Get Mystery Box with random crypto!

✞ የማርያም ✞ ፳፩ እና ✞ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ልጆች ፲፫ ✞

የቴሌግራም ቻናል አርማ muzemur — ✞ የማርያም ✞ ፳፩ እና ✞ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ልጆች ፲፫ ✞
የቴሌግራም ቻናል አርማ muzemur — ✞ የማርያም ✞ ፳፩ እና ✞ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ልጆች ፲፫ ✞
የሰርጥ አድራሻ: @muzemur
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 270
የሰርጥ መግለጫ

 
✝💚💛❤️@muzemur💚💛❤️✝
✝💚💛❤️@muzemur💚💛❤️✝
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
“አንተ ግን አቤቱ፥ መጠጊያዬ ነህ፥ ክብሬንና ራሴንም ከፍ ከፍ የምታደርገው አንተ ነህ።” መዝ ፫፥፫
join join join
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
 ✝💚💛❤️@muzemur💚💛❤️✝
 ✝💚💛❤️@muzemur💚💛❤️✝

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-07 11:30:36 ☞ጌታ ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የሰጠው ቃልኪዳን፡፡
☞ሰው ሁሉ ወደ ሥጋዊ ተግባርም ሆነ ወደ መንፈሳዊ ተግባርም ቢሆን ሲሄድ
ይህ የመጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ነው ብሎ ቅጽሩን፤ ገራገሩን
ቢሳለም የተሳለመውን ሰው ቢኖር እኔ መንበረ መንግሥቴን አሳልመዋለሁ፡፡
☞የገድልህንም መጽሐፍ የተሳለመ ቢኖር እኔ መንበረ መንግሥቴን
አሳልመዋለሁ፡፡
☞የገድልህ የተአምርህ መጽሐፍ የተነበበትን ውኃ እኔ እንደተጠመቅሁበት እንደ
ማዮርዳኖስ አደርገዋለሁ፡፡ የገድልህ መጽሐፍ በተነበበት ውኃ የተጠመቀበት
ሰው ቢኖር የሰማንያ ዓመት ኃጢአቱን አስተሠርይለታሁ፡፡
☞ወንድን የአርባ ቀን ሴቷን የሰማንያ ቀን ሕፃን አደርጋቸዋለሁ፤እኔ
በተጠመቅሁበት ማየ ዮርዳኖስ እንደተጠመቀ ሆኖለት ከኃጢአቱ ይነጻል፡፡
☞ሰውም ሆነ እንስሳ ቢታመም በጹኑ እምነት ይደረግልኛ ብሎ አምኖ ያለ
ጥርጥር ውኃ አቅርቦ የገድልህን መጽሐፍ በላዩ ላይ አንብቦ የተነበበትን ውኃ
ቢታጠብበት ወይንም ቢጠጣ ያለ ጥፋት ፈጥኖ ከደዌው ይፈወሳል፡፡
☞የገድልህን መጽሐፍ የተነበበትን ማየ ጸሎት በቤቱ ውስጥ ቢረጭ ከዚያ ቤት
በረከቴን እመላበታለሁ፤ ተድላን፤ ደስታን፤ ጥጋብን በዚያ ቤት አሳድራለሁ፤ እሰከ
ዘላለሙ ድረስ በቤቱ ውስጥ የእህል መታጣትና ርሃብ፤ የውኃ ጥማት፤ተላላፊ
በሽታ አይገባበትም፤ፈጽሜም አላመጣበትም፡፡
☞ሥጋዬን ደሜን መቀበል ያልተቻለሁ ሰው ቢኖር ለመታሰቢያህ ዝክር
ከተደረገው ፍርፋሪ ይቅመስ፤ ሥጋዬን ደሜን እንደተቀበለ እኔ አደርግለታለሁ፡፡
☞ፍርፋሪ ባያገኝ እንጀራውና ዳቦውን የተበላበትን ገበታ፤ ጠላው የተጠጣበትን
ጽዋ በምላሱ ይላስ፤ እኔ ኢየሱስ ቃል የሚያብለው ሥጋዬን ደሜን እንደተቀበለ
አደርገለታለሀ፤ ሰለ እምነቱ ሥጋዬን ደሜን ለመቀበል የሚያበቃውና
እውነተኛውን ምግባር የጽድቅ ሥራ እንዲሠራ አደርገዋለሁ ቡሎጌታ
ለመጥምቀ መለኮት ቃል ኪዳን ስጥቷል፡፡
☞(ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ)
☞እኛም የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የቃልኪዳኑ ተከፋይ ያድርገን
በጸሎቱ ይማረን፡፡ 
@muzemur
@muzemur

