው ወር (እያር)
ከ 1-15 ቀን==ካሪም
ከ 16-30 ቀን==ሥዖሪም

በሶስተኛው ወር (ሲቫን)
ከ 1-15 ቀን==መልክያ
ከ 16-30 ቀን==ሚያሚን

በአራተኛው ወር ( ታሙዝ)
ከ 1-15 ቀን== አቆስ
ከ 16-30 ቀን== አብያ

በሉቃስ ወንጌል 1፡5- 13 ከአብያ ቤተሰብ የሆነ በ 4ኛው ወር (ታሙዝ) የወሩ ሁለተኛ አጋማሽ ማለት ከ 16-30 ቀን በክፍሉ ተራ ለማጠን ወደ እግዚአብሔር መቅደስ የገባ ስሙ ዘካርያስ የሚባል ሰው እናገኛለን ።
መቅደስ ውስጥ እያጠነ መልአኩ ገብርኤል ተገልጦ ልጅ እንደሚወልድ ይነግረዋል ከዚያም ዩሐንስ መጥምቁ ይፀነሳል ማርያም ደግሞ ከ 6 ወር በኃላ በመንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን ትፀንሳለች።

መጥምቁ ዩሐንስ ኢየሱስን በ6 ወር ስለሚቀድመው በ 10ኛው ወር (#ቴቬት) ኢየሱስ ይፀነሳል
ቴቬት 10ኛ ወራቸው በኢትዮጵያ በታህሳሥ ወር ኢየሱስ ይፀነሳል ከታህሳሥ ጀምሮ 9 ወር ስንቆጥር መስከረም (ቴስር) መጨረሻ ጥቅምት መጀመሪያ ላይ ኢየሱስ ይወለዳል ።

ሉቃ 22:14-23, 1ቆሮ 11:23-25
ኢየሱስ ክርስቶስ በመጽሐፍ ቅዱስ ተወዳጅ እና የከበረ የጌታ እራት ስነስርዓት እስክመጣ ሞቴን አስቡ በማለት ለቤተክርስቲያን ሰጥቷል ። እንጂ የትኛውም ቦታ ላይ ልደቴን በታህሳስ ወር መጨረሻ አስቡልኝ አላለም

መፅሐፍ ቅዱስ እንደዚህ የሚናገር ከሆነ የገና በዓል እየተባለ በታህሳስ ወር የሚከበረው ከየት መጣ ??

የገና በዓል በቅርብ የጀመረ ሳይሆን ክርስቶስ ከመወለዱ በፊትም በአህዛቦች ይከበር የነበረ ነው ከታህሣሥ 25 አስከ ጥር 1 ድረስ ይከበር ነበር ይህ መፅሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት የሌለው የአህዛብ በዓል
ክርስትና ከተጀመረ ከ 313 በኃላ ቤተክርስቲያን ነፃነቷን ስታገኝ አህዛብን ተከትሎ የገባ የአህዛብ በዓል ነው። አህዛቦች የብርሃን አምላካችን(በዐል የተባለው ጣኦት) የተወለደበት ብለው ጨለማው አለፈ የበጋው ብርሃን መጣ በማለት እሳትን እያነደዱ የለመለመ ዛፍን እየቆረጡ ያከብሩ ነበር። ይህ አህዛባዊ በዓል በቤተክርስቲያን ውስጥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ተብሎ ተቀየረ ። ቆይቶም የካቶሊክ ቅዱስ የተባሉት ኒቆላዎስ የገና አባት ተብለው በየቤተክርስቲያኑ ውስጥ ተቀባይነት ካገኙ ዘመናትን አስቆጥረዋል ።

ቀኑ ወሩ አመቱም መጽሐፍ ቅዱሳዊ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን ይህ በዓል ክርስቶስን የማያከብር ብዙ ቤተሰብ የሚበጠበጥበት የጌታችን ስም የማያከብር አለም የዳንኪራ ምሽት አዘጋጅታ ወጣቱን እና ባለትዳሩንም ሁሉ የምትጋብዝበት አጋንንታዊ በዓል ነው።
ክርስቶስን የማያከብረው አለም በስሙ የሚያሳምጽበት እውነት ይሄ በዓል የክርስቲያኖች ነውን???

