Get Mystery Box with random crypto!

Ahmedin Jebel - አሕመዲን ጀበል

የሰርጥ አድራሻ: @ahmedin99
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 60.07K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ይፋዊ የአሕመዲን ጀበል የቴሌግራም ገፅ ነው!

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 44

2022-10-29 08:40:25
"እባካችሁን ልጄን አድኑልኝ " እናት

ይህ ቆንጅዬ የሁለት ወር ከሀያ ቀን ህፃን ሀኒፍ ሲርሀም ይባላል። በተወለደ በሳምንቱ የአተነፋፈስ ስርአቱ ሲቀየርባቸው እናት በአስቸኳይ ጤና ጣቢያ ስትወስደው ነበር አተነፋፈሱ ትክክል አይደለም ከአቅማችን በላይ ነው ብለው ወደ ዘውዲቱ ሪፈር የፃፉላት ቀላል ነገር የመሰላቸው የጨቅላ ልጃቸው ነገር ቤተሠብ በሰማው ነገር በጣም ተደናገ።


ሀኒፍ ልቡ በጣም ክፍተት አለው ሳምባውን ደም ይረጫል አልዋቸው ምንም የሌላቸው እናትና አባት ተጨነቁ ያ ደስታቸው በአንዴ ጨለመ
ዘውዲቱ ሆስፒታልም ካቅሜ በላይ ነው ብሎ ወደ ጥቁር አንበሳ ላካቸው ባልጠነከረ ወገብዋ አራስ ልጅዋን ይዛ ለ 1ሳምንት ጥቁር አንበሳ ተቀመጠች ከኦክስጅን ነፃ ሲሆን ግን ወደቤት ሂዱና ከ1ወር በኃላ ተመለሱ ተባሉ የልጃቸውን ደስታ ለመስማት ቀጠሮአቸውን ደርሶ ሲሄዱ በፍፁም ያላሰቡት ሌላ ዱብዳ ተነገራቸው በዚ 1ወር ውስጥ ውጪ ሄዶ መታከም አለበት የህክምና ወጪውም ከ1 ሚሊየን በላይ እንደሆነ ተነገራቸው ምንም የሌላቸው እናትና አባት ተጨነቁ ቶሎ ካልደረሱለት ሊሞትባቸው እንደሚችል ሲነገራቸው
ያልጠበቁት ዱብ እዳ ሆነባቸው

እናት ልጄ ሊሞትብኝ ነው እያለች ቀን ከሌት ማንባት ነው ስራዋ
ምታደርገው ግራ ሲገባት ልመና ወጣች በልጅ አይፈትናቹ አራስ ልጄን አድኑልኝ #ለአላህ ብላቹ እያለች እየተማፀነች ነው

የአቅማችንን #እናግዛቸው #ዱዓእናድርግላቸው 50 ሎሚ ለአንድ ሰው ሽክም ነውና
ምንም ነገር ማድረግ ባንችል እንኳን #ሼር በማድረግ ለብዙዎች እናድርስላቸው
#አካውንት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000433513758 ሰሚራ ኑርሰፋ ኡመር

#ስልክ

0912453547 አባት ሲርሀም
0904623864 እናት ሰሚራ
21.9K views05:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-28 09:16:01
በነቢዩ ሙሀመድ (ሰዓወ) ላይ ሰለዋት ሲያደርጉ ሀጥያት እንደሚራገፍልዎ ያውቃሉ?

★ T.me/ahmedin99

የአላህ መልዕክተኛ(ሰዓወ) እንዲህ ብለዋል:–

"በኔ ላይ አንዴ ሰለዋትን ላወረደ አላህ በሱ ላይ አስር ሰለዋትን ያወርድበታል። አስር ኃጥያቶችንም ያራግፍለታል።"
19.7K views06:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-25 13:47:44
Islaamummaa Rabbiin nuf filatee wanni caalu hin jiru.

