Get Mystery Box with random crypto!

☞ጌታ ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የሰጠው ቃልኪዳን፡፡ ☞ሰው ሁሉ ወደ ሥጋዊ ተግባርም ሆነ ወደ | ✞ የማርያም ✞ ፳፩ እና ✞ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ልጆች ፲፫ ✞

☞ጌታ ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የሰጠው ቃልኪዳን፡፡
☞ሰው ሁሉ ወደ ሥጋዊ ተግባርም ሆነ ወደ መንፈሳዊ ተግባርም ቢሆን ሲሄድ
ይህ የመጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ነው ብሎ ቅጽሩን፤ ገራገሩን
ቢሳለም የተሳለመውን ሰው ቢኖር እኔ መንበረ መንግሥቴን አሳልመዋለሁ፡፡
☞የገድልህንም መጽሐፍ የተሳለመ ቢኖር እኔ መንበረ መንግሥቴን
አሳልመዋለሁ፡፡
☞የገድልህ የተአምርህ መጽሐፍ የተነበበትን ውኃ እኔ እንደተጠመቅሁበት እንደ
ማዮርዳኖስ አደርገዋለሁ፡፡ የገድልህ መጽሐፍ በተነበበት ውኃ የተጠመቀበት
ሰው ቢኖር የሰማንያ ዓመት ኃጢአቱን አስተሠርይለታሁ፡፡
☞ወንድን የአርባ ቀን ሴቷን የሰማንያ ቀን ሕፃን አደርጋቸዋለሁ፤እኔ
በተጠመቅሁበት ማየ ዮርዳኖስ እንደተጠመቀ ሆኖለት ከኃጢአቱ ይነጻል፡፡
☞ሰውም ሆነ እንስሳ ቢታመም በጹኑ እምነት ይደረግልኛ ብሎ አምኖ ያለ
ጥርጥር ውኃ አቅርቦ የገድልህን መጽሐፍ በላዩ ላይ አንብቦ የተነበበትን ውኃ
ቢታጠብበት ወይንም ቢጠጣ ያለ ጥፋት ፈጥኖ ከደዌው ይፈወሳል፡፡
☞የገድልህን መጽሐፍ የተነበበትን ማየ ጸሎት በቤቱ ውስጥ ቢረጭ ከዚያ ቤት
በረከቴን እመላበታለሁ፤ ተድላን፤ ደስታን፤ ጥጋብን በዚያ ቤት አሳድራለሁ፤ እሰከ
ዘላለሙ ድረስ በቤቱ ውስጥ የእህል መታጣትና ርሃብ፤ የውኃ ጥማት፤ተላላፊ
በሽታ አይገባበትም፤ፈጽሜም አላመጣበትም፡፡
☞ሥጋዬን ደሜን መቀበል ያልተቻለሁ ሰው ቢኖር ለመታሰቢያህ ዝክር
ከተደረገው ፍርፋሪ ይቅመስ፤ ሥጋዬን ደሜን እንደተቀበለ እኔ አደርግለታለሁ፡፡
☞ፍርፋሪ ባያገኝ እንጀራውና ዳቦውን የተበላበትን ገበታ፤ ጠላው የተጠጣበትን
ጽዋ በምላሱ ይላስ፤ እኔ ኢየሱስ ቃል የሚያብለው ሥጋዬን ደሜን እንደተቀበለ
አደርገለታለሀ፤ ሰለ እምነቱ ሥጋዬን ደሜን ለመቀበል የሚያበቃውና
እውነተኛውን ምግባር የጽድቅ ሥራ እንዲሠራ አደርገዋለሁ ቡሎጌታ
ለመጥምቀ መለኮት ቃል ኪዳን ስጥቷል፡፡
☞(ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ)
☞እኛም የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የቃልኪዳኑ ተከፋይ ያድርገን
በጸሎቱ ይማረን፡፡ 
@muzemur
@muzemur

“አንተ ግን አቤቱ፥ መጠጊያዬ ነህ፥ ክብሬንና ራሴንም ከፍ ከፍ የምታደርገው አንተ ነህ።” መዝ ፫፥፫
join join join

  @muzemur
  @muzemur