Get Mystery Box with random crypto!

የጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ እውነተኛ ደጋፊዎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ abdisira — የጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ እውነተኛ ደጋፊዎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ abdisira — የጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ እውነተኛ ደጋፊዎች
የሰርጥ አድራሻ: @abdisira
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.46K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-07-17 00:26:31
88 views21:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 21:14:49
"የህዝብ አመኔታን መቼም ቢሆን አንዘነጋም፤ ክብራችን ህዝብን በፍትሃዊነት ማገልገል ስለሆነ !!"

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

ሌቦችና እምነታቸውን ሸጠው የሚበሉ ሁሉ ለጊዜው ቢታግሉንም አያሸንፉንም፤ እውነት ምንግዜም ታሸንፋለች!!
ከሁሉም በላይ ፈጣሪ ረድቶን የህዝብን ሀብት በቴክኖሎጂ ዉንብድና ከመዘረፍ ማዳን ችለናል ።

የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ አወጣጥ ስራ ላይ አጠራጣሪ ጉዳዮች ከገጠሙ ጊዜ አንስቶ በማጣራት ሂደት ለደገፋችሁን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ፣ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የኢኖቨሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርንና የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትን ከልብ ላመሰግን እወዳለሁ።

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
335 views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 20:02:29
ከ14ኛ ዙር የ20/80 እና ከ40/60 3ኛ ዙር እጣ ማውጣት ጋር በተያያዘ ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮና የቤቶች ቢሮ የተለያየ እርምጃ የተወሰደባቸው አመራሮችና ባለሙያዎችን ስም ዝርዝር ይፋ ተደረገ።

በዚህም መሰረት፦

1ኛ. ዶ/ር ሙሉቀን ሃብቱ ቢሮ ሃላፊ ከሃላፊነታቸው የተነሱ

በቁጥጥር ስር የዋሉ፡-

1ኛ. አብርሀም ሰርሞሎ የዘርፉ ምክትል ቢሮ ሃላፊ

2 ኛ . መብራቱ ወልደኪዳን፦ ዳይሬክተር

3ኛ. ሀብታሙ ከበደ፦ ሶፍትዌር ባለሙያ

4ኛ. ዬሴፍ ሙላት፦ ሶፍትዌር ባለሙያ

5ኛ. ጌታቸው በሪሁን፦ ሶፍትዌር ባለሙያ

6ኛ. ቃሲም ከድር፦ ሶፍትዌር ባለሙያ

7ኛ. ስጦታው ግዛቸው፦ ሶፍትዌሩን ያለማ

8.ኛ. ባየልኝ ረታ፦ ሶፍትዌር ተቆጣጣሪ

9ኛ. ሚኪያስ ቶሌራ ፦ የቤቶች ኢንፎሜሽንና ቴክኖሎጂ ባለሙያ

10ኛ .ኩምሳ ቶላ፦ የቤቶች ኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ዳሬክተር

(የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር)

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
334 views17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 19:41:08
293 views16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 19:41:07 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዛሬው እለት ሀምሌ 01/ 2014 የወጣውን የ 20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
በመግለጫውም ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ፤ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው ፤ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት የአጣሪ ቡድን መሪ አቶ በሀይሉ አዱኛ መግለጫውን በጋራ ሰጥተዋል፡፡

በዚህ መግለጫ የከተማ አስተዳደሩ ከኢንሳ፤ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፤ እንዲሁም ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አጣሪ ቡድን እንዲቋቋም ተደርጎ ወደ ማጣራት ስራ በመግባት ሲጣራ ቆይቶ በዛሬው እለት በጋዜጣዊ መግለጫው ይፋ ተደርጓል፡፡

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ያነሷቸው ነጥቦች ከዚህ እንደሚከተሉት ናቸው፡-

በጋዜጣዊ መግለጫው ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት የጋራ መኖርያ ቤት እጣ በማውጣት ሂደት ባጋጠመን ችግር ህዝቡንም ከተማ አስተዳደሩንም ያሳዘነ ድርጊት መፈፀሙን አንስተዋል፡፡

በዚህ አንገብጋቢ ጉዳይ ላይ ህብረተሰቡ በትእግስት በመጠበቅ እንዲሁም የጀመርነውን ጥረት ከጎናችን በመቆም ላሳየው ጥረት ከልብ እናመሰግናለን ብለዋል፡፡

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ለህዝባችን ቃል በገባነው መሰረት ችግር ቢያጋጥም እንኳን በቀጥታ ኦዲት እናደርጋለን ብለን በገለፅነው መሰረት ጥቆማ ስለደረሰ ጊዜ ሳንሰጥ በሚመለከታቸው አካላት የማጣራት ስራ እንዲጀመር አስደርገናል፡፡

