Get Mystery Box with random crypto!

Abel Birhanu የወይኗ ልጅ

የቴሌግራም ቻናል አርማ abe11 — Abel Birhanu የወይኗ ልጅ A
የቴሌግራም ቻናል አርማ abe11 — Abel Birhanu የወይኗ ልጅ
የሰርጥ አድራሻ: @abe11
ምድቦች: ስራ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.46K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው! ለሃሳብ አስተያየት ይህንን ይጠቀሙ!
@abel21bot

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-09-29 16:03:45 የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ ፦

- ቤንዚን በሊትር 57 ብር ከ05 ሳንቲም፣

- ነጭ ናፍጣ በሊትር 59 ብር ከ90 ሳንቲም

- ኬሮሲን በሊትር 59 ብር ከ90 ሳንቲም መሆኑ ተገልጿል፡፡

ይህ ማስተከከያ ከመስከረም 18 ቀን 2015 ዓ.ም እኩለ ሌሊት 6:00 ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።

ሌሎች የነዳጅ ውጤቶች ማለትም የአውሮፕላን ነዳጅ ፣ ቀላል ጥቁር ናፍጣና ከባድ ጥቁር ናፍጣ ባሉበት እንዲቀጥሉ መወሰኑን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገልጿል።

በሌላ በኩል አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በተረዘጋው የታለመ ድጎማ አሠራር ታቅፈው ሕዝቡን እንዲያገለግሉ የተመረጡት የሕዝብ ትራንስፖርት ተሽክርካሪዎች በሚጠቀሙት ነዳጅ ላይ በ2ኛው ምዕራፍ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አልተደገረም።

ሚኒስቴሩ እነዚህ ተሽከርካሪዎች በሐምሌ ወር በተወሰነላቸው ዋጋ ፦
- ቤንዚን በብር 41.26 በሊትር
- ነጭ ናፍጣን በብር 40.86 በሊትር እየገዙ እንዲቀጥሉ ብቻ ሳይሆን ከእጥፍ በላይ ያደገ ድጎማ ከመንግሥት እንዲያገኙ የተደረገ ስለሆነ በሚቀጥለው ጊዜ ዋጋ እስኪሻሻል ድረስ በሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ምንም ዓይነት ጭማሪ አይደረግም ብሏል።

ምንጭ፦ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር / ኢብኮ
4.4K views13:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-27 15:48:42
ተወዳጁ ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ አረፈ።

ተወዳጁ ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ባደረበት ህመም ምክንያት ማረፉን የቅርብ ወዳጆቹ ገልጸዋል።

በድምጻዊው ህልፈት የተሰማውኝ ሐዘን እየገለጽኩ ለቤተሰቦቹ፡ ለአድናቂዎቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ይመኛል።
5.1K views12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 14:24:14

4.0K views11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 12:22:34
ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል አሉ

➯በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መስከረም 11 አንድ ግለሰብ ከሚስቱ እጅ ሞባይል መንትፎ ሲሮጥ በቁጥጥር ስር ውሏል።

➯ጉዳዩ እንዲህ ነው የአካባቢያቸውን ጸጥታ ለመጠበቅ የተሰማሩ አካላት (ሮንድ ጠባቂዎች) በምሽት አንድ ግለሰብ ከተበዳይ እጅ ሞባይል መንትፎ ሲሮጥ ተመልክተው ግለሰቡን ተከታትለው በቁጥጥር ስር በማዋል ለፖሊስ ያስረክባሉ።

➯በዚህን ግዜ ታዲያ ጉድና ጅራት ከወደኋላ ነው እንዲሉ አበው ግለሰቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ሞባይሉን የዘረፈው ከራሱ ሚስት ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
5.2K views09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 12:33:53

11.8K views09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 14:11:04
የማይናማሯ የቀድሞ መሪ አዉንግ ሳንሱኪ በምርጫ ማጭበርበር የ 3 ዓመት ፍርድ ተፈረደባቸዉ፡፡

