Get Mystery Box with random crypto!

የኢትዮጵያ ብር እና የውጭ ሀገር ገንዘብን ይዞ መገኘት/ማዘዋወር ያለው የሕግ ተጠያቂነት በ:-ገመ | abyssinialaw.com

የኢትዮጵያ ብር እና የውጭ ሀገር ገንዘብን ይዞ መገኘት/ማዘዋወር ያለው የሕግ ተጠያቂነት

በ:-ገመቺስ ደምሴ

ሀገራችን የኢኮኖሚዋ መሠረት ሆኖ የሚያገለግልና ውስን የሀገር ሀብት በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋል አስፈላጊ የሆኑ የቁጥጥር እርምጃዎችን ለመውሰድ ገንዘብ የሚያዝበትና የሚተዳደርበትን አግባብ በተመለከተ የተለያዩ ሕጎች ተደንግገው እናገኛለን፡፡ ይህንን ዓላማ ለማሳካት አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነትን እንደማስፈፀሚያ መሳሪያ አድርጋ በተለያዩ የሕግ ማዕቀፎች ውስጥ አካታ እየተገበረች በመሆኑ በቀጥታ ከወንጀል ጋር ያለውን ቁርኝት ጽሑፉ ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡

ጽሑፉ በቅድሚያ አጠቃላይ መንደርደሪያ ሀሳቦችን ለማንሳት የሚሞክር ሲሆን የገንዘብ ትርጉምን፣ የውጭ ምንዛሬ ምንነትንና ሊታዩ የሚገባቸውን የሕግ ማዕቀፎችን መነሻ አድርጎ ያትታል፡፡ በመቀጠልም የኢትዮጵያ እና የውጭ ሀገር ገንዘብን በጥሬ ገንዘብ ለመያዝና ለማዘዋወር የሚፈቀድባቸው አግባቦች ከተለያዩ የሕግ ማዕቀፎች አንፃር ለማንሳት ይሞክሯል፡፡

የተለየ ትኩረትም ከውጭ ምንዛሪ ጋር በተያያዘ ሊታዩ የሚገቡ ነጥቦችን አንስቶ የሚሞግትና የሚያስገነዝብ አፃፃፍን ተከትሏል፡፡ ጽሑፉ በሕግ ከተቀመጠው አግባብ ውጭ ገንዘብ መያዝና ማስተላለፍ የሚያስከትለውን የወንጀል ተጠያቂነትን አጉልቶ በማንሳት የሚስተዋሉ የአረዳድና የአተረጓጎም ክፍተቶችን ሽፋን ሰጥቶ ካነሳ በኋላ ሊያዝ የሚገባውን ተገቢ አረዳድና አተረጓጎማቸውን አንስቶ ይሞግታል፡፡ በመጨረሻም ጽሑፉ ማጠቃለያ ሃሳቦችን ጨምቆ ለማስቀመጥ ሞክሯል፡፡

Enjoy reading!

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2032-money-holding-limit-in-ethiopian-law