የቴክኖሎጂ ውንብድና አጋጥሞናል፡ አመራር የመራው ውንብዳ ነው፡፡ በዚህ ሂደት የቤት ስርቆት ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ፍላጎት ጭምር መግለፅ ይቻላል ብለዋል፡፡
 የዚህ ስራ ሌላው አላማ መንግስት ህዝብን ማገልገል ብቃት የለውም የሚል ገፅታ ለመፍጠርና ህብረተሰቡ በመንግስት ላይ እንዲያምፅ ለማድረግ በማሰብ ነው በማለት ከንቲባ አዳነች ገልፀዋል፡፡

በዚህ ሂደት ችግር እንዳጋጠመን ማጣራት መጀመራችን ህዝብን ሃብት መታደግ እንድንችል አድርጎናል፡፡ ህዝቡን መታደግ ችለናል፡፡

ህብረተሰቡም መብቱን ለማስጠበቅ ያደረግነውን ጥረት ተረድቶናል፡፡ እኛም ድሃውን ማህበረሰብ መታደግ በመቻላችን ያስደስተናል፡፡

የቀረበልን ሪፖርት በሚገባ ሲስተሙ ተቆጣጣሪ ጭምር እንዳለውና አስተማማኝ እንደነበረ ነበር፡፡ ይህንንም ለማመን ምክንያቶች ነበሩ፡፡ ምክንያቱም ከዚህ በፊት በዚህ ቡድን የለሙና ጥቅም ላይ የዋሉ ሲስተሞች ነበሩ፡፡

ማረጋገጫ ለማግኘት የተሄደበትና ተቋም ለተቋም የተደረጉ ግንኙነቶችም ችግር ነበረባቸው፡፡ ሰዎች ለሰዎች የተደረጉ ግንኙነቶች አይነት የተደረጉ ግንኙነቶችም መመልከት ተችሏል፡፡

ኢንሳ ማረጋገጫ ሰጥቶ እንደነበርም በወቅቱ ተገልፆ ነበር ነገር ግን ህጋዊ በሆነ ደብዳቤ ኢንሳ ያረጋገጠው እንዳለሆነ ታይቷል፡፡

ዳታው በሰዎች አጅ ለአምስት ቀን ያህል መቆየቱና ይህም የተከናወነው በሃላፊዎች ትእዛዝ እንደነበር ገልፀዋል

ነገር ግን የምዝገባው ዳታውን በቴሌግራም ጭምር ሲላላኩ እንደነበር በኋላ በምርመራ መታወቁን

በሂደቱም እጣ ቁጠባ ያቋረጡ ሰዎች ፤ቁጠባቸውን ከረሱበት ቦታ ጭምር እጣ እንዲወጣላቸው መደረጉን

የማጣራት ሂደቱን እጣ የወጣ እለት ከሰዓታት በኋላ መጀመሩን ከንቲባ አዳነች ገልፀዋል፡፡

ይህ የማጣራት ሂደት ኢንሳ አራት ባለሙያዎች መወከሉንና ከዚህ በተጨማሪም ከሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ከብሄራዊ ደህንነት የተዋቀረ ኮሚቴ በኢንሳ አስተባባሪነት ስራውን ሲሰራ መቆየቱን ገልፀዋል፡፡

ቴክኖሎጂዎች ለመጠቀም ያደረግነውን ጥረት ወደፊትም አጠናክረን እንቀጥላለን፤ ቴክኖሎጂዎችን የሚያለማው ሰው ቢሆንም ወደፊት በረቀቀ የሙያ ስልት እጣ አወጣጡን ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን እናድርጋለን

እዚህ በግልፅ ማንሳት የምንፈልገው በወቅቱ የተሰጠን ማብራርያ ከእውነቱ የራቀ መሆኑን በባለሙያዎች ጭምር ተረጋግጧል፡፡

ባለሙያዎችና አመራሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ እንዲሁም አንድ ሃላፊና አንድ ምክትል ሃላፊ ከሃላፊነታቸው ተነስተዋል፡፡

ሌሎች እርምጃዎች እንደ ሚዛኑ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ አሁንም ቆራጥ አቋሙ ህዝቡን መብት ማስከበረት መሆኑን ይህንን ቤት ለህዝብ ለማቅረብ ከ21 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ጭምር የጎደለውን መሰረተ ልማት በሟሟላት ለህዝብ ማድረሱን

በፍትሃዊነት ህዝብን ሃብት ለማድረስና የኋላ የኮንዶሚኒየም መጥፎ ታሪክን ላለመድገም ከፍተኛ ፍላጎት ነበረን፡፡ አሁንም ይቀጥላል፡፡