“አንተ ግን አቤቱ፥ መጠጊያዬ ነህ፥ ክብሬንና ራሴንም ከፍ ከፍ የምታደርገው አንተ ነህ።” መዝ ፫፥፫
join join join

  @muzemur
  @muzemur
23 views# unknown, 08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 07:12:04
51 viewsTheotokos, 04:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 07:11:09 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
#አቡነ_ሙሴ_ጸሊም
መሴ ማለት መዋሴ፣ ዋስ፣ መሆን፣ ከችግር ማዳን፣ ከግዞት፣ከእስራት ነጻ ማውጣት ማለት ነው፡፡ አቡነ ሙሴ ጸሊም ኢትዮጵያዊ ሲሆኑ ተጋድሎአቸውን የፈጸሙት ግን በግብፅ ነው፡፡ መጀመሪያ ላይ እንደ አብርሃም በየዋህ ልቦና ሆነው ሥነ-ፍጥረትን በመመርመር እግዚአብሔር አምላካቸውን ያገኙ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ወላጆቻቸው ፀሐይ ያመልኩ ስለነበር ከልጅነታቸው ጀምሮ ኃጢአት በሠሩ ቁጥር ‹‹ተው አምላካችን ፀሐይ ይጣላሃል›› ይሏቸው ነበር፡፡ እርሳቸው ግን ሽፍታና ዘራፊ ሆኑ፡፡ እየዘረፉ ብዙ ይመገቡ ስለነበረር ከትልቅነታቸውና ከኃይለኝነታቸው የተነሳ ‹‹በግ ፈጅ›› እየተባሉም ይጠሩ ነበር፡፡
ብዙ ወርቅ ከባለ ሀብቶች ሰብስባ ለነዳያንና ለቤተ ክርስቲያን ልትሰጥ ትሄድ የነበረችን አንዲት ክርስቲያን ሴት ልጅ ሙሴና ግብረ-አበሮቻቸው ለወርቁ ሲሉ እርሷን ማርከው ወሰዷት፡፡ ማታ ላይ ስለ ውበቷ ሲያወሩ እርሷ ግን ‹‹ስምህ ማን ነው?›› ስትላቸው ‹‹ ሙሴ ነኝ›› አሏት፤ ‹‹ይሄ ስምስ እጅግ የተባረከ ነው…›› ብላ ስለ ሊቀ ነቢያት ሙሴና ስለ ክርስቶስ አስረዳቻቸው፡፡ ከዚህ በኋላ ወላጆቻቸው ስለ ፀሐይ አምላክነት ሲነገሯቸው ያደረጉትን ነገር መመርመር ጀመሩ፡፡ ‹‹ፀሐይ አምላክ ከሆነ እስከ ዛሬ ድረሰ ሽፍታና ዘራፊ ሆኜ ሰው ስገድልና ይህን ኹሉ ኃጢአት ስሠራ እንዴት ፀሐይ ሳታቃጥለኝ ቀረች? ደግሞ ፀሐይ ጠዋት ወጥታ ማታ ትጠልቃለች ይህችስ እንዴት አስገኝ ትሆናለች በራሷ አስገኚ አላት እንጂ…›› በማለት ፀሐይን ፣ ጨረቃን፣እሳትን ነፋስን በየተራ አምላክ መሆናችውንና አለመሆናቸውን ከመረመሩ ከፈተኑ በኋላ ‹‹የሁሉ አስገኚ አምላክ ተናገረኝ›› ብለው ሲጸልዩ ከሰማይ ድምጽ መጥቶላቸው ወደ ገዳም ሄደው ከአባቶች ትምህርተ ሃይማኖትን እንዲማሩ ተነገራቸውና ወደ አስቄጥስ ገዳም ሄደው መምህር ኤስድሮስ ሁሉንም ነገር አስተምረው ለማዕረገ ምንኩስና አበቋቸው፡፡
መጀመሪያ ወደ ገዳሙ ሲሄዱ ይዘርፉበትና ይቀሙበት የነበረውን ስለታም መሳሪያ እንደያዙ ስለነበር ያዩአቸው መነኰሳት ኹሉ ‹‹ሊገድለን መጣ›› አሉ፡፡ ከዚህም በኋላ ለመነኰሳቱ ሁሉ የሚላላኩ ሆኑ፡፡ ትንሹም ትልቁም ሙሴ ይሄን አድርግልኝ ይሏቸዋል እርሳቸውም ይታዘዛሉ፡፡ እራሳቸውን በትህትና ዝቅ በማድረግ በተጋድሎ እየኖሩ ታምራትን ማድረግ ጀመሩ፤ በጸሎታቸውም ዝናብ ያዘንቡ ነበር፡፡ ለቅድስና ደረጃ ከበቁም በኋላ 40 ዓመት ሙሉ ከሰው ሳይገናኙ ብቻቸውን ዘግተው ከኖሩ በኋላ ለ500 መነኰሳት አበምኔት ሆነው ተሾሙ፡፡ ቀን ወንጌል ሲያስተምሩ ይውሉና ሌሊት እየተነሱ ከበረሃ መነኰሳት ውኃ ይቀዱላቸው ነበር፡፡ አገልግሎታቸው የታይታ እንዳይሆንባቸው አረጋውያን መነኰሳት መተኛታቸውን ካረጋገጡ በኋላ የግብፅ በረሃን አቋርጠው ከሩቅ ስፍራ ውኃ እየቀዱ መነኰሳቱ ሳያዩአቸው በየደጃፋቸው ላይ ያስቀምጡላቸው ነበር፡፡ ብዙ መነኰሳትም ወደ አቡነ ሙሴ እየመጡ የሕይወትን ትምህርት ይማሩ ነበር፡፡ በአንድ ወቅት አንድ ሰው አባ ሙሴን ‹‹አንድን አገልጋይ ባጠፋው ጥፋት የተነሳ ጌታው መታው፤ አገልጋዩ ምን ማለት አለበት?›› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ አባ ሙሴም ‹‹አገልጋዩ ብጹዕ ከሆነ ፣ አጥፍቻለሁና ይቅር በለኝ ማለት አለበት›› አሉት፡፡ ‹‹ ሌላ አይጠበቅበትምን?›› ሲል ደግሞ ጠየቃቸው፡፡ ‹‹አይጠበቅበትም ፣ ለጊዜው ለጥፋቱ ኃላፊነቱን ወስዶ አጥፍቻለሁ ካለ ጌታው ይቅር ይለዋል፤ የዚህ ሁሉ አላማው በባልንጀራ ላይ አለመፍረድ ነው፡፡ በእውነቱ ጌታችን የግብፅን በኩራት ሁሉ ሲመታ ሰው ያልመታበት አንድም ቤት አልነበረም›› ብለው መለሱለት፡፡ ያም ሰው ‹‹ምን ማለት ነው?›› አላቸው፡፡ እርሳቸውም ‹‹ሁላችንም የየራሳችን ጥረቶች ካየን የባልንጀራችንን ለማየት ዕድል አንሰጥም፤ በራሱ ቤት ሰው ለመፈለግ የጎረቤት ለቅሶ አይሄድም፡፡ ለባልንጀራ መሞት ማለት ለራሱ ጥፋት ትኩረት በመስጠት፣ የሌላውን ጥፋት ከቁምነገር አለመቁጠር ነው፡፡ ማንንም አትጉዳ በማንም ላይ ክፉ አታስብ ክፉ የሚሠራውን ሰው አትናቀው በባልንጀራው ላይ ክፉ በሚሠራ ሰው ላይ አትተማመን፣ በባልንጀራው ላይ ክፉ በሚሠራ ሰው ላይ አትደሰት፣ ለባልንጀራ መዋቲ መሆን ማለት ይህ ነው፡፡ በማንም ላይ አትማረር ነገር ግን ሁሉንም እግዚአብሔር ያውቃል በል፡፡ ከሚያማ ሰው ጋር አትተባበር፣ በሐሜቱም አትደሰት፣ ወንድሙን የሚያማውን ሰውም አትጸየፈው፡፡ አትፍረድ ማለት ትርጉሙ ይህ ነው፡፡ በማንም ላይ የጥላቻ ሃሳብ አይኑርህ፣ ጥላቻ ልብህን እንዲያሸንፈውም አትፍቀድለት፡፡ ባልጀራውን የሚጠላውን አትጥላው፣ ሰላም ማግኘት ማለት ይህ ነው….›› ብለው መከሩት፡፡
በዕድሜአቸው መጨረሻ አካባቢ ቡራኬ ለመቀበል ከመነኰሳትና ደቀ መዛሙርቶቻቸው ጋር ወደ አባ መቃርስ ሄዱ፡፡ አባ መቃርስም ‹‹ልጆቼ ከእናንተ መካከል በሰማዕትነት የሚሞት አለ›› ብለው ትንቢት ሲናገሩ ሙሴ ጸሊምም ‹‹አባቴ ያ ሰው እኔ ነኝ ሰይፍ የሚያነሱ በሰይፍ ይጠፋሉ›› የሚል ቃል ተጽፎአል፤ (ማቴ 26፥52) ይህን ጊዜ በጉጉት ስጠብቀው ነበር አሏቸው፡፡ እንደተባለውም የበርበር ሰዎች ገዳሙን ዘርፈው መነኰሳቱን ሊገድሉ ሲመጡ ደቀ መዛሙርቶቻቸው ‹‹ሸሽተን እናምልጥ›› አሏቸው፤ አቡነ ሙሴ ግን ‹‹በጎልማሳነቴ ጊዜ ደም አፍስሻለሁና አሁን የኔም ደም ሊፈስ ይገባል›› በማለት እራሳቸውን ለሰይፍ አዘጋጅተው ጠበቋቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ሰኔ 24 ቀን አንገታቸውን በሰይፍ ተቆርጠው በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ የአባታችን የሙሴ ጸሊም ቅዱስ ሥጋቸው በገዳመ አስቄጥስ በክብር ይገኛል፡፡ በረከታቸው ይደርብን አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ምንጭ፦ ስንክሳር ዘሰኔ
44 viewsTheotokos, 04:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 08:07:38
53 viewsTheotokos, 05:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 08:07:28 ሰኔ 22 - "#ቅዱስ_ዻውሎስ_የዋህ"

