Get Mystery Box with random crypto!

Abel Birhanu የወይኗ ልጅ

የቴሌግራም ቻናል አርማ abe11 — Abel Birhanu የወይኗ ልጅ A
የቴሌግራም ቻናል አርማ abe11 — Abel Birhanu የወይኗ ልጅ
የሰርጥ አድራሻ: @abe11
ምድቦች: ስራ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.46K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው! ለሃሳብ አስተያየት ይህንን ይጠቀሙ!
@abel21bot

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-03-12 23:08:54 https://www.facebook.com/100068357883456/posts/531449619143630/
2.2K views20:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 12:37:07 https://www.facebook.com/100068357883456/posts/528910009397591/
574 views09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 21:01:19 https://www.facebook.com/100068357883456/posts/527560409532551/
3.7K views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-19 08:09:27 https://rumble.com/v267vqm-we-need.html
2.2K views05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 20:33:52 የስራ ማስታወቂያ

የስራ ዓይነት - ፕሮግራም አቅራቢ እና ሎኬሽን ማናጀር

መስፈርት
ፕሮግራም ማቅረብ እና የቀረፃ ቦታ ማመቻቸት የሚችል ቶሎ ተግባቢ ፈጣን የሆነ ልምድ ያለው ቢሆን ይመረጣል ባይሆንም ችግር የለውም

ፆታ አይለይም

ደሞዝ በስምምነት

መወዳደር የምትፈልጉ ሙሉ ስም ችሎታችሁን አድራሻችሁን ፎቷችሁን በማያያዝ በኢሜል abelentertainment0@gmail.com ወይም በዚህ ፔጅ ኢንቦክስ ማድረግ ትችላላችሁ ።

Abel Entertainment
Addis Abeba
3.0K viewsedited  17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-11 11:30:43

3.8K views08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 12:22:49

4.3K views09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 10:38:56
በመዲናዋ የስነጥበብና የሳይንስ ሙዚየም በዛሬው ዕለት ይመረቃል

➯ማክሰኞ መስከረም 24 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በመዲናዋ አዲስ አበባ አስደናቂ የቀለበት ቅርጽ ያለው ህንጻ እና ማራኪ የጉልላት ቅርጽ ያለው ተደርጎ የተገነባው ማዕከል እንዲሁም በአይነቱ አዲስ የሆነው የስነጥበብና የሳይንስ ሙዚየም በዛሬው ዕለት ይመረቃል።

➯ሙዚየሙ በ7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፤ በኪነ-ህንጻ ንድፍ ውስጥ ያካተተው ክብ ቅርጽም በማያቋርጥ እድገት ውስጥ ያለን እድገትና የሰው ልጆችን ጥበብ የሚያመለክት ነው ተብሏል።

➯በተጓዳኝም ኢትዮጵያ በአስገራሚ ፍጥነት በማደግ ላይ ካለው ቴክኖሎጂ ጋር ለመጣመር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይም እንደሆነም ተነግሯል።

የስነ ጥበብና የሳይንስ ሙዚየሙን አስደናቂ የሚያደርገው ምንድነው?

➯ሙዚየሙ በጥንቃቄ የተዘጋጁ የመኪና ማቆሚያዎች በተጨማሪ በዙሪያው ካሉ የከተማችን ፓርኮች ጋር የሚያገናኘው ውብ የእግረኛ መንገዶች ያሉት ነው።

➯ ትልቁ ህንጻ ከ15 ሺሕ ሜትር ካሬ በሚበልጥ መሬት ላይ ያረፍ ሲሆን፤ አጠቃላይ ሥፋቱ 132 ሜትር ያህል ነው።

➯ ከተፈጥሮ ስርዓት ጋር ተስማሚ በሆነ መንገድ ሃይል ከሚያመነጩ የውሃ ግድቦቻችን እንዲሁም በጣሪያው ላይ ከተገጠሙ የጸሀይ ብርሃን ሰብሳቢ መሣሪያዎች የሚያስፈልገው የኤሌክትሪክ አቅርቦት የሚያገኘው ይህ ሙዚየም ተፈጥሮአዊ የሃይል ማስተላለፊያዎችንና ሃይል ቆጣቢ የተፈጥሮ ብርሃንን የሚጠቀም ነው።

➯ይህ የስነጥበብና የሳይንስ ሙዚየም ትላንታችንን፣ ዛሬያችንን እና ነገአችንን በአንድ ላይ አሰናስኖ ሳይንስን ጥበባዊ በሆነ መንገድ፤ ጥበብን ደግሞ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ የሚያስቃኝ በመሆኑ አስደማሚ ተሞክሮዎችና አዳዲስ እውቀቶች የሚቀሰሙበት እንደሚሆንም ኢብኮ ዘግቧል።

#አዲስ ማለዳ
1.9K views07:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 10:08:36 በመዲናዋ የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል ተከብሮ እስኪጠናቀቅ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ተደረጉ

በአዲስ አበባ ከተማ የሚከበረው የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል በሰላም እንዲከበር የፀጥታ አካላት ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቀው ወደ ሥራ መግባታቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል።

