Get Mystery Box with random crypto!

Bilal Media & Communication

የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication B
የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication
የሰርጥ አድራሻ: @linkbi7
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 17

2022-09-13 20:59:11 (ነሱሀ አወል)

አልፎ አልፎ...!

መልካም ፣ጌታቸውን ፈሪ ፣ ትሁት ፣ ገር ያልካቸው ሰወች ከመቅፅበት ምራቅህን የምትውጥበት ሰአት እንኳ ሳይሰጡህ የመልካምነት ካባቸው ይገፈፋል። ስለ እንባህ የተጨነቁ ሲመስልህ የዘረገፍከውን እንባ ከሀይቅ ያጣጉልሀል። ስለህመምህ ባብራራህበት ልክ ቆሞ የሚሄድ ታካሚ የነበርክን አንተ በዊልቸር ትሄድ ዘንድ በሽታህን ያሻሽሉልሀል...እንዴት? እንደእይታየ የሰው ልጅ አሉታዊ ባህሪ በላይህ እንዲነግስ የምታደርገው አንተው ራስህ ነህ ከማመን በተጨማሪ ድክመትህን ሁሉ ገፅህን በሙሉ አስነብበሀል።...እርግጥ ነው አባት ልብ ያላቸው እንዳሉ ሁሉ በጥፍጥናቸው ውስጥ መራርነት የሚያስቀምሱህ አይጠፉም። እናም እላለሁ..ከአምላክ በላይ አማካሪ አታድርግ።

...አልፎ አልፎም ቢሆን ' ሰው ' መሆናችንን ባንዘነጋ መልካም ይመስለኛል።
85 viewsGlamor, 17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-13 17:25:11 “መውሊድን የፈለገ ያክብር የፈለገ ይተው። በዚህ መጯጯህ አያስፈልግም” የሚሉ ሰዎች አሉ። ከነዚህ ውስጥ ከፊሎቹ በተውሒድና በሺርክ፣ በሱናና በቢድዐ መካከል ያለውን ርቀት የማያውቁ፣ መስመሩ የተደባለቀባቸው ምስኪን ወገኖቻችን ናቸው። ዝም ሊያሰኙን ለሚሞክሩ ሁሉ በግልፅ የምንነግራቸው “ዝም አንልም” ነው። “በዚህ ልንጣላ አይገባም” ይላሉ። ሺርክና ቢድዐን እያየን ከተላለፍን ከዚህ በኋላ ያለ ህብረት ምን ዋጋ ሊኖረው? አንዳንዶቹ አውቆ አጥፊ አጭበርባሪዎች ናቸው። ተውሒድን በሚንዱ ከባባድ ጉዳዮች ተለያይተን ሳለ “በትንንሽ ነገሮች መለያየት የለብንም” እያሉ ያምታታሉ። የተውሒድና የሺርክ ጉዳይ፣ የሱናና የቢድዐ ጉዳይ ነው ትንንሹ? አዑዙ ቢላህ! ከፊሎቹ “አገር በጭንቅ በተወጠረችበት በዚህ ሰአት ይሄ ነው ወይ የሚያሳሰባችሁ?” ይላሉ። አገር በተወጠረችበት ለአዝማሪ ስታሸረግዱ ነበርኮ ወገን!
ወንድም እህቶች! በመውሊድ ላይ የምታደርጉትን ዘመቻ አጥብቃችሁ ቀጥሉ። የማምታቻ ቡቱቶዎቻቸውን በድምፅም በፅሁፍም እየበጣጠሳችሁ ጣሉ። በራሳችሁ ባትችሉ የሌሎችን ስራዎች ሼር፣ ኮፒ ፔስት፣ ላይክ እያደረጋችሁ አሰራጩ። ሞራላችሁ አይቀዝቅዝ። የሐቅ ሰዎች ከባጢል ሰዎች ያነሰ ሞራልና መነቃቃት ሊኖራቸው ፈፅሞ አይገባም። የዛዛታና የቀልድ ስራዎች በዩቲዩብና በፌስቡክ በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጩ እንዴት እኛ ሐቅ ለማሰራጨት እንሳነፋለን? የወገናችን ጉዳይ አያሳስበንም? የባጢል መንሰራፋት አያስጨንቀንም? የሺርክና የቢድዐ መብዛት ምቾት አይነሳንም? ታዲያ እንዴት በልጠንና ተሽለን መገኘት ያቅተናል? ስለዚህ የቻለ በየመስጂዱ፣ በየመንገዱ፣ በየገጠሩ፣ በየከተማው ይዋደቅ። ሌላው በፌስቡክ፣ በቴሌግራም፣ በዋትሳፕ፣ በትዊተር፣ በዩቲዩብ፣ በቲክቶክ ፣ በየመስኩ ይዝመት። ወንድሞቼ እህቶቼ ሆይ! አንድ ሰው ባይለወጥ እንኳ ልፋታችንን የሚመለከት ጌታ ይመነዳናልና አንቀዛቀዝ። ደግሞ ኢንሻአላህ የሚለወጡ እንደሚኖሩ ትልቅ ተስፋ አለን። ትላንት ሲሰድቡን ከነበሩት ውስጥ ስንቶቹ ተለውጠው አይተናል። ሐዲሡም በሆነ መልካም ስራ ላይ ያመላከተ ከሰራው ሰው ጋር ተመሳሳይ አጅር አለው ነው የሚለው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
79 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-13 13:27:04 * ኸሊፋ ሊሆን በማይገባው እድሜ ስልጣን ይዞ የመርዋን መጫወቻ የሆነ፣
* አገዛዙ ከኢስላም ሩህ የራቀ ነበር፣
* ከኡሥማን ይልቅ የኡሥማን ገዳዮች ለኢስላማዊ ሩሕ የቀረቡ ነበሩ።
* ኡሥማን ላይ በተነሳው ፊትና የአቡ ዘር እጅ አለበት ይላል። [አልዐዳለቱል ኢጅቲማዒያህ፡ 160-186]
አስተውሉ! ነብዩ ﷺ የዑሥማንን ገዳዮች ሙና^ፊቆች እንደሆኑ ቀድመው ገልፀዋል። የኢኽዋኖቹ ቁጥብ ሰይድ ግን እነዚህን ሙና^ፊቆች ከኡሥማን በበለጠ ለኢስላማዊ ሩሕ የቀረቡ ነበሩ ይላል። ይስተዋል! ሰይድ ቁጥብ የነብዩን ሶሐቦች ደጋግሞ ባስቀያሚ ቃላት መወረፉ ከራፊዷ ሺዓዎች ጋር የሚያመሳስለው ባህሪው ነው፡፡ ለዚህም ነው የራፊዷው የኢራን መንግስት በስሙ ቴምብር ያሰራለት። በርግጥ ሰውየው ከሺ^ዐዎች ጋር ጠንካራ ግንኙነት ነበረው። በነገራችን ላይ ሰይድ ቁጥብ ከዚህ ተግባሩ ተመልሷል የሚሉ ሰዎች አሉ። ይሄ ግን ውሸት ነው።