°°°
በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ግብጽ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ቅዱሱ ስሙ ዻውሎስ ቢሆንም ብዙ ጊዜ የሚጠራው "የዋህ ዻውሊ" በሚል ነው:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ የዋህ ዻውሊ ከሕጻንነቱ ጀምሮ መጻሕፍትን የተማረ: ግን ደግሞ ትዕቢት: ቁጣና ቂምን የማያውቅ ገራገር ሰው ነበር::

°°°
ዕድሜው ለአካለ መጠን ሲደርስ ቤተሰቦቹ ሚስት አግባ አሉት:: እርሱ ባያስብበትም ወገኖቹን ላለማሳዘን አገባ:: እንዳለመታደል ሆኖ ግን ያገባት ሴት በጣም ቆንጆ በዚያም ላይ ክፉ ነበረች:: የዋህ ዻውሊ ክፋቷን ሁሉ ታግሶ ለበርካታ ዓመታት አብሮ ኖረ:: ልጆችንም አፈሩ::

°°°
አሁንም ግን እርሷ ከክፋቷ ልትታገስ አልቻለችም:: ይባስ ብላ ዻውሊ በሌለበት ከሌሎች ወንዶች ጋር ትዘሙት ጀመረች:: የዋሁ ሰው ይህንኑ ያውቃል፤ ነገር ግን የእግዚአብሔርን ሥራ ዝም ብሎ በተስፋ ይጠብቅ ነበር:: እሱ ያርሳል: ይቆፍራል: ነዳያንን ያበላል: እንግዳ ይቀበላል እንጂ ክፋትን ለማሰብ ጊዜ አልነበረውም::

°°°
አንድ ቀን ግን ለሥራ ወደ በርሃ ወጥቶ አንድ ግሩም ዜና ሰማ:: "አባ እንጦንስ ምንኩስና የሚባል ሕይወተ መላእክትን ጀምሯል: ደቀ መዛሙርትንም ይቀበላል" አሉት:: ነገር ግን ሚስትና ልጆች አሉትና ምን ያደርጋል? የዋህ ዻውሊ ሙሉ ቀን ሲሠራ ውሎ ወደ ቤቱ ሲመለስ የጠበቀው ሌላ ነው:: ሚስቱ በራሱ መኝታ ላይ ከአገልጋይ እረኛው ጋር ራቁታቸውን አገኛቸው::

°°°
ልብ በሉልኝ በትክሻው ሞፈርና ምሳር: መጥረቢያም ይዟል:: እርሱ ግን ክፉን አላሰበም:: ጥሩ ልብስ አንሥቶ ሁለቱንም አለበሳቸው:: እንዲህም አላቸው:- "ከዚህ በኋላ እኔ አልመለስም:: ሃብት ንብረቴን ውረሱ: በደስታም ኑሩ:: የልጆቼን ነገር ግን አደራ" ብሏቸው ተነሣ::

°°°
በእጁ ምንም አልያዘም:: በትከሻው ያለችውን ብጣሽ ጨርቅ ይዞ ወደ በርሀ ተጓዘ:: አባ እንጦንስም ተቀብለው አስተምረው አመነኮሱት:: ከዚያች ቀን ጀምሮ ራስን ዝቅ በማድረግ: በመታዘዝ አገለገለ:: ጾም: ጸሎትና ስግደቱንማ ማን ቆጥሮት::

°°°
እያለ እያለ ከብቅዐት ማዕርግ ደረሰ:: ምዕመናንም ሆነ መነኮሳት ሊጠይቁት ሲመጡ የእያንዳንዱ ኃጢአት በግንባራቸው ተጽፎ ይመለከት ነበርና ስለ እነሱ ሲያለቅስ ቅንድቡ
ተላጠ:: ሰውነቱም አለቀ::

°°°
አንድ ቀን ጋኔን የያዘውን ሰው ፈውስ ብለው አመጡለት:: እርሱ ግን በአጋንንት ላይ ሥልጣን እያለው በትሕትና ተጠግቶ ጋኔኑን "አባ እንጦንስን ከምጠራብህ ቀስ ብለህ ውጣ" አለው:: ጋኔኑ ግን የፈራው መስሎት በትዕቢት "እንጦንስ ማነው?"አለው::

