የአርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ ************************* የአርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስተ ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል። በስርዓተ ቀብሩ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የሙያ ባልደረቦቹ እንዲሁም አድናቂዎቹ ተገኝተዋል። ዛሬ ጠዋት በአርቲስቱ መኖሪያ ቤት ቤተሰቦቹ፣ የሙያ ባልደረቦቹ፣ አድናቂዎቹ በተገኙበት በሃይማኖታዊ ሥርዓት ተከናውኖ የአስከሬኑ ሽኝት ተከናውኗል። 4.3K views13:04