2022-08-28 14:10:34
አስቸኳይ የኸይር ሥራ ጥሪ!
ከታች በፎቶው ላይ የምትመለከቱት ህንፃ አሸዋ ሜዳ ጉቱ ሪል ስቴት በሚገኘው አቡበከር ሲዲቅ መስጂድ አጠገብ የሚገኝ ሲሆን የአካባቢው ጀመዓ ሊገዛው በመረባረብ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ጊዜ ከ500 በላይ የሚሆኑ የአከባቢው ጀመዓ ቤተሰብ ልጆች እጅግ በጣም ጠባብ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ሆነው በመማር ላይ ይገኛሉ። ለወደፊትም የጀመዓው ቁጥር እየጨመረ ስለሚሄድ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍል እጅግ አስፈላጊ ይሆናል።
በምስሉ ላይ የምትመለከቱት G+2 ህንፃ ከመስጂዱ ፊት ለፊት የሚገኝ ሲሆን ህንፃውና 550 ካሬ ስፋት ያለው ግቢ አንድ ላይ 12 ሚሊዮን ሽያጭ ዋጋ ተገምቷል። ባለቤቶቹ መስጂዱ ህንፃውን መግዛት ከቻለ 2 ሚሊየን ቅናሽ በማድረግ 10 ሚሊየን እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል። ሁሉም አቅሙ በፈቀደለት መጠን አላህ በሰጠው ፀጋ ድጋፍ አድርጎ ለሙስሊሞች ወቅፍ በሚሆን ሰደቃ ላይ እንድንረባረብ ጥሪ ቀርቧል።
የመስጂዱ ጀመዓ እስካሁን ባደረጋቸው ጥረቶች በአላህ ፈቃድ 50%ቱን ሸፍኗል። ቀሪውን 50% በአላህ ፈቃድ ሁላችንም ብንረባረብ እንሸፍነዋለን።
መስጂዱ ህንፃውን በአስቸኳይ ለመግዛት ካልቻለ ባለቤቶቹ ባለቸው አጣዳፊ ሃጃ ምክንያት ለሌላ አካል ሊሸጡት ይችላሉና በዚህ አጅሩ እስከ የውመልቅያማ የማያቋርጥ የወቅፍ ስራ በአስቸኳይ እንረባረብ!አሻራችን እናሳርፍ!
አስታውሱ ይህ ስራ የዘላቂ ሰደቃ ( ስደቃ ጀቀሪያ) ዲን መማሪያ መድረሳ ግዥ ነው! አሏህ የሰጠንን ገንዘብ በተገቢው ቦታ ላይ እንቨስት በማድረግ ለአኺራ ስንቃችንን እናዘጋጅ።
√ የባንክ አካውንት ስም፦
GUTU REAL STATE ABUBEKER SIDIQ MESJID
√ የአካውንት ቁጥር፦ 1000376777875
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
መልዕክቱን ሼር በማድረግ፣ ለምናውቃቸው 10 ሰዎች በመጠቆም አጅራችንን እናብዛ።
18.5K views11:10