ምሳሌ 30
5፤ የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች፤ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው።
6፤ እንዳይዘልፍህ፥ ሐሰተኛም እንዳትሆን በቃሉ አንዳች አትጨምር።

የገና በዓል እንዲህ ስር የሰደደ እና በብዙኀን ዘንድ ተቀባይነት ቢያገኝም እውነት ሊሆን ግን አይችልም እውነቱ የእግዚአብሔር ቃል የሚናገረው ብቻ ነው።

1 ዮሐንስ 5 ፡21፤ ልጆች ሆይ፥ ከጣዖታት ራሳችሁን ጠብቁ።

ይሁዳ 1፡17
እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት ቀድሞ የተነገረውን ቃል አስቡ፤
237 viewsNathnael M. Gawo, 10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-09 09:08:50 #ጌታችን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #በታህሳሥ #ወር #አለመወለዱን #ያውቃሉ???
===============================

#መንፈሳዊ #ሰው #ግን #ሁሉን #ይመረምራል
1ቆሮ 2፡15

ዮሐንስ 8
32፤ እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል፡ አላቸው።

ቆላስይስ 2
16፤ እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ።
17፤ እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮች ጥላ ናቸውና፥ አካሉ ግን የክርስቶስ ነው።

ኢሳይያስ 34
16፤ በእግዚአብሔር መጽሐፍ ፈልጉ አንብቡም፤ አፌ አዝዞአልና፥

1) በእውነት ኢየሱስ ክርስቶስ በታህሳስ ወር ተወልዷልን???
2) የሚደረገው ስርዓትስ ከክርስትና ጋር ግንኙነት አለው??
3) የገና ዛፉስ ከየት መጣ???
4) መብራቱ እና አፉፋውስ ከየት መጣ???
5) ቅዱስ ኒቆላዎስ ( የገና አባት ) የተባሉትስ ከየት መጡ???

መንፈሳዊ ሰው ግን ሁሉን ይመረምራል 1ቆሮ 2:15
መፅሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደው በታህሳስ ወር እንዳልሆነ ይናገራል።

መፅሐፍ ቅዱስ ምን ይላል !!!

1ዜና 24፡7-19 ንጉሥ ዳዊት ካህናትን በተራቸው ወደ እግዚአብሔር መቅደስ ገብተው ያጥኑ ዘንድ መደባቸው 24 ካህናት ነበሩና በወር 2 ካህን ማለትም( ከ 1-15 እና ከ 16-30) በ 12 ወር 24 ካህናትን አደረገ ።

በእስራኤላዊያን ቀን አቆጣጠር መሰረት ደግሞ የመጀመሪያ ወራቸው ኒሳን (Nisan) ይባላል።
ዘፀ 12:1- አስቴር 3፡7 , 8፡9
የእስራኤል የመጀመሪያ ወር ኒሳን በኢትዮጵያውያን ቀን አቆጣጠር ሚያዚያ መሆኑ ነው።

፨ በምድቡም መሰረት
በአንደኛው ወር (ኒሳን)
ከ 1-15 ቀን== ዮአሪም
ከ 16-30 ቀን== ዮዳኤ

በሁለተኛው ወር (እያር)
ከ 1-15 ቀን==ካሪም
ከ 16-30 ቀን==ሥዖሪም

በሶስተኛው ወር (ሲቫን)
ከ 1-15 ቀን==መልክያ
ከ 16-30 ቀን==ሚያሚን

በአራተኛው ወር ( ታሙዝ)
ከ 1-15 ቀን== አቆስ
ከ 16-30 ቀን== አብያ

በሉቃስ ወንጌል 1፡5- 13 ከአብያ ቤተሰብ የሆነ በ 4ኛው ወር (ታሙዝ) የወሩ ሁለተኛ አጋማሽ ማለት ከ 16-30 ቀን በክፍሉ ተራ ለማጠን ወደ እግዚአብሔር መቅደስ የገባ ስሙ ዘካርያስ የሚባል ሰው እናገኛለን ።
መቅደስ ውስጥ እያጠነ መልአኩ ገብርኤል ተገልጦ ልጅ እንደሚወልድ ይነግረዋል ከዚያም ዩሐንስ መጥምቁ ይፀነሳል ማርያም ደግሞ ከ 6 ወር በኃላ በመንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን ትፀንሳለች።

መጥምቁ ዩሐንስ ኢየሱስን በ6 ወር ስለሚቀድመው በ 10ኛው ወር (#ቴቬት) ኢየሱስ ይፀነሳል
ቴቬት 10ኛ ወራቸው በኢትዮጵያ በታህሳሥ ወር ኢየሱስ ይፀነሳል ከታህሳሥ ጀምሮ 9 ወር ስንቆጥር መስከረም (ቴስር) መጨረሻ ጥቅምት መጀመሪያ ላይ ኢየሱስ ይወለዳል ።

ሉቃ 22:14-23, 1ቆሮ 11:23-25
ኢየሱስ ክርስቶስ በመጽሐፍ ቅዱስ ተወዳጅ እና የከበረ የጌታ እራት ስነስርዓት እስክመጣ ሞቴን አስቡ በማለት ለቤተክርስቲያን ሰጥቷል ። እንጂ የትኛውም ቦታ ላይ ልደቴን በታህሳስ ወር መጨረሻ አስቡልኝ አላለም

መፅሐፍ ቅዱስ እንደዚህ የሚናገር ከሆነ የገና በዓል እየተባለ በታህሳስ ወር የሚከበረው ከየት መጣ ??