Sabummaa, biyyummaa, naannummaa fi gandummaa martu waan biyya lafaatti hafan malee gara akiraatti waan ce'ani miti. Akiraa miti qabrittu fayidaa hinqabanu. Nama Kana wallaalee taanaan vidiyoo kana haga xumuraatti hordafi.
27.3K views10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-21 08:34:32 ልብ ይሰብራል። የኢልም አባት የሆኑት ሸህ ሙሳ ዩሱፉ ጌታሁን አልወሂመኖ አልጎጃሚ በኢትዮ ጠቢብ ሆስፒታል አንዲት ክፍል የስቃይ ትንፋሽ እየተነፈሱ በግልኮስ ድጋፍ ተኮርምተው ማየት ውስጥን ይረብሻል። በሀገር ቤት ያልተገደበ ለአለም በተበረከተ ኪታብ ጭምር የናኘ የሀቅ ብእራቸው ያሳረፉ፤ አንጋፋ መሻኢኮችን ያፈሩ ከልጅነት እስከአሁን ከደርስ ያልተነጠሉ የዒልም ምልክት እጅ ሰጥተው ደረሳ በትነው፤ የመድሃኒት ተቸግረው ሆስፒታል ተኝተዋል። እዚህ አዲስአበባ ላይ በእውቀት የምናውቃቸው ትላልቅ ሸኾች የእሳቸው ደረሳ ነበሩና ጠዋት ማታ እየተመላለሱ ሲጠይቋቸው ከዚያም ከፍ ብሎ የሰው ፊት ቆመው ገንዘብ ሲለመንላቸው የችግሩን ጥልቀት ማየት ያሳዝናል።

የራሳቸውን ደረሳዎች እያስተማሩ የመታከሚያ እንኳ እስኪቸገሩ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የኢልም አዝመራ ሲዘሩ ኑረው ይኸው ለህምም እጅ ሰጥተው ኢትዮ ጠቢብ ሆስፒታል ያለ አምስት ሳንቲም በደረሳዎቻቸው ድጋፍ መጥተው ወደቀዋል።

መካ በሄዱበት ወቅት የደረስነት ሸሪካዎቻቸው ታላቁ ሙሀዲስ ሸህ ሙሀመድ ሼህ አልቦረኒይ አቆይተዋቸው ለኪታባቸው ግብዓት የሆኑ፤ የራሳቸውንም ኪታብ ፅፈው አሳትመው ያሰራጩ ያ የሚፅፉበት እጃቸው ሲያቀሩ ኪታብ የሚገልጡበት ክንዳቸው ግልኮስ ተተክሎበት አቅም አጥቶ ስናይ እንዴት ልባችን አይዘን?

አሁን ላይ ጠዋት ማታ እየተመላለሱ የርሳቸው ተማሪ የነበሩ የአሁን ዑለማዎች ህይወታቸውን ለማትረፍ ያቅማቸውን እየጣሩ ነው። ነገሩ ግን በተወሰኑ ሰዎች እንቅስቃሴ የሚሆን አልሆነምና ሙስሊሞች ሆይ ሀላፊነቱ የሁላችንም በመሆኑ ዑለማዎች በሞት ሲለዩን አዝነን ከመቅበር ይልቅ በህይወት እያሉ የመርዳት ግዴታችንን ልንዘነጋ አይገባም!!!

ሸህ ሙሳ ዩሱፍን ለመደገፍ

በልጃቸው አብዱልፈታህ ሸህ ሙሳ በሸህ ሀሰን ምስጋናው እና በአብደላ ያሲን የተከፈተ
★ኦሮሚያ ህብረት ስራ : 1000092629377
★አቢሲኒያ : 113882287
★ ዳሽን : 2955735826411

★ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000501717178 ሸህ ሙሀመድ ሀሰን እና ሸህ ያቁብ ሙሀመድ እና አብደላ ያሲን
34.4K viewsedited  05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-21 08:34:00
22.7K views05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 20:18:39
ሼህ አደም ቱላ አላህ ምህረቱን ይለግሳቸውና በየካቲት 2010 ከእስር የተፈታሁ ጊዜ እድሜያቸው ከ100 ዓመት በላይ ሆነው ሳለ ከሀረር ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በፎቶግራፉ ላይ እንደምታዩት «እንኳን አላህ አስፈታችሁ» ብለው መርቀውኝ ነበር።አላህ ጀነቱል ፊርደውስን ይመንዳቸው።