አሁንም ተቋም ግንባታ አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡

ስለሆነም በዚህ ሁሉ ችግር እና ሂደት የወጣን እጣ ተዓማኒነት ስለሌለው እጣው ሙሉ ለሙሉ ውድቅ እንዲሆን አድርገናል፡፡

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
357 views16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 17:34:07
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሐምሌ 1 ቀን 2014 የወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ ውድቅ አደረገ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ ባሳለፍነው ሐምሌ 1 ቀን 2014 የወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውድቅ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ዝርዝር መረጃውን በተከታይነት የምናቀርብ ይሆናል

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
11 views14:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 21:30:42 ሀምሌ 01/ 2014 የወጣውን የ 20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ይመለከታል::

በከተማችን አዲስ አበባ ከሚስተዋሉ ችግሮች መካከል አንዱ የቤት አቅርቦት እጥረት ሲሆን ይህንኑ ደረጃ በደረጃ ለማቃለል አስተዳደሩ የተለያዩ አማራጮችን ነድፎ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

የዚህ ሂደት አካል የሆነው የነባሩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ያሉበትን ወስብስብ ችግር ለይቶ በመፍታት ተመዝጋቢዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ እና የቤት እጥረት ጫና ለመቀነስ የተደረገው ሰፊ ጥረት ተጠቃሽ ነው፡፡
በዚህ ሂደት በግንባታ ላይ የነበሩ 20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል 25,491 ያህሉ በቅርቡ ለባለ እድለኞች የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት መካሄዱ ይታወቃል፡፡

ይህ የቤት ማሰስተላለፍ ስራ እንደ ከዚህ በፊቱ በቆጣቢወች መካከል አድሎና ብልሹ አሰራር እንዳይኖር ለማድረግ ግልፅነት በሚያሰፍን አግባብ ለማስተላለፍ ሲባል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራ በመስራት ሂደቱን ግልጽና አሳታፊ ለማድረግ የተደረገው ተነሳሽነትና ጥረት እንዲሁም የባልሙያዎችን ሙያዊ ነፃነት አክብረን አስፈላጊውን ሂደት ተከትለን ተዓማኒነቱን እንዲያረጋግጡልን አድርገን ነበር:: በዚህ ሂደት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ አዲስ ሶፍትዌር እንዲበለፅግ እና ስለሶፍትዌሩ ታአማኒነት የኢኖቬንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር እንዲያረጋግጥልንም ተደርጓል::
በቀጣይም ከሁለት ጊዜ በላይ ታዛቢወች እና ባለሙያወች ፊት ቀርቦ እንዲያረጋግጡልን ተደርጎ ማረጋገጫ ሰጥተዋል::
ይህ ሁሉ ሂደት ከእለት ጉርሱ የቆጠበዉን እና በከፍተኛ ጉጉት የሚጠባበቀውን ሕዝብ በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ ቀና ሃሳብ እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል::
ይሁን እንጂ ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ስንጀምር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነቶች ተግኝተዋል::
በመሆኑም በእስካሁኑ የማጠራት ስራ ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል፡፡

ከዚህ በመነሳትም የቤት ማስተላለፉን ሂደት ግልፅነት ለማስፈን ሲባል እና ውጤቱን የሚያዛባ ተግባር ሲያጋጥም መልሰን ኦዲት እንዲደረግ በገባነው ቃል መሰረት የተፈጠረውን ችግር ከጉዳዩ ገለልተኛ በሆኑ በሚመለከታቸው ተቋማት የማጣራት ስራ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በጉዳዩ የተጠረጠሩ ባለሙያዎች እና አመራር በቁጥጥር ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገ ይገኛል::

ስለሆነም ሂደቱን በአጭር ጊዜ አጠናቀን ለቤት ተመዝጋቢዎችና ለመላው የከተማችን ነዋሪ የምናሳውቅ መሆኑን ስንገለጽ ተመዝጋቢዎች እንደተለመደው በከፍተኛ ትዕግስት እንድትጠባበቁ እናሳውቃለን፡፡

ለተፈጠረው ስህተት የከተማ አስተዳደሩ በዚህ አጋጣሚ ይቅርታ ይጠይቃል
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ሐምሌ 4/2014 ዓ/ም

