Get Mystery Box with random crypto!

abyssinialaw.com

የቴሌግራም ቻናል አርማ abyssinialaw — abyssinialaw.com A
የቴሌግራም ቻናል አርማ abyssinialaw — abyssinialaw.com
የሰርጥ አድራሻ: @abyssinialaw
ምድቦች: ብድር, ግብሮች እና ህጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.20K
የሰርጥ መግለጫ

A complete and easy access to Ethiopian Legal Information!

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-08-09 16:52:52 የማዕድን ሥራዎች ፈቃድ የተሰጠው ሰው እና በኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ ንዑስ-ሥራ ተቋራጭ የግብር ግዴታ
በ፡ - ከተማ አዳነ ባርጊቾ

በዚህ አጭር ጽሑፍ የማዕድን ሥራዎች ፈቃድ የተሰጠው ሰው እና ንዑስ-ሥራ ተቋራጭ ማነው? የማዕድን ሥራዎች ፈቃድ የተሰጠው ሰው የግብር ግዴታ ምንድነው? ፈቃድ የተሰጠው ሰው ለንዑስ-ሥራ ተቋራጭ ክፍያ ሲፈጽም ቀንሶ የሚይዘው የግብር መጣኔ ምን ያህል ነው? እንዲሁም በኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ ንዑስ-ሥራ ተቋራጭ ያለበት የግብር ኃላፊነት ምን ይመስላል? ለሚሉ ጥያቄዎች ዝርዝር ምላሽ ለመስጠት ተሞክሯል፡፡

መልካም ንባብ!

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2034-tax-liability-of-person-who-is-licensed-for-mining-operations-and-sub-contractor-who-is-not-a-resident-of-ethiopia
6.6K viewsLiku Worku, 13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 19:03:36
ዳሽን ቢራ አክሲዮን ማኅበር ጠበቆችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፤
10.6K viewsLiku Worku, 16:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 11:47:24 ሕጎችን በቀላሉ በዴስክቶፕ ወይም በላፕቶፕዎ ከዚህ ማግኘት ይችላሉ፤

https://www.abyssinialaw.com/lawandcassationDB/

Enjoy and Share
12.1K viewsLiku Worku, 08:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 18:17:26 አዲስ ለተወለደ ህፃን ልጅ ስም የማውጣት መብት፤ የእናት ወይስ የአባት? - የሕግ ባለሙያዎች ወግ
በ፦ አቤል ልዑልሰገድ አበበ

ከሰሞኑ በአንድ ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ዓቃቢያነ ሕግች፣ የሕግ ምሁራን እና የሴቶች መብት አቀንቃኞች የተገኙበት የሴቶች እኩልነት እና ሰብዓዊ መብቶች በሚል ርእስ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ተገኝቼ ሳለሁ፤ አንዲት ተሳታፊ ጠበቂት ሃሳቧን ስታጋራ ለህፃን ስያሜ የመስጠት መብት የወላጆች የጋራ መብት ነው ብላ በደፈናው ተናግራ ስትጨርስ የውይይቱ መሪ ይህን ሀሳብ በሕግ የተደነገገ መብት ነው ብላ ስትደግም ከተሳታፊዎች ጉርምምታ ሲበዛ ለምን አላጠራውም በሚል፤ ይህንን ንግግሯን የሚደግፍ የሕግ ማዕቀፍ ካለ በሚል ጥያቄ አቅርቤላት ነበር፡፡ አወያዪዋም የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ እና ሕገ-መንግሥቱ ይደነግጋል በማለት ምላሽ ስትሰጥ፤ በዚህ ነጥብ ላይ የጦፈ ክርክር ይነሳል፡፡

በአንድ ወገን ይህንን ስያሜ የመስጠት ቅድሚያ መብት የሚደነግገው የፍትሐብሔር ሕጉ ነው እንዲሁም በቤተሰብ ሕጉ በግልፅ የተደነገገ አንቀጽ የለም በሚል ሲቃወሙ፤ በሌላ ፀንፍ አወያዩዋን ጨምሮ ሌሎች ተሳታፊዎች ደግሞ የሴቶች እኩልነት በሕገ-መንግሥቱ ስለተደነገገ እና በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ ስር ቤተሰብን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት በጋራ መሆን አለበት በሚለው አንቀጽ ስር ይወድቃል በማለት ተከራከሩ፡፡ በመጨረሻም ከስምምነት መድረስ ሲያቅተን ጭብጥ ቀይረን ውይይቱን ቀጠልን፤ ነገር ግን እንደ አንድ የሕግ ባለሙያ ጉዳዩን የበለጠ ልመረምር ይገባል ብዬ ይህንን ዕልባት ያላገኘ ነጥብ ወደ ማውቃቸው የሕግ ምሁራን ወስጄ ሀሳባቸውን ስጠይቅ እዚህም ሁለት ጎራ የያዘ ምላሽ አገኘሁ፡፡ በዚህም የተነሳ ይህንን ነጥብ የበለጠ ለማጥራት ከሕግ ማዕቀፎቹ፣ ከመሰረታዊ የሕግ ፍልስፍና መርሆች እና ከፆታ እኩልነት አንጻር ለመመርመር ወደድኩ፡፡ ምንም እንኳ በውይይቱ አንዱን ጎራ ይዤ ስከራከር የነበረ ቢሆንም ለዚህ ፅሁፍ አላማ ሲባል ገለልተኛ ሆኜ የሁለቱንም ገራ ክርክር አካትቼ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2033-choice-of-first-name-in-ethiopia
4.5K viewsLiku Worku, 15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 16:41:55 የኢትዮጵያ ብር እና የውጭ ሀገር ገንዘብን ይዞ መገኘት/ማዘዋወር ያለው የሕግ ተጠያቂነት

