Get Mystery Box with random crypto!

Bilal Media & Communication

የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication B
የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication
የሰርጥ አድራሻ: @linkbi7
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 21

2022-07-27 22:27:27 ፍፃሜው ስክነትና መርጋት እንዲሁም ማረፍ መሆኑን ብናውቅም ባለንበት ውጥረት ሳቢያ ከማዘን የሚያግደን አንድም ውል የለም።
በቃ ሰዋዊ ባህሪ ያጠቃናል..ነገ ባለው ድል የአሁን ሐዘናችንን ከመርታት ይልቅ ማዘንን እንመርጣለን..ያለንበት ሁሉ ጊዜያዊ መሆኑን ለራሳችን ከማሳመን ይልቅ ጭንቀት እንገዛለን..ካለንበት ተጨባጭ ውስጥ ወጥተን ሌላ ያልተኖረ የብስራት መኖር ወደኛ እንደሚመጣ ለልባችን ከማስረዳት ይልቅ መከፋትን እንዋጃለን።
በርግጥ ይሁን እንዘን..እንከፋ..ጭንቀት ከላይ እስከታች ይቆጣጠረን። ነገር ግን ነገ ለሚጮረው ውብ ቀን ስንል ሐዘኑን መከፋቱን ና መጨነቁን አናብዛ፣ልባችንን በብዙ lose ማድረጉን እንቀንስ።
ከዚህ ካለንበት ስሜት መላቀቅ ያቃተን እንደሆንም ሁሉን ለአላሁ እናስጠጋ፣ ያኔ ታዲያ ዛሬም ነገም ያማረ ይሆናል።

/አብድልቃድር ኑር/
58 viewsGlamor, 19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 19:36:18 ...በፊት ላይ እኔጋ ያለሽን ቦታ አጣሽብኝ እንዴ? ወይስ ስሜትን መደበቅ በደንብ ተካንኩ? ...ብቻ ግን አለመኖርሽ ያጎለኛል ይሄን ግን የመንገር አቅሙ እንኳን የለኝም


( glamor)
63 viewsGlamor, 16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 15:09:28 ከሰዎች ውስጥ ÷ ከመጮህ በቀር ማድመጥ የማይችሉ ፣ ከመናገር በቀር ማናገር የማይችሉ ፣ ከፌዝ በቀር ቁም ነገር የማያውቁ . . . ሰዎች አሉ።
(አብዱልሀኪም ሰፋ)
76 viewsGlamor, 12:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 09:48:36 ሙስሊም ያልሆኑ ምሁራን ስለ ነብዩ ሙሀመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)
ሞሀንዳስ ካራምቻንድ ጋንዲ
(ህንድ ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ነፃ ያወጣ የሰላማዊ ትግል መሪ)

"...በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህዝቦችን ልብ በጭብጡ ውስጥ ስላስገባው ሰው ምርጥ የህይወት ቅፅበቶች ለማወቅ ፈለግኩ።...(አንብቤ ስጨርስ) በዚያ ወቅት በነበረው የህይወት ማእቀፍ ውስጥ ለእስልምና ቦታ ያስገኘለት የሰይፍ ሀይል እንዳልሆነ ከምንም በላይ አመንኩ። ይልቁንም ቦታ ያስገኘለት የነብዩ (ሙሀመድ) ቅልል ያለ እና በመተናነስ የተሞላ ህይወት ፣እንከን የለሽ ቃል ኪዳን አክባሪነት ፣ለጓዶቹ ያላቸው ፍፁም መስጠት (አጋርነት )፣የተስተዋለበት ሀያል ወኔ እና ፍርሀት አልባነት ፣እንዲሁም በአምልልክ እና በተልዕኮው ላይ የነበረው ጥልቅ መተማመን ነበር ።(ትግሉን) ያስኬደለት እና በየመንገዱ ያገኘውን እንቅፋት ያስገበረለት ሰይፍ ሳይሆን እኒህ ባህሪዎቹ ነበሩ።(የነብዩ/ሙሀመድ/ን የህይወት ታሪክ መፅሀፍ) ሁለተኛ ጥራዝ አንብቤ ጨርሼ ስዘጋው ስለታላቅ ህይወቱ ተጨማሪ የማነበው ነገር ባለመኖሩ እያዘንኩ ነበር።