7. ሰይድ ቁጥብ ኡማውን በጅምላ የሚያከ^ፍር ተክ^ፊሪ፣ ኻሪ^ጂ ነው፡፡ ምን እንደሚል አይታችሁ ፍረዱ።
* “እሄ የምንኖርበት ማህበረሰብ እራሱ ሙስሊም ማህበረሰብ አይደልም። ለዚያም ነው ኢስላማዊ ስርኣት ያልዘረጋው፡፡” “በመጨረሻም ከነዚህ የጃሂ^ሊያ ስብስብ ውሰጥ የሚካተቱት እነዚህ ሙስሊም እንደሆኑ የሚሞግቱት ህዝቦች ናቸው።” [ፊ ዚላሊል ቁርኣን፡ 3/1816፣ 4/2009-2010]
* “ጉዳዩ የማመንና የመካ^ድ ጉዳይ ነው። ሰዎች እንደሚሞግቱት ሙስሊሞች አይደሉም። የሚኖሩት የጃሂ^ሊያ ህይወት ነው። ደዕዋችን የተነሳው እነኚህን ጃሂ^ሊዮች ወደ ኢስላም ለመመለስ ነው፣ እንደ አዲስ ሙስሊም ለማድረግ።” [መዓሊሙን ፊጦሪቅ፡ 173]
* “የሙስሊሙ ኡማ ህልውና ከብዙ ከፍለ-ዘመናት በፊት ተቋርጧል። እንደ አዲስ መመለስ ይኖርብናል።” [መዓሊሙን ፊጦሪቅ፡ 6]
* “ዛሬ ያለነው ኢስላም ሲነሳ ያጋጠመው ዓይነት ጃሂ^ሊያ ውስጥ ነው ወይም ከዚያ የከፋ የሆነ!” [መዓሊሙን ፊጦሪቅ፡ 21]
* በአሁኑ ጊዜ ያሉ ሙስሊሞችን እርድ መብላት ይቻላል ወይ” ተብሎ ሲጠየቅ “እንደ አህለል ኪታብ (አይሁድና ክርስቲያን) እርድ ቆጥራችሁ ብሉ” ብሎ ነው የመለሰው። [አታሪኹ ሲሪይ ሊጀማዐቲል ኢኽዋኒል ሙስሊሚን፡ 80]
ይሄ ሁሉ ጉድ ያለበትን ሰው እያንቆለጳጰሱ ነው ኢኽዋኖች ሌሎችን “ተክ^ፊር” “ፅንፈኛ” እያሉ የሚወነጅሉት። “የሌባ አይነ-ደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ!”