በ:-ገመቺስ ደምሴ

ሀገራችን የኢኮኖሚዋ መሠረት ሆኖ የሚያገለግልና ውስን የሀገር ሀብት በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋል አስፈላጊ የሆኑ የቁጥጥር እርምጃዎችን ለመውሰድ ገንዘብ የሚያዝበትና የሚተዳደርበትን አግባብ በተመለከተ የተለያዩ ሕጎች ተደንግገው እናገኛለን፡፡ ይህንን ዓላማ ለማሳካት አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነትን እንደማስፈፀሚያ መሳሪያ አድርጋ በተለያዩ የሕግ ማዕቀፎች ውስጥ አካታ እየተገበረች በመሆኑ በቀጥታ ከወንጀል ጋር ያለውን ቁርኝት ጽሑፉ ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡

ጽሑፉ በቅድሚያ አጠቃላይ መንደርደሪያ ሀሳቦችን ለማንሳት የሚሞክር ሲሆን የገንዘብ ትርጉምን፣ የውጭ ምንዛሬ ምንነትንና ሊታዩ የሚገባቸውን የሕግ ማዕቀፎችን መነሻ አድርጎ ያትታል፡፡ በመቀጠልም የኢትዮጵያ እና የውጭ ሀገር ገንዘብን በጥሬ ገንዘብ ለመያዝና ለማዘዋወር የሚፈቀድባቸው አግባቦች ከተለያዩ የሕግ ማዕቀፎች አንፃር ለማንሳት ይሞክሯል፡፡

የተለየ ትኩረትም ከውጭ ምንዛሪ ጋር በተያያዘ ሊታዩ የሚገቡ ነጥቦችን አንስቶ የሚሞግትና የሚያስገነዝብ አፃፃፍን ተከትሏል፡፡ ጽሑፉ በሕግ ከተቀመጠው አግባብ ውጭ ገንዘብ መያዝና ማስተላለፍ የሚያስከትለውን የወንጀል ተጠያቂነትን አጉልቶ በማንሳት የሚስተዋሉ የአረዳድና የአተረጓጎም ክፍተቶችን ሽፋን ሰጥቶ ካነሳ በኋላ ሊያዝ የሚገባውን ተገቢ አረዳድና አተረጓጎማቸውን አንስቶ ይሞግታል፡፡ በመጨረሻም ጽሑፉ ማጠቃለያ ሃሳቦችን ጨምቆ ለማስቀመጥ ሞክሯል፡፡

Enjoy reading!

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2032-money-holding-limit-in-ethiopian-law
6.1K viewsLiku Worku, 13:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 12:50:28 ከባድ አታላይነት የሙስና ወንጀል፣ የሕግ ማዕቀፋ እና አተገባበሩ

ይህ ጽሑፍ ከባድ አታላይነት የሙስና ወንጀል በኢትዮጵያ ያስዳስሰናል።

ጸሐፊው፦ ገብረእግዚአብሔር ወልደገብርኤል

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2031-fraudulent-misrepresentation-under-corruption-laws-in-ethiopia
6.0K viewsLiku Worku, 09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-07 13:38:47 የፌዴራል ጠበቆች ምዝገባ - መራዘሙን ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማኅበር በአባልነት ላቀፋቸው ጠበቆች አስፈላጊውን አገልግሎት በመስጠት ኃላፊነት እና ግዴታውን ለመወጣት ይችል ዘንድ እስከ ሚያዝያ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ

1. በድህረ-ገጽ በኦንላይን በዚህ አድራሻ http://t.ly/RzWs ወይም
2. በፍትሕ ሚኒስቴር ዋና መ/ቤት ወይም በአራዳ ምድብ ችሎት በሚገኘው የማኀበሩ ጽ/ቤት በአካል በመገኘት
እንድትመዘገቡ መጠየቁ ይታወሳል።

በዚህ መሠረት በርካታ ጠበቆች በኦንላይን እና በአካል በመገኘት ምዝገባቸውን አከናውነዋል።

ምዝገባው እንዲከናወን የታሰበበት ጊዜ የበዓል ቀናት የተበራከቱበት መሆኑን በመገንዘብ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች ለመመዝገብ ያልቻሉ ጠበቆች ምዝገባውን እንዲያከናውኑ ተጨማሪ ቀን መስጠት አስፈላጊ እንደሆነ ማኅበሩ አምኗል።

በዚህ መሠረት ያልተመዘገባችሁ የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች በሙሉ የምዝገባ ጊዜው