➯ይህ የ 3ዓመት ፍርድ ከዚህ በፊት በወታደራዊዉ የማይናማር መንግስት በተፈረደባቸዉ 17 ዓመት የእስር ጊዜ ላይ የሚጨመር ነዉ፡፡

➯ሳንሱኪ በምርጫ ማጭበርበር ወንጀል የ3 ዓመቱ ፍርድ ከከባድ የስራ ጫና ጋር የተፈረደባቸዉ ሲሆን፣ ከዚህ በፊት በተለያዩ ወንጀሎች ከተፈረደባቸዉ የ 17 ዓመት እስር ላይ የሚጨመር መሆኑም ነዉ የተገለጸዉ፡፡

➯ሳንሱኪ በ2020 ህዳር ወር ላይ በተደረገዉ ምርጫ ላይ ፓርቲያቸዉ በከፍተኛ የበላይነት አሸንፏል በማለት ምርጫ አጭበርብረዋል ነዉ የተባለዉ ፡፡

➯በዚህ ወንጀል የተነሳ በተፈረደባቸዉ ፍርድ ሳንሱኪ ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት ከፖለቲካዉ ርቀዉ ይቆያሉ የተባለ ሲሆን፣ ወታደራዊዉ መንግስት በሳንሱኪ ዙሪያ ከዚህ በኋላ የሚከሰዉ እና ለፍርድ የሚያቀርባቸዉ ብዙ ወንጀሎች አሉት ነዉ የተባለዉ፡፡

➯የኖቤል ሽልማት ተሸላሚዋ እና የማይናማር ተቃዋሚ ፓርቲ ቀንደኛ መሪ አዉንግ ሳንሱኪ ባለፈዉ ዓመት በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣን መዉረዳቸዉ የሚታወስ ነዉ፡፡

➯ወታደራዊ መንግስቱ ወደ ስልጣን ከመጣ ወዲህ በተፈጠሩ ግጭቶች ከ 2ሺህ 200 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ህይወታቸዉን ያጡ ሲሆን ፣ ከ 15ሺህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ለእስር ተዳርገዋል ሲል የዘገበዉ አልጀዚራ ነዉ፡፡

#Ethio Fm
152 views11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 17:23:48
የቀድሞዋ የሶቪየት ህብረት መሪ ሚሀይል ጎርባቾቭ በ91 አመታቸው አረፉ
የተለያዩ የዜና አውታሮች የሩሲያ የዜና ወኪሎችን ጠቅሰው እንደዘገቡት  የመጨረሻው የሶቪየት ህብረት መሪ ሚሀይል ጎርባቾቭ በሞስኮ ማዕከላዊ  ሆስፒታል ነው ያረፉት።
«ግላስኖስት» እና «ፔሬስትሮይካ» በመባል የሚታወቁትን የተሃድሶ እንቅስቃሴዎች በሶቭየት ህብረት የመሩት  ጎርባቾቭ በ91 አመታቸው ነው ከዚህ አለም በሞት የተለዩት።
የሆስፒታል ባለስልጣናትን ጠቅሰው የተለያዩ የዜና አውታሮች ትናንት ማምሻውን እንደዘገቡት ጎርባቾቭ “በአስቸጋሪ እና ለረዥም ጊዜ በቆየ ህመም” ነው ህይወታቸው ያለፈው።
ጎርቫቾቭ በ53 ዓመታቸው በጎርጎሪያኑ 1985 የኮሚኒስት ፓርቲ ዋና ፀሃፊ ሆነው የሰሩ ሲሆን፤  ፓርቲው እስኪፈርስ እስከ1991 ዓ/ም ቀጥለዋል።  ብዙም ሳይቆይ ደግሞ ሀገራቸው ሶቪየት ህብረት ፈራርሳለች።
የሶስተኛውን የአለም ጦርነት አስቀርተዋል በሚል የሚወደሱት ጎርቫቾቭ በጎርጎሪያኑ 1990  የሰላም የኖቤል ሽልማት አግንተዋል።
የጎርቫቾቭን ህልፈት ተከትሎ ተከትሎ የዩኤስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን “አስደናቂ ራዕይ” ያላቸው ሰው በመሆናቸው እና ሀገራቸውን በተሃድሶ ጎዳና በመምራታቸው ትልቅ ክብር እንደነበራቸው ተናግረዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ጎርባቾቭን ታላቅ ፣ቁርጠኛ እና ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ለሰላም ጠበቃ የሆኑ መሪ ሲሉ ገልፀዋቸል።
ጎርባቾቭ በሞስኮ ኖቮዴቪቺ መቃብር  ስፍራ ከባለቤታቸው  አጠገብ ዘላለማዊ እረፍት እንደሚያደርጉም  ዘገባዎች ያሳያሉ ።