8. ሰይድ ቁጥብ ጁሙዐ አይሰግድም ነበር!! ዐሊይ ዐሽማዊ (የሰይድ ቁጥብ ቅርብ ሰው ነው) በአንድ ወቅት ከሰይድ ቁጥብ ጋር ያጋጠመውን እንዲህ ሲል ይገልፃል፡-
“የጁሙዐ ወቅት ሲደርስ “ተወንማ እንነሳና እንስገድ” አልኩት፡፡ አስደንጋጭ ነበር! ለመጀመሪያ ጊዜ ሰይድ ቁጥብ ጁሙዐ እንደማይሰግድ አወቅኩኝ፡፡ “ኢስላማዊ ኺላፋ ከሌለ ጁሙዐ የለም፡፡ ያለ ኺላፋ ጁሙዐ የለም!” አለ፡፡ [አተንዚሙ ሲሪይ፡ 112]

9. ሰይድ ቁጥብ ወደ ሶሻሊዝምና ኮሙኒዝም የክህ^ደት ርእዮተ ዓለም የሚጣራ ነበር! “መንግስት ንብረቶችንና ሀብቶችን በሙሉ በመንጠቅ እንደገና እንደ አዲስ ሊያከፋፍል የግድ ይለዋል። እነዚህ ንብረቶች ኢስላም እውቅና በሚሰጠው መልኩ የተገኙ፣ በሚያፀድቃቸው መንገዶች የበለፀጉ ቢሆኑም እንኳን። ምክንያቱም ከማህበረሰብ ላይ ጉዳትን ማስወገድ እና በዚህ ህብረተሰብ ላይ የሚጠበቁ ጉዳቶችን መከላከል ከግለሰብ መብቶች ይልቅ ተቀዳሚ ናቸውና።” [መዕረከቱል ኢስላም ወረእሰማሊያህ፡ 44]

10. ሰይድ ቁጥብ በርካታ የቁርኣን አያዎችን ለክብራቸው በማይገባ መልኩ በሙዚቃዊ ቃና ደጋግሞ ይገልፃቸዋል። ለዚህም በሙዚቃ ባለሙያ በሙዚቀኛ እንደታገዘ ያለምንም ሀፍረት ይገልፃል። [አተስዊሩል ፈኒይ፡ 89]

11. ሰይድ ቁጥብ በዐቂዳ ጉዳይ ቁርኣን ብቻ እንጂ ሶሒሕ እንኳን ቢሆኑ ሙተዋቲር ያልሆኑ ሐዲሦችን አይቀበልም። [ፊዚላሊል ቁርኣን፡ 6/2008] ልብ በሉ! ይሄ የአፈን^ጋጩ ሙዕ^ተዚላ ቡድን አቋም ነው።

12. ሰይድ ቁጥብ ደግሞ ደጋግሞ ቁርኣንን “ሲሕር” /ድግምት/ እያለ ይገልፃል! [አተስዊሩል ፈኒይ፡ 11፣ 17፣ 25] አዑዙ ቢላህ! ድግምት ነው ሲል ግን ማድነቁ ነው በሱ ቤት። አያችሁ ይህን የቋንቋ መርቀቅ፡፡ ድንቄም!! ያላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል።

13. ሰይድ ቁጥብ ነብያትን ሳይቀር ለክብራቸው በማይመጥን መልኩ በነገር ይወጋል። [አተስዊሩል ፈኒይ፡ 200፣ ...]
ኢኽዋኖች ሆይ! ይህ ነው ሰይዳችሁ! ይሄ ነው ቁጥባችሁ!