Mufti sheh Aadam Tuulaan bara 2010 yeroo mana hidhaati hikamee umrin isaani waggaa 100 darbee illee qaamaan Harari gara finfinnee dhufuun akkuma suuraa armaan gadi irratti argitanutti "baga Rabbin si hiiksisee" jechuun na eebisani fi du'ai naaf godhani turan. Rabbin araaramee fi jannatal firdawsin isaan habadhaasu.
23.5K views17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 09:37:40 የሙፍቲ ሼህ አደም ቱላ ሕይወት እጅግ የሚያስደስት ነው።


የሙፍቲ ሼህ አደም ቱላ ሕይወት እጅግ የሚያስደስት ነው። እድሜያቸውን በሙሉ በዲን ኪድሚያ ነው ያሳለፉት።

ሙሉ ስማቸው ሼህ አደም ቱላ አህመድ ኢብራሂም ዑስማን(ሸንኮር) ይባላሉ።ወደ 110 ዓመት የሚጠጋ እድሜ በሕይወት ኖረዋል።ከዚህ ቀደም ከኑረል ሁዳ ቲቪ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ እርሳቸውና የጎረቤት ልጅ በተመሳሳይ እለት የተወለዱ ሲሆን የጎረቤቱ ልጅ አባት ልጁ የተወለደበትን ቀን በማስታወሺያ የተጻፈውን መነሻ በማድረግ በጊዜው እድሜያቸው 104 ዓመት እንደሆነ ገልጸው ነበር። ከ2ኛው የጣሊያን ወረራ ቀደም ብሎ ነበር በ12 ዓመታቸው እያሉ በሱማሌው ሼህ ሙሀመድ ኢብራሂም ኩርኮሮ ላይ ቁርኣንን ጨርሰው ሰፊናንና ዑምደቱል አህካም ኪታብን ተማሩ።

ሼህ አሊይ ዐርሲ ዘንድ ለ10 ዓመታት የተለያዩ የፊቅህ ኪታቦችን እስከ ሚንሀጅ ድረስ ተማሩ።የዐረብኛ ቋንቋ ናህው፣ ሰርፍ፣በያንና መንጢቅ የጅማ ተወላጅና በአንይ ማዕከል በተማሩት በሸህ አብዱልመጂድ ዘንድ ጀምረው፣በሀረሩ የኮምቦልቻ ተወላጅ ሼህ ሰኢድ ዘንድ አጠናቀቁ።

የተፍሲር ትምህርት በኮምቦልቻው ሼህ ሰኢድ ዘንድ ጀምረው የለኦዳ የተሰኘ አከባቢ ሼህ ሙሳ ዘንድ አጠናቀዋል። የተውሂድና ሀዲስ ትምህርቶችን የተለያዩ ዓሊሞች ዘንድ ተምረው ማስተማር ጀመሩ።

በኢስላማዊ ዳዕዋና ተግባራት ላይ ለ80 ዓመታት ገደማ ቆይተዋል። በዚህ ጊዜ በሺዎች የሚቆጠሩ ዓሊሞችን ያፈሩ ሲሆን በምዕራብና ምስራቅ ሀረርጌ፣በሀረሪ ክልልና ድሬደዋ አብዛኛዎቹ ዓሊሞች፣ የመስጂድ ኢማሞች የርሳቸው ተማሪዎች ወይንም የተማሪዎቻቸው ተማሪዎች የነበሩ ናቸው።

ሼህ አደም ቶላ በራሳቸው የኢልም ማዕከል(መጅሊስ) በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች የነበራቸው ሲሆኑ እስከ አምና ድረስ በርካቶችን አስተምረው አስመርቀዋል።