ያንግ ኢንዲያ-1924
69 viewsGlamor, 06:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 20:08:51 "የተዘጉ በሮች እና ያሳወሩን ብዥታዎች ትናንትና ነበር ።የ22 ወር ልጄ የራሱን ነፃነት ለማወጅ ሲንቀሳቀስ በአይኔ አየሁት ። ከመኪና ወንበሩ መቀመጫ መሀል ከወጣ ቡሀላ እንደ ትልቅ ልጅ በሩን ለመዝጋት ሞከረ ። እኔ የሚሰራውን ሁሉ በቅርበት እከታተለው ነበር ።እኔ በሩን እንዲዘጋ ብተወው ኖሮ ትንሹ ጭንቅላቱ በግጭት አይተርፍም ነበር ። አነሳሁትና በሩን ራሴ ዘጋሁት ።ድርጊቴ አናደደውና አለቀሰ ።እሱ ማድረግ የፈለገውን ነገር ስለከለከልኩት ነበር የተበሳጨው ።

ክስተቱን እያየሁኝ የሆነ ሀሳብ ጭንቅላቴ ውስጥ መጣ ። በተለይ ከአላህ አንፃር የዚህ አይነቱ ነገር በህይወታችን ውስጥ ሁሌም ያጋጥማል ። እኛ አንድን ነገር ስንፈልግ አላህ ግን ሳይፈልግ ሲቀር እንዴት እንደሚከለክለን አስተዋልኩበት ። በተለይ ወጣት ሆነን ሳለ የዚህ አይነቱ ነገር በተደጋጋሚ ያጋጥመናል ። አንዱን ነገር በእጅጉ ፈልገን እኛ በፈለግነው መልኩ ካልተሳካልን ተስፋ እንቆርጣለን ፣እንናደዳለን ፣ክፉኛእንበሳጫለን ። ግና ኃላ ላይ ቆይቶም ቢሆን አለመሳካቱ ለበጎ እንደሆነ ይገለጥልናል ። እኔ ልጄ እንዳይጎዳ ያደረኩት ነገር ቢኖር በሩን እንዳይታገለው እሱን መውሰድ ብቻ ነበር ። እሱ ግን ለእሱ ጥቅም እንደሆነ አልገባውም ። በመነጫነጩ መሐል ሆኖ ከትልቅ አደጋ እንዳዳንኩት አያውቅም ነበር ። ልጄ ምንም ሳያቅ በየዋህነቱ እንዳለቀሰው ሁሉ እኛም እንዲሁ ካለቀስንላቸው ነገሮች አላህ እኛን ያዳነበት ሁኔታ ብዙ ነው ።

የአውሮፕላን የበረራ ሰዓት ሲያመልጠን፣ስራ ስናጣ ፣ካሰብነው ሰው ጋር በትዳር የመጣመር ጉጉታችን ሲከሽፍ ...ሌላም ሌላም ገጠመኝ ሲገጥመን "ይሁን ለበጎ ነው "ብለን ያሰብንበትና ያሳለፍንበት አጋጣሚ ይኖር ይሆን!

አላህ በቁርአኑ እንዲህ ይለናል ፦

كُتِبَ عَلَيْكُمُ ٱلْقِتَالُ وَهُوَ كُرْهٌۭ لَّكُمْ ۖ وَعَسَىٰٓ أَن تَكْرَهُوا۟ شَيْـًۭٔا وَهُوَ خَيْرٌۭ لَّكُمْ ۖ وَعَسَىٰٓ أَن تُحِبُّوا۟ شَيْـًۭٔا وَهُوَ شَرٌّۭ لَّكُمْ ۗ وَٱللَّهُ يَعْلَمُ وَأَنتُمْ لَا تَعْلَمُونَ
መጋደል እርሱ ለእናንተ የተጠላ ሲሆን በእናንተ ላይ ተጻፈ፡፡ አንዳች ነገርን እርሱ ለናንተ የበለጠ ሲሆን የምትጠሉት መኾናችሁ ተረጋገጠ፡፡ አንዳችንም ነገር እርሱ ለናንተ መጥፎ ሲሆን የምትወዱት መሆናችሁ ተረጋገጠ፡፡ አላህም (የሚሻላችሁን) ያውቃል ግን እናንተ አታውቁም፡፡"