(ኢንሻአላህ ክፍል 4 ይቀጥላል)
(ኢብኑ ሙነወር፣ ህዳር 13/2007)
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
79 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 10:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-13 13:26:09 የኢኽዋን ምሽጎችን ማንኮታኮት
(ተከታታይ፣ ክፍል-3)
ሰይድ ቁጥብን ለማያውቀው
~
1. ሰይድ ቁጥብ የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን አይቀበልም። ኢስቲዋእን ልክ አሕባሾች እንደሚያደርጉት በጀህ^ሚያ፣ በሙዕ^ተዚላና በአሻ^ዒራ ተፍሲር ነው የፈሰረው። [ፊዚላሊል ቁርኣን፡ 4/2328፣ 5/2807፣ 6/3480] በዚህ ጉዳይ የአሕ^ባሽን ጥመቶች ለማጋለጥ የምትታትሩ ወንድሞችና እህቶች ሆይ! የጥመት ቡላና ዳለቻ የለውም! የሰይድ ቁጥብን ጥመትም እንዲሁ አትርሱ።

2. ሰይድ ቁጥብ አደገኛውን የ“ወሕደተል ውጁድ” በተጨማሪም የጀህ^ሚያዎችን፣ የቀደ^ሪያዎችንና የጀብ^ሪያዎችን ዐቂዳ አስፍሯል። [ፊዚላሊል ቁርኣን፡ 4/2249፣ 5/2719፣ 6/4002]

3. ሰይድ ቁጥብ {የኡሉሂያ ጉዳይ የውዝግብ አጀንዳ አልነበረም። ይልቁንም የሩቡቢያ ጉዳይ ነው የውዝግብ አጀንዳ የነበረው። መለኮታዊ ተልእኮዎች (ሪሳላዎች) ሲጋፈጡት የነበረውም ይህን ነው። የመጨረሻው ተልእኮም (ሪሳላም) ይጋፈጠው የነበረው ይህ ነው} ይላል። [ፊዚላሊል ቁርኣን፡ 4/1846]
እውነታው ግን በነቢያትና በህዝቦቻቸው መካከል የነበረው ፍጭት ዋና መንስኤው ተውሒደል ኡሉሂያን አለመቀበላቸው ነበር። እንጂ ተውሒደ ሩቡቢያህ አልነበረም። ለምሳሌ የመካ ሙሽሪኮች የአላህን ፈጣሪነትና ጌትነት ያውቁ ነበር። ችግራቸው እሱን በብቸኝነት ለማምለክ ፈቃደኞች አለመሆናቸው ነው።

4. ሰይድ ቁጥብ ላኢላሀኢለላህ ማለት “በመፍጠርና በመምረጥ ተጋሪ የለውም ማለት ነው” ይላል። [ፊዚላሊል ቁርኣን፡ 5/2707] ይሄም ግልፅ ስህተት ነው። ላኢላሀኢለላህ ማለት ከአላህ በስተቀር በሐቅ አምልኮት የሚገባው የለም ማለት ነው። የአላህን ፈጣሪነትማ ብዙሀኑ የመካ አጋሪዎችስ መቼ ካዱ? ይሄውና የቁርኣን ዘላለማዊ ምስክርነት:-
{ قُلۡ مَن یَرۡزُقُكُم مِّنَ ٱلسَّمَاۤءِ وَٱلۡأَرۡضِ أَمَّن یَمۡلِكُ ٱلسَّمۡعَ وَٱلۡأَبۡصَـٰرَ وَمَن یُخۡرِجُ ٱلۡحَیَّ مِنَ ٱلۡمَیِّتِ وَیُخۡرِجُ ٱلۡمَیِّتَ مِنَ ٱلۡحَیِّ وَمَن یُدَبِّرُ ٱلۡأَمۡرَۚ فَسَیَقُولُونَ ٱللَّهُۚ فَقُلۡ أَفَلَا تَتَّقُونَ}
{“ከሰማይና ከምድር ሲሳይን የሚሰጣችሁ ማነው? መስሚያዎችንና ማያዎችንስ የፈጠረስ ማን ነው? ከሙትም ሕያውን የሚያወጣ ከህያውም ሙትን የሚያወጣስ ማን ነው? ነገሩን ሁሉ የሚያስተናብርስ ማን ነው?” በላቸው። በእርግጥም “አላህ ነው” ይሉሃል። እናም “ታዲያ (እንደሚገባው) አትፈሩትም?” በላቸው።} [ዩኑስ፡ 31]