ከመደበኛ በተማሪዎች ባሻገር አርሶ አደር ዓሊሞችንም አስተምረው ከ3 ዓመታት በፊት አንድ ሺህ ስምንት መቶ ስልሳ አንድ ሴቶችና ሦስት መቶ ሰባ ሁለት ወንዶች በድምሩ ሁለት ሺህ ሁለት መቶ ሠላሳ ሦስት የገበሬ ተማሪዎችን በሀረር በጨለንቆ አዳራሽ አስመርዋል። ተመራቂዎቹ በግብርና ስራ የሚተዳደሩ ገበሬዎች የሆኑ ሥራቸውን እየሠሩ በቀን ለአንድ ሰዓት ብቻ ከጠዋቱ 2:30 እስከ 3:30 ብቻ ከ3 እስከ ስድስት ዓመታት በመቅራት ቂርዓታቸውን ጨርሰው በሸይክነት የተመረቁ ነበሩ።

ሼህ ዐደም ቱላ በ1960ዎቹ የሙስሊሞች መሪ ድርጅት ለማቋቋም በሀረርጌ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ከነበሩት ዓሊሞች አንዱ የነበሩ ሲሆን 1966 ጀምሮ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን(መጅሊስን) ለመመረሰት በተደረገው ጥረትና ከመሰረቱት ዑለሞች መካከል አንዱ ነበሩ።

በሙስሊሞች የመብት ጉዳይ በድፍረት ይናገሩ ዓሊም ሲሆኑ በ2004 ጀምሮ በተደረገው የድምጻችን ይሰማ እንቅስቃሴ በግልጽ መንግስትን ሲተቹ የነበሩና ለታሳሪዎች ዱዓ ያደርጉ ነበር።

በመጋቢት 2010 ከእስር ቤት ስንፈታ እድሜያቸው 100 አልፎ እንኳ ከሀረር አዲስ አበባ እኔ ቤት ድረስ በአካል በመምጣት «እንኳን አላህ አስፈታችሁ» ብለው መርቀው ዱዓም አድርገውልን ነበር።

በሀረርጌ በሞላ «የመሻይኮች ሼህ» በሚል ማዕረግ ይታወቁ የነበረ ሲሆን ከዓመት በፊት የኦሮሚያ መጅሊስ «ሙፍቲ» የሚል ማዕረግ ሰጥቷቸው ነበር።

እኚህን ታላቅ ዓሊምና ሙፍቲን ለመሸኘት ዛሬ በጠዋቱ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱልከሪም በድረዲን፣የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሼህ ሱልጣን ሀጅ አማን፣ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢ የመጡ ዓሊሞችና እንግዶች ድሬደዋ ገባን።የድሬደዋ ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር አቀባበል አደረጉልን። ቁርስም ጋበዙን።

ቀጥሎም ከሀረርጌ ወረዳዎችና ድሬደዋ ለቀብር ተሚመጣው ህዝብ ብዛት መንገዱ ስለተጨናነቀ በፍጥነት እንድንደርስ በፖሊስ መኪኖች አጀብ ወደ ሀረር አብረን አቀናን።

ህዝቡ በኢማም አህመድ ስታዲየም ከሱብሂ በፊት መግባት የጀመረ ሲሆን በጠዋቱ ሞልቶ ተጨናንቆ አብዛኛው ሰው በከተማው መንገዶች ላይ ተጨናንቆ ደረስን።

ከህዝብ መጨናነቅ የተነሳ ገሚሱ ህዝብ ቀድሞ ሰግዶ እየወጣ ነበር። እኛና እንደ አዲስ ስታዲየሙን የሞላው ህዝብ በመጅሊስ ምክትል ፕሬዝዳንት መሪነት ሰላቱል ጀናዛ ሰገድን። ከተለያዩ አከባቢ የመጡና አውሮፕላን አምልጧቸው የዘገዩት እንደ ዶ/ር ጄይላን ከድር፣ዶ/ር ሼህ ሙሀመድ ሀሚዲን፣ ኡስታዝ ጋሊ አባቦር፣የኦሮሚያ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሼህ ጀማል ሙሳ፣ሼህ አሊ ጅማ፣ሼህ ሻፊ አብዱራህማን እና ሌሎች እንግዶች እንዲደርሱ ሲባል ቀብሩ በአስር ላይ እንዲሆን በተወሰነው መሰረት ቀብሩ በአስር ሰላት ላይ ተፈጸመ።