ከሰኞ ከግንቦት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 26 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ መሆኑን አውቃችሁ ምዝገባችሁን እንድታከናውኑ ማኅበሩ ያሳስባል።

በኦንላይን ለመመዝገብ ይህንን ሊንክ ይጫኑ፦ http://t.ly/RzWs

በአካል ተገኝተው ለመመዝገብ፦
1. የጥብቅና ደብተርዎን መያዝዎን አይዘንጉ፤
2. የጥብቅና ደብተርዎን የፊት ገጽ እና ፈቃድዎ የታደሰበትን የሚያሳየውን ክፍል ኮፒ አድርገው መያዝዎን አይዘንጉ
3. ለማኅበሩ ገቢ ያደረጉበትን የባንክ ስሊፕ መያዝዎን አይዘንጉ፤
4. የግብር መለያ ቁጥር መያዝዎን አይርሱ፤

የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማኅበር
11.0K viewsLiku Worku, 10:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-27 12:25:30 የጦር መሣሪያ አስተዳደርና ቁጥጥር አዎጅ ቁጥር 1177/2012፡ መንግስት በፉጨት የጠራውን በጅራፍ የገረፈበት ሕግ

በ፡ ዳግም አሠፋ

ይህ ጽሑፍ የጦር መሣሪያ አስተዳደር ቁጥጥር አዎጅ ቁጥር 1177/2012 የአተገባበር አድማስን ከሁኔታዎች ጋር ያገናዝባል።
መልካም ንባብ!

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2030-firearm-administration-and-control-proclamation-of-ethiopia
11.9K viewsLiku Worku, 09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 13:30:22 የፌዴራል ጠበቆች ምዝገባ

የፌዴራል ጠበቆች ማኅበር በአዋጅ ቁጥር 1249/2013 አንቀጽ 57 ጥር 15 ቀን 2014 ዓ.ም መሠረት መቋቋሙ ይታወቃል። በመሆኑም የማናቸውም እና የመጀመሪያ ደረጃ የተሰጣቸው የፌደራል ፍ/ቤቶች ጠበቆች እንዲሁም የጥብቅና ድርጅቶች በአባልነት ያቀፈ ሲሆን ማንኛውም ጠበቃ ወይም የጥብቅና ድርጅት የጥብቅና ፍቃድ ሲሰጠው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የማኅበሩ አባል እንደሚሆን በአዋጁ በግለጽ ተደንግጎ ይገኛል። በመሆኑም የፌዴራል ጠበቆች ማኀበር በሥሩ ያሉትን ጠበቆች መመዝገብ፣ መረጃቸውን በአግባቡ መያዝ እና ማደረጃት እንዲሁም ለሌሎች አስፈላጊ አገልግሎቶች ማዘጋጀት ተቀዳሚ ተግባሩ ነው።

ስለሆነም የዚህ ምዝገባ ዓላማ በፌደራል ደረጃ የሚገኙ እና ፍቃድ የተሰጣቸው የማናቸውም እና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤቶች ጠበቆችን እና የጥብቅና ድርጅቶችን ምዝገባ በማድረግ መረጃዎቻቸውን አደራጅቶ መያዝ እንዲሁም ለአበል ጠበቆች ደረጃውን የጠበቀ መታወቂያ መስጠት ነው።

ምዝገባው የሚካሔደው በዋናነት በኦንላይን ሲሆን ይህም ጠበቆች ባሉበት ሆነው ትክክለኛ መረጃቸውን በእጃቸው በያዙት ስልክ ወይም በኮምፒወተር እንዲያስመዘግቡ ሲሆን በኦንላይን ማስመዝገብ ለማይችሉ ደግሞ በተመረጡ ሁለት ቦታዎች ማለትም በፍትሕ ሚኒስቴር ዋና መሥሪያ ቤት እና በፍትሕ ሚኒስቴር አራዳ ምድብ በአካል ተገኝተው ማስመዝገብ የሚችሉበት መንገድ ተመቻችቷል።

ምዝገባውን በኦንላይን ለማስመዝገብ ይህንን ሊንክ ይጫኑ፡

t.ly/RzWs (ይህ ሊንክ በየትኛውም ጊዜ ይሠራል)

ለምዝገባው የሚያስፈልገውን አንድ ሺ ብር በሞባይል ስልክዎ ወይም በመረጡት የሞባይል መተግበሪያ ወደማኅበሩ የሒሳብ ቁጥር ለማስገባት ይችላሉ። ያስገቡበትን ማስረጃ (ስክሪን ሾት፣ የባንክ ስሊፕ ወይም ማናቸውንም ማስረጃ) ማያያዝ ይችላሉ።

የማኅበሩ የሒሳብ ቁጥር፦ 1000469494218 (ንግድ ባንክ)

ምዝገባውን እስከ ሚያዚያ 28 ቀን 2014 ድረስ ያከናውኑ፤

ይህንን መረጃ ለሌሎች ጠበቆች ያጋሩ
11.8K viewsLiku Worku, 10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 13:17:25 t.ly/RzWs
8.6K viewsLiku Worku, 10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