የገና በዓል በቅርብ የጀመረ ሳይሆን ክርስቶስ ከመወለዱ በፊትም በአህዛቦች ይከበር የነበረ ነው ከታህሣሥ 25 አስከ ጥር 1 ድረስ ይከበር ነበር ይህ መፅሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት የሌለው የአህዛብ በዓል
ክርስትና ከተጀመረ ከ 313 በኃላ ቤተክርስቲያን ነፃነቷን ስታገኝ አህዛብን ተከትሎ የገባ የአህዛብ በዓል ነው። አህዛቦች የብርሃን አምላካችን(በዐል የተባለው ጣኦት) የተወለደበት ብለው ጨለማው አለፈ የበጋው ብርሃን መጣ በማለት እሳትን እያነደዱ የለመለመ ዛፍን እየቆረጡ ያከብሩ ነበር። ይህ አህዛባዊ በዓል በቤተክርስቲያን ውስጥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ተብሎ ተቀየረ ። ቆይቶም የካቶሊክ ቅዱስ የተባሉት ኒቆላዎስ የገና አባት ተብለው በየቤተክርስቲያኑ ውስጥ ተቀባይነት ካገኙ ዘመናትን አስቆጥረዋል ።

ቀኑ ወሩ አመቱም መጽሐፍ ቅዱሳዊ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን ይህ በዓል ክርስቶስን የማያከብር ብዙ ቤተሰብ የሚበጠበጥበት የጌታችን ስም የማያከብር አለም የዳንኪራ ምሽት አዘጋጅታ ወጣቱን እና ባለትዳሩንም ሁሉ የምትጋብዝበት አጋንንታዊ በዓል ነው።
ክርስቶስን የማያከብረው አለም በስሙ የሚያሳምጽበት እውነት ይሄ በዓል የክርስቲያኖች ነውን???

ምሳሌ 30
5፤ የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች፤ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው።
6፤ እንዳይዘልፍህ፥ ሐሰተኛም እንዳትሆን በቃሉ አንዳች አትጨምር።

የገና በዓል እንዲህ ስር የሰደደ እና በብዙኀን ዘንድ ተቀባይነት ቢያገኝም እውነት ሊሆን ግን አይችልም እውነቱ የእግዚአብሔር ቃል የሚናገረው ብቻ ነው።

1 ዮሐንስ 5 ፡21፤ ልጆች ሆይ፥ ከጣዖታት ራሳችሁን ጠብቁ።

ይሁዳ 1፡17
እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት ቀድሞ የተነገረውን ቃል አስቡ፤

Henok
202 viewsAMNA TEMESGEN, 06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-09 08:53:37 ማንም አልተወለደም
******************
ከኢየሱስ በቀር.........
ማንም ያለወንድ ፈቃድ አልተወለደም!!

ማንም ከድንግል አልተወለደም!!

ማንም ፈቅዶ አልተወለደም!!

ማንም ራሱ ተንብዮ አልተወለደም!!

ማንም ቀድሞ ኑሮ አልተወለደም!!

ማንም ንጉስ ሆኖ አልተወለደም!!

ማንም አምላክ ሆኖ አልተወለደም!!

ማንም ከሰማይ መጥቶ አልተወለደም!!

ማንም ነፍሱን ሊሰጥ አልተወለደም!!

ማንም ነፍስ ሊያድን አልተወለደም!!

ማንም የሀጥያት መስዋዕት ሊሆን አልተወለደም!!

ማንም ተፈፀመ ሊል አልተወለደም!!

ማንም ሀጥያተኛ ወዶ አልተወለደም!!


አወላለዱ ልዩ የሆነው ኢየሱስ አዳዳኑ ልዩ ነው.......የወንጌል ርዕስ ኢየሱስ ተወልዷል ሳይሆን ኢየሱስ ያድናል ነው!!

የምስራቹ ያለው መወለዱ ላይ ሳይሆን የመወለዱ ምክንያት ላይ ነው......ተወለደ ብሎ የሚቆም ወንጌል የለም.........ተወለደ ብቻውን ወንጌል አይደለም........ለምን ተወለደ?

መጽሐፍ እንደሚል

ሉቃስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ መልአኩም እንዲህ አላቸው፦ እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤
¹¹ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።

ደግሞም መጽሐፍ እንደሚል.......

“ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።”
— ሮሜ 1፥3-4


ለኢየሱስ ትልቁ ጉዳይ ሚልዮኖች የሚያከብሩለት የእርሱ ልደት ሳይሆን የአንድ ሰው ዳግም ውልደት ነው!!

የተወለደው ልደት ፍለጋ ሳይሆን የጠፋውን ሰው ፍለጋ ነው!!

ወንጌል ስለ ልደቱ ሳይሆን ስለ ልጁ ነው!!



#ሄኖክ_አሸብር
186 viewsAMNA TEMESGEN, 05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