Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 127.33K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 490

2021-02-05 15:01:45
የተፈናቀሉ ዜጎች በምርጫው የሚሳተፉበት አሰራር መዘጋጀቱን ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ገለጹ፡፡

የተፈናቀሉ ዜጎች በ6ኛው አገራዊ ምርጫ የሚሳተፉበት አሰራር መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ገለጸዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ”ይጠይቁ” በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የማህበራዊ ሚዲያ የተሳትፎ መድረክ ለቀረቡ ጥያቄዎች በቦርዱ የፌስቡክ ገጽ በቀጥታ ምላሽ ሰጥተዋል።

የተፈናቀሉ ዜጎች በምርጫው በምን አይነት መልኩ ይሳተፋሉ? በሚል ከተሳታፊ ለተነሳው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ የተፈናቀሉ ዜጎች በምርጫው ላይ የሚሳተፉበትን ሁኔታ ቦርዱ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል። ዜጎቹ ባሉበት ቦታ ሆነው የሚመዘገቡበትና ከመጡበት አካባቢ በሚኖሩ ሰዎች ምርጫውን የሚያደርጉበት ሁኔታ መመቻቸቱን አመልክተዋል።

ምርጫ ቦርድ የተፈናቀሉት ዜጎች የሰጡትን ድምጽ ከመጡበት አካባቢ ሰዎች ከሚሰጡት ድምጽ ጋር የሚደመርበት የውጤት ማስላት ዘዴ ማዘጋጀቱን ተናግረዋል። በአዲስ መልክ ዜጎች የተፈናቀሉባቸው ቦታዎች በመኖራቸው የወቅቱን መረጃዎች ማወቅ እንደሚያስፈልግም ገልፀዋል። ለዚህ ደግሞ የሰላም ሚኒስቴርና የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይ.ኦ.ኤም) የሚያወጧቸውን መረጃዎች መሰረት በማድረግ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የተፈናቀሉ ዜጎች ባሉባቸው አካባቢዎች ለመራጮች ትምህርት ለመስጠት፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ምልመላና ሌሎች በተጓዳኝ የሚከናወኑ ስራዎች የሚመሩበት እቅድ መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።

[Arts TV]
@Yenetube @FikerAssefa
13.8K viewsedited  12:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-05 14:52:27
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያየ የትምህርት ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 5 ሺህ 117 ተማሪዎች ነገ ያስመርቃል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ በልዩ ልዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 5 ሺህ 117 ተማሪዎች ነገ ቅዳሜ ጥር 29/2013 ዓ.ም በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ፣ በስፔሻሊቲ እና ፖስት ግራጁዬት ዲፕሎማ ያስመርቃል፡፡በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ትምህርት ለማስቀጠል የ2012 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን ብቻ ጠርቶ በ15 አካዳሚክ ክፍሎች ማካካሻ ትምህርት ሲሰጥ እንደቆየ ነው የዩቨርሲቲው የኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮምዩኒኬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውዱ እምሩ (ዶክተር) የተናገሩት፡፡

[AMMA]
@YeneTube @FikerAssefa
10.3K views11:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-05 13:23:51
በየመን የአልቃይዳ መሪ በቁጥጥር ስር ውሏል ተባለ!

የተባሩት መንግስታት ድርጅት በየመን የአልቃይዳ መሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታወቀ፡፡የድርጅቱ የክትትል ቡድን ትናንት ሃሙስ ለጸጥታው ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት ካሊድ ባታርፊ በቁጥጥር ስር ከዋለ መቆየቱን ጠቁሟል፡፡ባታርፊ ከዓመት በፊት ነበር የሽብር ቡድኑን እንዲመራ የተመረጠው እንደ አረብ ኒውስ ዘገባ፡፡ምክትሉ ሰዓድ አቲፍ አል-አውላቂ አል ማህራህ ግዛት ውስጥ በምትገኘው ጋይዳ ከተማ ተካሂዶ በነበረው ዘመቻ መገደሉንም ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በኦሳማ ቢን ላደን እና አጋሮቹ መመስረቱ የሚነገርለት አልቃይዳ የጸጥታው ምክር ቤትን ጨምሮ በአሜሪካ እና በሌሎችም ሃገራት በሽብርተኝነት መፈረጁ የሚታወስ ነው፡፡ቢንላደን አሜሪካ በባራክ ኦባማ የስልጣን ዘመን ባካሄደችው ዘመቻ በፓኪስታን አቦታባድ መገደሉም አይዘነጋም፡፡

[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
10.6K views10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-05 13:20:18
የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳዳር ከአፍሪካ ኅብረት ጋር ጠንካራ ትስስርን እንደገና ለመገንባት ቁርጠኛ መሆኑን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስታወቁ፡፡