DW Amharic
4.3K views14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 10:32:18
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 'የአፍሪካ ተወዳጁ አየር መንገድ' ሽልማትን አሸነፈ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ2022  'የአፍሪካ ተወዳጁ አየር መንገድ' ሽልማትን ማሸነፉን አስታወቀ፡፡

ግሎባል ትራቭል ማጋዚን  'ትሬዚስ አዋርድ' በተሰኘው ውድድር ድምጽ የማሰባሰብ ሂደት አየር መንገዱ አሸናፊ የሚያደርገውን ድምጽ አግኝቷል፡፡

አየር መንገዱ ሽልማቱን ያሸነፈው በተከታታይ ለ3ኛ  ጊዜ መሆኑን የሽልማቱ አዘጋጅ አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድም  በደንበኞቻችን ዘንድ የአፍሪካ ተመራጩ አየር መንገድ እንድንሆን ድምጻቸውን ስለሰጡን እናመሰግናለን ፤ ኩራትም ይሰማናል ብሏል፡፡

አየር መንገዱ ሽልማቱን ያሸነፈው በተከታታይ ለ3ኛ  ጊዜ መሆኑን የሽልማቱ አዘጋጅ አስታውቋል፡፡

#EBC
8.5K views07:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 08:14:50
የቤት ኪራይ ለቀጣይ ስድስት ወራት መጨመር አይቻልም ተባለ፡፡

የመኖርያ ቤት ኪራይ መጨመርም ይሁን ተከራይን ማስወጣት የሚከለክለው ደንብ ለቀጣይ ስድስት ወራት ተራዘመ፡፡

የመኖርያ ቤት ኪራይ መጨመርም ይሁን ተከራይን ማስወጣት የሚከለክለው ደንብ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት መራዘሙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታዉቋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዜጎች ላይ የሚደርሰውን የኑሮ ጫናን ለመቀነስ በመኖርያ ቤት ተከራዮች ላይ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ እና ተከራይን ማስለቀቅን የሚከለክል ደንብ አውጥቶ ተግባራዊ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

ይህም ደንብ በተለያየ ጊዜ እየተራዘመ ላለፈው አንድ አመት ተግባራዊ ተደርጎ ቆይቷል፡፡

ስለሆነም የከተማ አስተዳደሩ አሁን ያለውን አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታ እና የህብረተሰቡን የኑሮ ጫና ከግምት ባስገባ ወቅቱን በአብሮነትና በመተሳሰብ ለማለፍ ይረዳ ዘንድ ይህ ደንብ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት እንዲራዘም ወስኗል፡፡

በመሆኑም ይህንን ክለከላ በመተላለፍ ተከራዮችን የሚያስወጡ እና የኪራይ ዋጋን የሚጨምሩ አካላት ላይ ማህበረሰቡ በ 9977 አጭር ቁጥር  ጥቆማውን ለከተማ አስተዳደሩ ማድረስ እንደሚችል አስታዉቋል፡፡

#Ethio Fm
8.8K views05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 14:56:47 ሁሌ የምናያቸው ጥቅማቸውን አስበናቸው የማናውቃቸው 6 አስገራሚ ነገሮች

14.7K views11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