5. ሰይድ ቁጥብ ኢማንን ወጥና የማይከፋፈል ነው ይላል። [ፊዚላሊል ቁርኣን፡ 2/798] ይሄ አደገኛ አንድምታ ያለው የሙር^ጂአ እና የኸ^ዋሪጅ አቋም ነው።

6. ሰይድ ቁጥብ እንደ ራፊ^ዷ/ ሺ^0 የነብዩን ﷺ ሶሐቦች ያንቋሽሻል።
[ሀ]:- አቡ ሱፊያንን ረዲየላሁ ዐንሁ "የአቡ ሱፊያንን እስልምና የከንፈርና የምላስ እስልምና እንጂ የልብ ኢማንና እውነቱን የማግኘት አይደለም። ኢስላም ወደዚህ ሰውየ ልብ አልሰረፀም፣ ከሰለመ በኋላም የሙስሊሞችን ሽንፈት ሲመኝ የነበረ ነው!!” በማለት በኒፋ^ቅ ይወነጅላል። ይስተዋል! ነብዩ ﷺ ግን የአቡ ሱፊያንን እስልምና ተቀብለዋል። አቡ ሱፊያን ሙስሊም ሆነው ጂሃድ ሲዋጉ አንድ አይናቸውን እንዳጡ እና ነብዩም ﷺ “ከፈለግክ ዱዐ ላድርግልህና አይን ይመለስልሃል። ከፈለግክ ደግሞ (ታገስና) ጀነት አለህ” ሲሏቸው “ጀነት ይሻለኛል” እንዳሉ ኢብኑ ሐጀር ጠቅሰዋል። [አልኢሷባህ፡ 4066]
[ለ]:- ሰይድ ቁጥብ ሙዓዊያንና ዐምር ብኑል ዓስን በውሸት፣ በማጭበርበር፣ በማታለል፣ በንፍ^ቅና፣ በሙሰኝነት … ይወነጅላቸዋል። [ኩቱቡን ወሸኽሲያት፡ 242] ሙዓዊያን ረዲየላሁ ዐንሁ ደግሞ ደጋግሞ በሚያስቀይሙ ቃላት ወርፏቸዋል። አሁን በነዚህ አስቀያሚ ቃላት የተወነጀለው ሰይድ ቁጥብ ቢሆን ኖሮ ኢኽዋኖች ምን ይሉ ነበር? ለመሆኑ ከሶሐቦቹና ከሰይድ ቁጥብ ማነው የሚበልጠው? ዛሬም ተከታዮቹ ሰይድ ቁጥብ ተሳስቷል ከማለት ይልቅ ሶሐቦችን መወንጀል ነው የሚቀናቸው። ለሶሐቦች የማይሰጡትን ምክንያትም ለሰይድ ቁጥብ ይደረድራሉ።
ኢብኑ ሙባረክ፡ ከሙዓዊያና ከዑመር ብኑ ዐብዲልዐዚዝ የትኛው እንደሚበልጥ ሲጠየቁ “ወላሂ ሙዓዊያ ከነብዩ ጋር ሆኖ ባፍንጫው የገባው አቧራ ከዑመር ሺህ ጊዜ ይበልጣል” ብለው ነው የመለሱት። ልብ በል! ከሙዓዊያና ከሰይድ ቁጥብ ማን ይበልጣል አይደለም የተጠየቁት። ሌላም ጊዜ “ሙዓዊያ እኛ ዘንድ ፈተና ነው። እሱን በመጥፎ ሲመለከት ያየነውን በሶሐቦች ጉዳይ አናምነውም” ብለዋል። ኢማሙ አሕመድ “ከሙዓዊያና ከዑመር ብኑ ዐብዲልዐዚዝ ማን ይበልጣል?” ተብለው ሲጠየቁ፣ “ሙዓዊያ ነው የሚበልጠው። የነብዩን ሶሐቦች ከማንም ጋር አናወዳድርም” ብለዋል። አንድ ሰው ኢማሙ አሕመድን “አንድ ሙዓውያን የሚያንቋሽሽ አጎት አለኝ” ቢላቸው “ከሱ ጋር አብረህ እንዳትበላ!” ብለውታል። ብዙ ኢኽዋኖች ግን ብዙ ፀያፍ ጥፋቶች ያሉበትን ሰይድ ቁጥብን ሸሂድ እያሉ እያወደሱ እነ ሙዓዊያን ለማብጠልጠል ግን ሁለት ጊዜ እንኳን ማሰብ አይፈልጉም።