በውጭ ጉዳይ ፖሊሲያቸው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ገለፃ ካደረጉ በኋላ በሰጡት አስተያየት ባይደን ከአፍሪካ ኅብረት ጋር ያለውን ትስስር እንደገና እንደሚገነቡት ቃል ገብተዋል፡፡ቀዳሚያቸው ዶናልድ ትራምፕ ከ2 ዓማት በፊት ‹‹አፍሪካዊያንን የማይረቡ አገራት ያሉበት አኅጉር›› ሲሉ መግለፃቸው ቁጣን ቀስቅሶ እንደነበርና ኅብረቱን ከዩናይትድ ስቴትስ ማራራቁ ይታወቃል፡፡ምንም እንኳን ትራምፕ ‹‹እኔ ዘረኛ አይደለሁም›› ሲሉ ሊያስተባብሉ ቢሞክሩም በተግባር ግን ለጥቁር ቆዳ ቀለም ሕዝቦች ያላቸው ጥላቻ በተለያየ ጊዜ ሲገለጥ ኖሯል፡፡ነጩን ቤተ መንግሥት የተረከቡት ባይደን ግን ከኅብረቱ ጋር የነበረውን ጠንካራ ትስስር እንደሚመልሱት ነው የገለፁት፡፡ፕሬዝዳንቱ አክለውም ኅብረቱ በአኅጉሪቱ ያሉ ግጭቶችን በመፍታት ጠንካራ እንዲሆን እገዛ እንደሚያደርጉ ነው ያሳወቁት፡፡ዩናይትድ ስቴትስና አፍሪካ በባራክ ኦባማ ዘመንም ጠንካራ ትስስር ነበራቸው፡፡

Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
10.1K viewsedited  10:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-05 13:13:45
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ለዘንድሮው ምርጫ 435 የምርጫ ወረዳዎች ማቋቋሙን ይፋ አደረገ፡፡

ፓርቲው በዘንድሮ አመት ለሚካሄደው ሃገራዊ ምርጫ እያከናወነ ያለውን ተግባር አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ፓርቲው በሁሉም የሃገሪቱ አካባቢዎች መዋቅሩን የመዘርጋት ስራ እያከናወነ መሆኑን የተናገሩት የኢዜማ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ ፓርቲው በዘንድሮ አመት የሚካሄደው ምርጫም ኢትዮጵያን ወደ ዴሞክራሲዊ ምዕራፍ ያሸጋግራታል ብሎ እንደሚያምን ገልጸዋል፡፡

አሁን ላይ አስፈላጊውን ሁሉ የምርጫ ፓርቲው እያከናወነ መሆኑን የገለጹ ሲሆን ከ435ቱ የምርጫ ወረዳዎች በ406ቱ የምርጫ ወረዳዎች ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለክልል ምክር ቤት እና ለወረዳ የሚሳተፉ እጩዎች አስመርጦ ማጠናቀቁንም አቶ ዘላለም ተናግረዋል፡፡

ለሚካሄደው ምርጫ ማስፈጸሚያ የሚሆን የገንዝብ ድጋፍ ፓርቲው እያሰባሰበ መሆኑን የሚናገሩት የኢዜማ ምክትል መሪ አቶ አንዱአለም አራጌ በማዕከል ደረጃ ብቻ 140 ሚሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡

በሌላ በኩል ከፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በኪራይ ያገኘውንና በ5 ሚሊየን ብር እድሳት የተደረገለትን የፓርቲውን ዋና ጽህፈት ቤት ፓርቲው ይፋ አድርጓል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
13.3K views10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-05 13:13:23
ለጓደኛ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለሙሽሮች እና ለተመራቂዎች ለየት ያለ ስጦታ መስጠት ይፈልጋሉ?
#join

@giftsoflovee
@giftsoflovee

+251914839754
+251936871620
#ኣድራሻችን፡ 4 ኪሎ: ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ
5.8K views10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-05 13:13:23
የዋሪት የውሀ ማጣሪያ ከ15% ልዩ ቅናሽ ጋር

ሰብስቤ www.sebsibie.com በመግባት መገበየት ይችላሉ።

ሰብስቤ ሁሉንም ሰብስቦ በአንድ ላይ የያዘ የግብይት ድረገፅ

ከ3,200 በላይ ዕቃዎች

@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com

0953707070

Dedicated online shopping platform
6.5K views10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 22:58:53
14.0K viewsedited  19:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 21:12:07
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 749 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተያዙ፡፡

ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 6,002 የላብራቶሪ ምርመራ 749 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡

ባለፋት 24 ሰዓታት የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 2,126 አድርሶታል።

በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 254 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር 124,242 አድርሶታል፡፡

በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 140,157 ደርሷል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
18.0K views18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 20:30:17 የሱዳን ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት በምዕራብ አርማጭሆ ሰላም በር ከተባለ አካባቢ የተፈናቀሉ ሰዎች እስካሁን ተገቢ መጠለያ አላገኘንም ሲሉ አማረሩ።

እንደተፈናቃዮቹ ከወራት በፊት በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ መኖሪያ አካባቢቸውን ቢለቁም ተገቢ የመጠለያ ድጋፍ አልተደረገላቸውም፡፡የከተማ አስተዳደሩ ከዚህ በፊት መጠለያ ሰትጫቸዋለሁ ቢልም ተፈናቃዮች ግን በቂ እንዳልሆነ ተናግረው ነበር፡፡ የአማራ ክልል አደጋ መከላከል፣ ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ኮሚሽነር ዘለዓለም ልጅለም በበኩላቸው 1ሺህ 800 ያህል ተፈናቃዮች መኖራቸውን የሚያመለክት መረጃ እንደደረሳቸው አመልክተው አጠቃላይ ጉዳዩን የሚያጠና ቡድን ነገ ወደ ቦታው እንደሚሄድም ተናግረዋል፡፡

[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
16.8K views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