2022-12-30 15:54:29
ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ
በ፡ ሙሉቀን ሰይድ ሐሰን
በዚህ ጽሑፍ ጋብቻ በተጋቢዎቹ የግልና የጋራ ንብረት ላይ ስለሚኖረው ውጤት እንዲሁም በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የግል ወይም የጋራ ሊባል ሲለሚችልበት የሕግ አግባብ፤ በተጋቢዎቹ መካከል የሚደረግ የስጦታ ውል ሕጋዊ ውጤቱና የአደራረግ ስነ ስርዓቱ፣ በትዳር ውስጥ የወጣ ወጪ ለትዳር ጥቅም ዋለ ሊባል ስለሚችልባቸውና የማይቻልባቸው ሁኔታዎች ከፌዴራሉ የቤተሰብ ሕግ እንዲሁም ከሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ ውሳኔዎች አንጻር በተመረጡ የንብረት አይነቶች በመከፋፈል ዳሰሳ ተደርጓል፡፡ በጽሑፉ፦
- የግል ወይም የጋራ ንብረት ለማለት መሰረቱ
- የግል ንብረት
- ቤትና ይዞታን በተመለከተ
- ይዞታው ከጋብቻ በፊት በምሪት የተገኘ ሆኖ ቤቱ ግን በጋብቻ ውስጥ በጋራ የተሰራ በሆነ ጊዜ
- የአንደኛው ተጋቢ የግል የሆነ ቤትን በጋብቻ ውስጥ ባልና ሚስቱ እድሳት ካከናወኑ
- ከጋብቻ በፊት አንደኛው ተጋቢ ተበድሮ ቤት ቢሰራ እና ብድሩ በጋብቻ ጊዜ ከጋራ ሀብት ( ደመወዝ) ቢከፈል ቤቱ የጋራ? ወይስ የግል ሊባል ይገባል?
- በውርስ በተገኘ ንብረት ምትክ በካሳ መልክ ከመንግስት በተሰጠ ገንዘብ የተሰራ ቤትን በተመለከተ
- የስጦታ ውል በባልና ሚስት መሀከል የሚደረግበት የሕግ አግባብ
- ለትዳር ጥቅም የዋለ ገንዘብ
- የኮንዶሚኒየም ቤት
- የንግድ ፈቃድ
የሚሉ ነጥቦችን ይዟል።
መልካም ንባብ!
https://www.abyssinialaw.com/blog/joint-and-personal-property-of-spouses-under-ethiopian-law
1.4K viewsLiku Worku, 12:54