°°°
ያን ጊዜ የዋህ ዻውሊ እንደ እሳት ከጋለ ድንጋይ ላይ ቁሞ "ሕያው እግዚአብሔር ምስክሬ ነው:: ይህ ጋኔን ካልወጣ አልወርድም" አለ:: ወዲያው በዘንዶ አምሳል ከሴትዮዋ ወጥቶ እየጮኸ ወደ ቀይ ባሕር ገባ:: ቅዱስ ዻውሊ የዋሕም እንዲህ በቅድስና ተመላልሶ በዚህች ቀን በመልካም ሽምግልና ዐርፏል::
ምንጭ፦ ገድለ ቅዱሳን

°°°
"አምላከ ቅዱሳን ልዑል እግዚአብሔር ከቅዱሳን አባቶቻችን ከጸናች ገድላቸው፣ ከበዛች ትዕግስታቸው፣ ከፍጹም ጸሎታቸውና በረከታቸው ያሳትፈን፤ ፍጻሜያችንን ያሳምርልን።"
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
51 viewsTheotokos, 05:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-18 21:14:09 ​​​​ሰኔ 12 #የቅዱስ_ሚካኤል ዓመታዊ በዓል!

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ።

በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡

ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡

ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡

ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡

ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡

በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡

ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡

ለጊዜው “በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ድረስልኝ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡

ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡

ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
94 viewsTheotokos, edited  18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 22:24:28 #ጾመ_ሐዋርያት (ሰኔ 6 - ሐምሌ 5)
(የ2014 ዓ.ም)

‹‹ይህ ጾም በአላዋቂዎችን እና በቤተክርስቲያን ጠላቶች የሽማሌዎች ጾም እየተባለ ምዕመናን እንዳይጾሙት ብዙ ተለፍቷል..››

በየዓመቱ በዕለተ ሰኑይ የሚጀምሩ ሶስት አጽዋማት ብቻ አሉ ፡፡ ከእነርሱ መካከል አንዱ ጾመ ሐዋርያት ነው ፡፡ ቅበላው በዕለተ እሑድ ይሆንና ጾሙ ሰኞ ይውላል ፡፡ የ2014 ዓ.ም ጾመ ሐዋርያት ሰኔ 6 ይገባል ፡፡

ይህ ጾም እራሱ ጌታቸን ኢየሱስ ክርቶስ ትንቢት የተናገረለት ጾም ነው፡፡
ይህ ታላቅ ጾም የዛሬ 1901 ዓመት በፊት በራሳቸው በቅዱሳን ሐዋርያት የተጀመረ ጾም ነው ፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከልም አንዱ ነው ፡፡
ፈሪሳውያ ጌታችንን ደቀ መዛሙርትህ አይጾሙም ብለው በጠየቁት ጊዜ እርሱም ‹‹ ሚዜዎች ሙሽራ ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን ? ነገር ግን መሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል ፤ በዚያ ጊዜም ይጾማሉ ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም ፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና ፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል ፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም ፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል የወይን ጠጁም ይፈሳል ፡፡አቁማዳው ይጠፋል ፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ ፡፡›› ማቴ 9 ፥ 14-17 አላቸው ፡፡ይህ ቃለ እራሱ ጌታችን መድኀኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ስለ ጾመ ሐዋርየት የተናገረው ትንቢት ነው ፡፡

‹‹#መሽራው_ከተወሰደ በኃላ›› ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኃላ ማለት ሲሆን ይህን ጾም ከዕረገት በኃላ የምንጀምረው ፤ ይህን ምሳሌ በማድረግ ነው ፡፡ አስር ቀን ዘግይቶ መጀመሩም የሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበትና ነው ፡፡

የዚህን ማብራርያ በቀጣይ ጽሁፋችን እንመለስበታልን፡፡
ይህ ጾም በአላዋቂዎችን እና በቤተክርስቲያን ጠላቶች የሽማሌዎች ጾም እየተባለ ምዕመናን እንዳይጾሙት ብዙ ተለፍቷል ልናውቅ የሚገባው ነገር ግን ሐዋርያት ዓለምን ዞረው ከማስተማራቸው በፊት ይህን ጾም ጾመዋል ፡፡ በዚህም ጌታችን የተናረው ተንቢት ተፈጽሟል፡፡ ከሰባቱ አጽዋማትን አንዱ ነው ፡፡ በዚህ ምክንያት ይህን ጾም ታላቅ እና ልዩ ያስብለዋል ፡፡ ይህንን አውቀን ሁላችንም ልንጾመው ይገባል ፡፡
101 viewsTheotokos, 19:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 08:07:32 ​​​​​​ሰንበት
ሰንበተ ክርስቲያን (እሑድ)