አላህ ጀነተል ፊርደውስን ይመንዳቸው። ከፊል እንግዶች ሀረር ሲያድሩ እኛም በአላህ ፈቃድ በሼህ አደም ቱላ ሽኝት ላይ ተሳትፈን በአላህ ፈቃድ አሁን ወደ አዲስ አበባ አሁን ተመለስን።
21.2K views06:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 09:37:33
16.7K views06:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 18:31:47
ዘመናዊ ፤ቀላል እና ቀልጣፋውን የሂጅራ ዲጀታል (ኦምኒ ቻናል) አገልግሎት ይጠቀሙ::
ኦምኒ ቻናል ሁሉን በአንዴ ያስችላል::

Hijra Digital
1.2K views15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 16:18:57
ትኩረት የነፈግነው ሐቅ

"ከናንተ በላጫችሁ ቁርኣንን ተምሮ ያስተማረ ነው" ብለዋል ነብያችን (ﷺ)። [ቡኻሪ]

ይሁን እንጂ ብዙ ቁርኣን ያልቀራ ወገን እያለን ለጉዳዩ የሰጠነው ትኩረት ግን ለችግሩ የሚመጥን አይደለም። ስለሆነም ችግሩን በመቅረፍ ላይ ከራሳችን ልንጀምር ይገባል።

* ቁርኣን ካልቀራን ለምን አንቀራም?

* ያልቀራ ቤተሰብ ፣ ጓደኛ፣ ጎረቤት፣ ወዘተ. ካለ ለምን አናቀራም?

* ይህም ካልሆነልን የሚያቀሩትን በምንችለው አቅም ለምን አናግዝም?

ዛሬ ዛሬ ቁርዓን ማስተማር የሰነፎች ወይም እውቀታቸው የደከሙ ሰዎች ስራ እየመሰለ ነው።
ቁርዓን ያልቀራህ ወገኔ ሆይ! የትኩረት ማነስ እንጂ እውነት ቁርኣን ማንበብ መቻል ይህን ያክል ከባድ ነገር ሆኖ ነው ወይ? እስከ መቼ ነው 28 የዐረብኛ ፊደላትን አገጣጥሞ ማንበብ ተራራ የሚሆንብህ? ተገቢ ትኩረት ብንሰጠው ቁርኣን ፈፅሞ ዛሬ በሃገራችን የሚወስደውን የጊዜ መጠን የሚጠይቅ አልነበረም። ከልብ ካለቀሱ እምባ አይገድም ይባላል።

እና ወንድሜ ሆይ! በነፃ የሚያስተምርህ ካገኘህ እሰየው። ካልሆነ ግን በክፍያ የሚያስተምሩ ወንድም/እህቶች ካሉም ደስ እያለህ ከፍለህ ተማር። ለሚያሳንፉ ሰዎች ጆሮ አትስጥ። ቁርኣን መማር ዲግሪና ዲፕሎማ ከመማር በታች ነውንዴ? ቁርኣን መማር ቋንቋ፣ ኮምፒተር፣ ... ከመማር በታች ነውንዴ? እነዚህን ነገሮች ለመማር ስንትና ስንት እያወጣን ቁርኣን ለመማር የሚወጣው ላይ ለቅሶ ማብዛት ምንድነው?
ይልቅ በጊዜ ቁርጠኛ ውሳኔ ወስን። ከዜሮም ብትነሳ እሩቅ አይደለም ትደርሳለህ። ማረም ማስተካከል ከሆነም በአጭር ጊዜ ትጋት ሁነኛ ለውጥ ታያለህ። አላህ ያግዘን።

ኢብኑ ሙነወር
8.4K views13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