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
255 views18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 21:30:40
237 views18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 01:40:15
ሳሩ እንጂ ገደሉ የማይታያቸው ቆሞ ቀሮች!
ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስትን መቅጣት የሚቻለው በምርጫ ካርድ ብቻ ነው! ህዝባችን ለብልጽግና ፓርቲ ድምጹን ሰጥቶ በህዝብ የተመረጠ መንግስት ተመስርቷል! በዚህ ሂደት ውስጥ ከመጀመሪያው ጀምሮ በቋሚነት በቋሚ ተቃውሞ የሚታወቁ እንደ ጅብ የፊት የፊታቸውን ብቻ የሚያዩ ቁሞ ቀሮች እያንዳንዱን አጋጣሚ ለራሳቸው የፖለቲካ ትርፍ ሲሉ ሀገርን ለእርድ የሚያመቻቹ "ሳሩን እንጂ ገደሉ የማይታያቸው ቆሞ ቀሮች ዛሬም ከመስከረም 30 በኋላ መንግስት የለም ነጠላ ዜማ ላይ ናቸው! ጅል አንድ ዘፈን ነው የሚያውቀው እንዲሉ አበው በምርጫ ያላገኙትን የመንግስት ስልጣን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን አስይዘው ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላት ጋር ከመጋረጃ ጀርባ ይዶልታሉ .. . እኛም እንመከራለን የኢትዮጵያን የመንግስት ስልጣን በሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ይሁንታ እንጂ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ሲፈልጉ የሚሰጡት ሲፈልጉ የሚወስዱት ተራ ኃላፊነት አይደለም !
መንግስት ህዝብ የሰጠውን ኃላፊነት ተጠቅሞ ለህዝብ ቃል የገባውን ካልፈጸመ ፤ በየአምስት አመቱ የሚደረገውን የምርጫ መርሃ ግብር የተሻለ ሀሳብ ይዞ በመቅረብ ሀሳብን ሽጦ መንግስት ሁኖ መመረጥ የሚያስችልን ዕድል መጠቀም ይቻላል! ከዚህ ውጭ በሆነ መንገድ በኋይል የህዝብን አደራ በግርግር ለሌባ አሳልፎ የሚሰጥ ደካማ መንግስት አለመኖሩን ያሰባችሁትን በሃይል ማሳካት ሳትችሉ ስትቀሩ ይገባችኋል! በተጨማሪ ለተቃውሞ እና ለአመጽ ከሚወጣው ህዝብ በእጥፉ ለድጋፍ እና መንግስቱን ለመጠበቅ እንደሚወጣም መዘንጋት የለበትም!
አለቀ ደቀቀ
የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
621 views22:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 01:39:56
የቀብር ሳጥን ነጋዴዎች Vs ETHIO 360!
የቀብር ሳጥን መሸጫ ሱቆች ባለቤት ጠዋት ወደ ስራ ሲሄዱ "ፈጣሪ ሆይ ሰው እንዳይሞት አድርግ" ብለው ሊፀልዩ አይችሉም። "የዛሬውን ገበያ አድራልኝ" ነው የሚሉት፤ ይህም ሰው ይሙት ማለትነው።
ሞት በሚበዛ ወቅት ፒያሳ ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ ቢዝነስ ይደራል። የሞተባቸው አዝነው ባለ ሱቆቹ ተደስተው ማየት የዘወትር ትእይንት ነው። በዚህኛው ገበያ ሰው ወደ ሱቆቹ የሚሄደው ሰው ሲሞትበት እንጂ ሞት ፍለጋ አይደለም።
የዩቲዩብ ሚዲያዎች ጥሩ ገንዘብ የሚከፈላቸው ብዙ ተመልካች ሲያገኙ መሆኑ ይታወቃል። ጥሩ ተመልካች የሚያገኙት ሰው ሲሞት በመሆኑ እንደ ቀብር ሳጥን ነጋዴዎቹ "ፈጣሪ ሆይ ሀገራችንን ሰላም አድርግልን፤ ሰው አይሙት" ብለው ሊፀልዩ አይችሉም። ለምሳሌ በቅርብ በነበረው የዜጎች ሞት ኢትዮ360 ከ200ሺ በላይ ተመልካች አግኝቶ ነበር፤ ገቢም ደርቶለታል። ሞት ለሚያው ቢዝነስ ነው። ብዙ ጊዜ ኢትዮ360 ሞት ሲበዛ ብዙ ተከታይ መኖሩን ስለሚያውቁም ሮጠው 'GoFundMe' ከፍተው ተከታዮቹን እርዱኝ ማለትም ያዘወትራሉ።
በመሆኑም ለቀብር ሳጥን ነጋዴዎቹ እና የኢትዮ360 አይነት ሚዲያዎች ሞት ቢዝነሳቸው ነው፤ እንዳይቋረጥም ይፀልያሉ።
ከደንበኞቻቸው አንፃር ሁለቱም ጋር የምንሄደው ሰው ሲሞትብን መሆኑ ቢያመሳስላቸውም ከቀብር በኃላ ግን ሳጥን ቤት ዳግም አንሄድም። ሚዲያዎቹ ጋር ግን ከቀብር በኃላም ለሌላ ሞት ፍለጋ ደግመን መሄዳችን ከሞት ጋር ሱስ የያዘን መሆኑን ነው የሚያረጋግጠው።

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩየጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ እውነተኛ ደጋፊዎች1/
531 views22:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