እሑድ ማለት ‹‹አሐደ›› ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም የመጀመሪያ ማለት ነው፡፡ ይህቺ ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን›› በመባል ትታወቃለች፡፡

ዮሐንስም በራዕዩ ‹‹የጌታ ቀን›› ያላት ናት (ራእይ 1፤10)፡፡ ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ ‹‹ዕለተ እግዚአብሔር›› የሚላት ዕለተ እሑድ ናት፡፡

ዕለተ እሑድ እንደ ሰንበት የሚከበርበት ምክንያቶች፡-

እግዚአብሔር ሥራውን የጀመረባት ለሥነፍጥረት መጀመሪያ ዕለተ (ጥንተ ዕለት) ናትና
ዕለተ ሥጋዌ ናት፡፡ ጌታ የተፀነሰባትና እርቅ የተወጠነባት የፍሰሐ ቀን፡፡
ዕለተ ትንሣኤ ናት፡፡ ጌታ ከሙታን ተለይቶ የተነሳባት ዕለት
የቤተ/ክ የልደት ቅን ናት፡፡ መንፈስ ቅዱስ ለሐዋሪያት የወረደባት ኃይልና ፅናትን ያገኙባት ዕለት
ጌታ በክበበ ትስብእት በግርማ መለኮት ዳግም በቅዱሳን መላእክቱ ታጅቦ በጌትነቱ ለፍርድ የሚመጣባት ታላቅ የፍርድ ቀን ናትና የተለያዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች የሚካሄዱባት ዕለት ናት(1ኛ ቆሮ 16፤1)
የሐዋሪያት ዘመንም በጤሮዓዳ ያሉ ክርስቲያኖች እሑድ ቀን ይሰበሰቡ ነበር (የሐዋ. 20፤7 በቤተክርስቲያን ታሪክ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዕለተ እሑድ የክርስቲያኖች ሰንበት ናት በማለት
ሥራ እንዳይሰራባት አዋጅ አስነግሮ ነበር፡፡

ምንም እንኳን ይህቺ ዕለት በሐዲስ ኪዳን መከበር የጀመረ ቢሆንም በብሉይ ኪዳን ከፋሲካ በፊት የሰንበት (የቀዳሚት) ማግስት በመባል በኩራት እና ቀዳሚያት የሚያቀርቡበት ቀን ነበር። (ራዕ 1፡10)

በቀዳሚት ሰንበት ቅዱስ እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ አርፎ ሥጋዊ እረፍትን ለሰው እንዳስተማረ በእሑድ ቀን (በሰንበተ ክርስቲያን) በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት የተገኘውን የዘላለማዊ የነፍስ ዕረፍት የምናስብበት ነው፡፡ (ዕብ 4፡1-10)

ከሰንበት ረድኤት በረከት ይካፍለን!
ሌሎች እህት ወንድሞች ይማሩበት ዘንድ አጋሩ

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
@muzemur
@muzemur
@muzemur

✞✞✞✞✞✞
✞✞✞✞✞✞

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
✞✞✞ @muzemur ✞✞✞

✞✞✞✞✞✞
✞✞✞✞✞✞
@Muzemur
@muzemur
@muzemur
175 viewsTheotokos, edited  05:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 05:35:17
የእግዚአብሔር ልጅ ግን ያለ መሰለል በሚንቦገቦግ የደመና ተን ዐረገ …… ኪሩቤል ሊያሳርጉት አልመጡም እርሱ ራሱ በመለኮት ኃያል አብን ተካክሎ በቀኝ በኩል ተቀመጠ የማረጉም ምስጋና ለእኛ መሰላል ሆነን። ከገሊላ ሴት እንደተወለደ ባሰብን ጊዜ ወደ አባቱ አንዳረገ እናስተውላለን በጭኖቿ እንደ ታቀፈ ስናስታውስ በአባቱ እቅፍ እንዳለ እናስባለን በደብረ ዘይት ከደቀመዛሙርቱ ጋር እንደተቀመጠ ባሰብነው ጊዜ በመላእክቱ እልልታ እንዳረገ በወላጁም ቀኝ እንደተቀመጠ እናስታውስዋለን።

(መጽሐፈ ምስጢር ገጽ330)
@muzemur
@muzemur
@muzemur

✞✞✞✞✞✞
✞✞✞✞✞✞

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
✞✞✞ @muzemur ✞✞✞

✞✞✞✞✞✞
✞✞✞✞✞✞
@Muzemur
@muzemur
@muzemur
114 viewsTheotokos, edited  02:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 05:08:47 #ዕርገተ_እግዚእነ
እንኳን ለጌታችን 1980ኛው በዓለ ዕርገት፤ ኀሙስ ግንቦት 25/2014 ዓ.ም. አደረሳችሁ፥ አደረሰን፤
‹‹አልቦ ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ ዕጓለመሕያው፤ ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፡፡›› እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው፡፡ ዮሐ.3፥13