የምስጋና፣ የፍቅር፣ የሰላምና የይቅርታ በዓል የሆነው እና በዓለም የትምህርት፣ ሳይንስና የባህል ድርጅት /ዩኔስኮ/ በማይዳሰሱ በዓለም ዓቀፍ ቅርስነት የተመዘገበው የገዳ ስርዓት አካል የሆነው የኢሬቻ በዓል በአገራችን በብሄራዊ ደረጃ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በመከበር ላይ ይገኛል።

በርካታ ህዝብ የሚታደምበት እና አባገዳዎች፣ አደ ስንቄዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚገኙበት የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል መስከረም 21 ቀን 2015 በልዩ ድምቀት በአዲስ አበባ ይከበራል፡፡ በዓሉ በሰላም እንዲከበር መላው የፀጥታ አካላት ዝግጅታቸውን አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል።

የአዲስ ዓመትና እና የመስቀል በዓል አከባበር የነበሩ ጠንካራና ያጋጠሙ ክፍተቶች ተለይተው ለኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል በሰላም መከበር ጠቃሚ ግብዓቶች መወሰዳቸውንም ግብረ ኃይሉ ጨምሮ ገልጿል።

ከዚህም በተጨማሪ ለወንጀል መከላከል ተግባር ልዩ ትኩረት በመስጠት አብዛኛውን የሰው ኃይል በወንጀል መከላል ሥራ ላይ መሰማራቱንና በዓሉ ወደ ሚከበርበት ስፍራ የሚመጡ ታዳሚዎች ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ መኖሩን ተገንዘበው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ ጠይቋል።

በያዝነው ዓመት በርካታ ህዝብ የታደመባቸው ልዩ ልዩ ሃይማኖታዊና ብሄራዊ በዓላት በሰላም እንዲከበሩ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ወሳኝ ሥራ ማከናወኑን ግብረ ኃይሉ አስታውሶ፤ የዘንድሮው የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል በሰላም እንዲከበር የበዓሉ ታዳሚዎች እና የከተማው ነዋሪ የተለመደውን ትብብራቸውን እንዲያደርጉ በፀጥታ አካላት ሥም ጥሪውን አስተላልፏል።

በተመሳሳይ ዜና የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል ተከብሮ እስከሚጠናቀቅ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር እና አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገድን እንዲጠቀሙ ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

በዚህም መሰረት፡-
=> ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒዬም አዳራሽ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ወሎ ሰፈር አደባባይ

=> ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ 22 ማዞሪያ

=> ከ4ኪሎ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኮንሰን መስቀለኛ ወይም ወዳጅነት ፓርክ

=> ከፒያሳ በቸርቸር ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ

=> ከጦር ሃይሎች በለገሃር ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት

=> ከጀሞ በትንባሆ ሞኖፖል ወደ ሜክሲኮ የሚወስደው መንገድ አፍሪካ ህብረት አደባባይ

=> ከቄራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚሄደው መንገድ ቡልጋርያ ማዞሪያ

=> በአዲሱ መንገድ ከቄራ በቂርቆስ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ታቦት ማደሪያ

=> ከሳሪስ ፣ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ጎተራ ማሳለጫ

=> ከቦሌ ወደ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ አትላስ ሆቴል አካባቢ

=> ከአዋሬ ወደ ካሳንቺዝ የሚወስደው መንገድ ሴቶች አደባባይ

=> ከልደታ በጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ የሚወስደው መንገድ አብነት ፈረሰኛ ፖሊስ አካባቢ

=> ከመርካቶ በጎማ ተራ ወደ አምስተኛ የሚወስደው መንገድ በርበሬ በረንዳ

=> ከመርካቶ በራስ ቴአትር ወደ ጎማ ቁጠባ ተክለ ሃይማኖት አደባባይ

ከአርብ መስከረም 20 ቀን 2015 ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለጊዜው ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናል።

በዓሉ በሚከበርበት ዙሪያ እና በአካባቢው በግራና በቀኝ ለረጅም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

በመጨረሻም ህብረተሰቡ የፖሊስን አገልግሎት ለማግኘትም ሆነ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት መረጃ ለመስጠት በ991 ወይም 816 ነፃ የስልክ መስመሮችን እና 01-11-11-01 -11፣ 01-11-26-43-59፣ 01-11-01-02-97፣ መጠቀም እንደሚችል እና ለፀጥታው ሥራ ስኬታማነት ህብረተሰቡ እያደረገ ላለው ቀና ትብብር የአዲስ አበባ ፖሊስ በመላው የፀጥታ አካላት ስም ምስጋናውን እያቀረበ በዓሉ የሰላምና የደስታ እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል።
(አዲስ ማለዳ)
6.6K views07:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 16:04:42 የአርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ
*************************

የአርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስተ ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።

በስርዓተ ቀብሩ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የሙያ ባልደረቦቹ እንዲሁም አድናቂዎቹ ተገኝተዋል።

ዛሬ ጠዋት በአርቲስቱ መኖሪያ ቤት ቤተሰቦቹ፣ የሙያ ባልደረቦቹ፣ አድናቂዎቹ በተገኙበት በሃይማኖታዊ ሥርዓት ተከናውኖ የአስከሬኑ ሽኝት ተከናውኗል።
4.3K views13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