ምንጭ
(ልብህን አስመልስ በYasmin Mujahid )
82 viewsGlamor, edited  17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 13:46:45 *አንዳንዴ እየወደድክ የምትርቀው አንዳንዴ ደግሞ እየጠላህ የምትቀርበው ብዙ ጊዜ ግን ዝም ብለህ አብረህ የምትኖረው ሰው አለ ...*አንዳንዴ ፍቅሩን ሳይገልፅልህ የሚወድህ አንዳንዴ ደግሞ እወድሀለው እያለ የሚጠላህ ብዙ ጊዜ ግን ስሜቱን የማታውቀው ሰው አለ *አንዳንዴ እየራበህ የማትበላው አንዳንዴ ጠግበህም የምትመገበው ብዙ ጊዜ ግን ዝም ብለህ የምትውጠው ነገር አለ *አንዳንዴ ሳትኖር የምትሞትበት አንዳንዴ ደግሞ ሞተህም የምትኖርበት ብዙ ጊዜ ግን ዝም ብለህ የምትጓዝበት ህይወት አለ ...***አንዳንዴ አስደስቶህ የምታለቅስለት አንዳንዴ ደግሞ አሳዝኖህ የምታለቅስበት ብዙ ጊዜ ግን ዝም ብለህ የምታነባበት ጉዳይ አለ ...
97 viewsGlamor, 10:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 12:41:51
90 viewsGlamor, 09:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 20:33:53 የአንዳንድ ሰዎች በሓሪ ፡ ልክ አምነው ሲረግጡት ጭቃን አፈናጥሮ ልብሳችንን እንደሚለውስ የመንገድ ዳር ድንጋይ ነው!!! ስናምነው የሚከዳን!

አንዴ ልብሳችን በጭቃው ከተበላሸ ቀጣይ የምንረግጠው ኹሉ እንደ መጀመሪያው ስለሚመስለን እምነታችን ጎዶሎ ይሆናል!!!

ክቡሩን የሰው ልጅ ከግዑዙ አካል ጋር ማመሰላችን እንዳልሆነ ልብ ይባልልን!
93 viewsGlamor, 17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 05:58:16 ያንተን ድካም ፣ ልፋትህን ፣ ጥረትህን ስለማያዩ ሚታይ ነገር ብቻ በመፈለግ ያናንቁሃል፤ያጣጥሉሃል!
101 viewsGlamor, 02:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 22:37:44 ጥቂት መልእክት አለችኝ ለክረምት

ክረምትን ሸሪዐን በጠበቀ ዲናዊ ትምህርት በመማር እናሳልፈው

ራስህን ከ "ጠብቆ ወጊዎች" ጠብቅ እነዛ በጥላቻ የሠከረ ንግግር በአእምሯቸው ተሸክመው ምንም ሳትላቸው አፋቸው ሲከፈት ውስጣቸውን የሞላው የጥላቻ ጋጋታ የሚፈስባቸውና ቢድዐ ቢድአ አትበል እያሉ ሊያሸማቅቁህ የሚፈልጉ ናቸው።ደሞ አለማፈራቸው ወንድና ሴትን ቀላቅለው እያስተማሩ አንተን ሹብሀ ውስጥ ሊከቱህ የሚፈልጉ መሆናቸው።

ምን ማን ጋር መማር እንዳለብህ እደግመዋለው ማንጋር ምን መማር እንዳለብህ ተገንዘብ።አዛኝ መስሎ ኮርስ ምናምን ብሎ የስሜቱን ዐቂዳ ሊጭንብህ የሚፈልግን ሁሉ ልትከላከለው ይገባል።ታናሽ ወንድምህ እና እህትህ ምንድነው እየተማሩ ያሉት? ህፃናትን ጥላቻ ከሚሠብክ ስሜትን እንዲከተሉ የሚያደርግ እንዲሁም በሀፊዝ ስም የሚነግድ ከሆነ ሁሉ ራስህን ብሎም ቤተሠብህን አድን

አቋምህ በማዕረጎችና በተቀፂላ ስሞች የሚቀያየር አይሁን አቋምህ/እምነትህ እንደተራራ የፀና እንጂ ድንጋይ ላይ እንደበቀለ ዛፍ በንፋስ የሚወድቅ ወይም ስር የሌለው ገለባ መሆን የለበትም።

ሱለይማን ኢስማዒል
117 viewsibnu rebah, 19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