* የሰውን ልጅ በመውደዱ ልዑል ባሕርዩን ዝቅ አድርጎ ከሰማይ ወረደ፥ ሥጋ ለበሰ፥ በምድር ላይ ተመላለሰ፥ ምድርን በኪደተ እግሩ ቀደሰ፥ ድውያንን ፈወሰ፡፡
* ፍጹም ሰው እንደ መሆኑ ተራበ፥ ተጠማ፤ ፍጹም አምላክ መሆኑንም ያስረዳ ዘንድ አምስት ገበያ ሕዝብ በአምስት እንጀራ በሁለት ዓሣ አጠገበ ማቴ.14፥19፡፡
* መምህረ ትሕትና ነውና ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር በዚህ ዓለም ኖረ ለሐዋርያት ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ወንጌልን አስተማረ፤ ትምህርት በሚገባ ከተረዳለት በኋላ ለድኅነተ ዓለም በማዕከለ ምድር በቀራንዮ ተሰቀለ፡፡#ወገብረ_መድኀኒተ_በማዕከለ_ምድር_በምድር_መካከል_መድኀኒትን_አደረገ_እንዲል _መዝ.73፥12
* ነቢያት እንደተናገሩ በሞቱ ዓለምን አድኖ ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር አድሮ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ብርሃነ መለኮቱን ገልጾ ተነሣ፡፡ የተተነበየውን ትንቢት ፈጽሞ ተነሣ፡፡
* በሞቱ ሞታችንን ሻረልን፤ ‹‹በሞቱ ሞትን አጠፋው›› እንዲል መጽሐፈ ኪዳን፡፡ ሕንፃ መነኰሳት ‹እርሱ በሁሉ ምሉዕ ሲሆን በመቃብር ለመቀበር ዮሴፍ ኒቆዲሞስ ገንዘውት ታየ፡፡ ከመሬት ውስጥ በመቀበሩም ሙስና መቃብርን አጠፋ፤ ከሥሩም ነቀለው ከተነሣ በኋላ ትንሣኤውን መጀመሪያ ለማርያም መግደላዊት ገለጸ ማር.16፥9፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ትንሣኤው ሲመሰክር ‹‹ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፤ ተቀበረም፤ መጽሐፍ እንደሚል፤ በሦስተኛው ቀን ተነሣ፡፡ ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፡፡ ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ›› 1ቆሮ.15፥3-8 ብሎ ክርስቶስ ትንሣኤውን ለተከታዮቹ በሙሉ የገለጠ መሆኑን መስክሯል፡፡

*የሚያምኑ ፈሪሳውያንም ‹‹ትንሣኤው ምትሐት ነው›› እንዳይሉ እየታየ እያስተማረ እስከ 40 ቀን ድረስ መቆየቱን ይገልጽልና፡፡ በዚህም የአርባ ቀን ከትንሣኤ በኋላ ቆይታው ሦስት ቀን ጉባኤ አድርጎ ደቀ መዛሙርቱን እንዳስተማረ ቅዱስ ወንጌል ይነግረናል፡፡ ኢየሱስ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ሲገለጥላቸው ይህ ሦስተኛ ጊዜ ነበረ እንዲል ዮሐ.21፥14 ይህንም ሊቃውንት አባቶቻችን፡-

1ኛ) *የትንሣኤ
2ኛ) *የአግብኦተ ግብር /ዳግም ትንሣኤ/
3ኛ) *የጥብርያዶስ፡፡
በዚህ 40 ቀን ቆይታ መጽሐፈ ኪዳንን ለደቀ መዛሙርቱ አስተምሯል፡፡

* ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስም ዕርገቱን ለመናገር ከሰማየ ሰማያት መውረዱን አስቀድሞ ከሰማይ ከወረደው ከሰው ልጅ በቀር ማንም ወደ ሰማይ የወጣ የለም እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው ብሎ ከዕርገቱ በኋላ በየማነ አብ፥ በዘባነ ኪሩብ ፥ ወደ ሰማይ የወጣ ከእርሱ በቀር ሌላ እንደሌለ አስረግጦ ነገረን፡፡ ሲጀምር ከሰማይ መውረዱን ማስቀደሙ ወረደ ብሎ ዐረገ ለማለት ይመቻል፡፡ ተጸነሰ ተወለደ ለማለት ጥንቱ ከሰማያት ወረደ ማለት እንደሆነ ሁሉ፤ ‹‹ተሰቀለ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፤ ተነሣ›› ለማለት ‹‹ጥንቱ፤ ተጸነሰ፥ ተወለደ፥ አደገ፥ ተመላለሰ፥ ሠላሳ ዓመት ኖረ›› የሚለው ነው፡፡ ስለሆነም ቅዱስ ዮሐንስ ጠርዝና ጠርዙን ይዞ ተናገረ፡፡

* ‹‹ወረደ ዐረገ›› የሚሉት ሁለት ቃላት የዓለም ድኅነት መነሻና መድረሻ ናቸው፤ እነዚህን ሁለት ቃላት ስናይ በሁለቱ መካከል የተፈጸሙትን የአምላክ ሥራዎች ልብ ማለት ይገባል፡፡ ቤት በመሠረት ይጀመራል በጣሪያ ይፈጸማል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ይህን የቤዛነት ሥራ ሲያስረዳ በዮሐ.1፥14 ‹‹ቃል ሥጋ ኮነ፤�ቃል ሥጋ ሆነ›› ብሎ ጀምሯል፤ ይህንንም ቃል ‹‹ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም›› በማለት ሰው መሆኑን ብቻ ሳይሆን በአርያም የሚኖር መሆኑን አስተማረን፡፡ እንግዲህ ጌታችን ዕርገት እንዲሁ እንደ እንግዳ ደራሽ ፥ እንደ ውኃ ፈሳሽ አለመሆኑን ቀድሞ በነቢያት የተነገረ፤ ኋላም በሐዋርያት የተመሰከረ መሆኑን ማወቅ ያስፈለጋል፡፡

#የክርስቶስ_ዕርገት_በትንቢተ_ነቢያት
፠ ‹‹ሰማዮችን ዝቅ ዝቅ አደረገ ወረደም ጨለማ /ዲያብሎስ/ ከእግሩ በታች ነበር በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ በነፍሳትም ክንፍ በረረ፡፡›› መዝ.17፥9
፠ ‹‹አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምጽ ዐረገ መዝ.46፥5
ወደላይ ዐረግህ፥ ምርኮን ማረክህ ፥ ስጦታንም ለሰዎች ሰጠህ›› መዝ.67፥18፡፡
፠ ‹‹ዘምሩ ለእግዚአብሔር ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘመንገለ ጽባሕ፤ በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ›› መዝ.67፥33፡፡
#የክርስቶስ_ዕርገት_በትምህርተ_ሐዋርያት
፠ ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተነጋገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ፡፡ ማር.16፥19
፠ ‹‹እስከ ቢታንያ አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ፡፡››�ሉቃ.24፥50

፠ ‹‹ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ ደመናም ከዐይናቸው ሰውራ ተቀበለችው፤ እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኩር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ እነሆ ነጫጭ ልብስ ለብሰው ሁለት ሰዎች /መላእክት/ በአጠገባቸው ቆሙ ደግሞም ‹‹የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት ዳግመኛ ይመጣል፡፡›› አሏቸው››� ሐዋ.1፥9-12
በማለት ሐዋርያት የክርስቶስን ዕርገት ከመላእክት ጋር ሆነው እንደተመለከቱ ደስታውን እንደተካፈሉ ቅዱስ ሉቃስ ጽፎልናል፡፡ በትንሣኤው ነጭ ልብስ ለብሰው የታዩ መላእክት የደስታ ዘመን ነው ሲሉ በዕርገቱም ነጭ ልብስ ለብሰው የዕርገቱን የምሥራች ለሐዋርያት አብስረዋል፡፡

፠በዓለ ዕርገት መቼ ነው?
ጥንተ ዕርገቱ ግንቦት ስምንት ሐሙስ ቀን በ34 ዓ.ም በዘመነ ማርቆስ ነው፡፡
፠የዕረገት በዓል አከባበር እስከ አራተኛው መቶ ዓመት ድረስ እንደ ዛሬው ሐሙስን ሳይጠብቅ በጥንተ ዕርገቱ ግንቦት ስምንት ቀን ብቻ ይከበር ነበር፡፡
በአራተኛው ምዕተ ዓመት ወዲህ ግን ትንሣኤ በዋለ በአርባኛው ቀን ብቻ እንዲከበር ቅዱስ ዲሜጥሮስ በባሕረ ሐሳብ ቀመሩ ስሌት መሠረት ይከናወን ዘንድ በቀኖና ቤተክርስቲያን ተወስኖ በሥራ ላይ ውሎ ይገኛል፡፡
@muzemur
@muzemur
@muzemur

✞✞✞✞✞✞
✞✞✞✞✞✞

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
✞✞✞ @muzemur ✞✞✞

✞✞✞✞✞✞
✞✞✞✞✞✞
@Muzemur
@muzemur
@muzemur
100 viewsTheotokos, edited  02:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