[ሐ]:- ሰይድ ቁጥብ ከዚህም ተሻግሮ በኑ ኡመያን በጅምላ በኒፋ^ቅ ይወነጅላል፡፡ “በኑ ኡመያ በጥቅሉ ኢማን ከልባቸው አልሰረፀም፡፡ ኢስላም ለነሱ እንደ ጥቅማቸው ሲያሻቸው የሚለብሱት ሲፈልጉ የሚያወልቁት ካፖርት ማለት ነው። ስነ ምግባር፣ ዲን፣ ልቦና የማይገታቸው ሰዎች ናቸው…” ይላል። [አልዐዳላህ ፡172]
ከግለሰብ ክብር በላይ ለእውነት የምትወግኑ ሁሉ ቆም ብላችሁ አስተውሉ! ሰይድ ቁጥብ በዚህ መልኩ የሚገልፀው እናንተን ቢሆን ምን ትሉ ነበር? በነዚህ አስቀያሚ ቃላት የሚገልፀው የነብዩን ﷺ ሶሐቦች ሲሆንስ? የነብዩን ሶሐቦች በማብጠልጠል የተለከፈው ሰይድ ቁጥብ የተከተለው የራፊ^ዷዎች/የሺ^0ዎች መንገድ ነው። ሶሐባ የሚሳደብን ሰው በተመለከተ ነብዩ ﷺ “የአላህ፣ የመላእክትና የሰዎች ሁሉ እርግማን በሱ ላይ ይሁን” ብለዋል። ኢማሙ ማሊክ፡- “የአላህ መልእክተኛን ﷺ ሶሐቦች የሚሳደብ ሰው በኢስላም ውስጥ ምንም ድርሻ የለውም” ብለዋል። ኢማሙ አሕመድ፡ “አንድ ሰው የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሶሐቦችን በክፉ ሲያነሳ ካየህ ሙስሊምነቱን ተጠራጠረው” ብለዋል። አቡ ዙርዐህ፡- “አንድ ሰው ከአላህ መልእክተኛ ﷺ ሶሐቦች የየትኛውንም ክብር ሲያጎድፍ ካየኸው እወቅ እሱ አፈንጋጭ ነው” ብለዋል።
[መ]:- ሰይድ ቁጥብ ከዚህም አልፎ በጀነት የተመሰከረላቸውን፣ ነብዩ ﷺ ሁለት ሴቶች ልጆቻቸውን የዳሩላቸውን፣ “ሶስተኛ ቢኖረኝ እድረው ነበር” ያሏቸውን፣ ሶስተኛውን ፍትሃዊ ኸሊፋ ዐሥማን ብኑ ዐፋንንም እንዲህ ሲል ይወነጅላል:-
* የኡሥማን ረዲየላሁ ዐንሁ የኺላፋ ዘመን በሶስቱ ኸሊፋዎች ዘመን ውስጥ የገባ ክፍተት እንጂ የእውነት የነገሰው እሱ ሳይሆን መርዋን ነው።
* ዑሥማን በስልጣኑ ተከልሎ የሙስሊሙን ገንዘብ ያላግባብ የተጠቀመ፣
* ለዘመዶቹ እያዳላ የነብዩን ወዳጆች ያራቀ፣
74 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 10:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 19:08:36 (ነሱሀ አወል)

ነገን ለማይሆንሽ ሰው ፊት አትስጪ፣ ውሎሽን አታጋሪ ፣ ኑሮሽን አታሳይ፣ ችግርሽን አታዋይ ፣ ስለስሜቶችሽ ግልፅ አትሁኚ ፣ ሙሉ በሙሉ ስለማንነትሽ አታብራሪ ፣ ድክመትሽን አታውጪ ፣ ዝምታሽን አትስበሪ፣ ልብሽን አትክፈቺ ፣ የጌታሽን ድንበር አትተላለፊ ፣ መቻልሽን በማይችልሽ ሰው አታሟጪ ፣ መልካምነትሽን ስለመልካም ነገር ባልተረዳ ሰው ፊት አታባክኚ ፣ ከማያዛልቅሽ መንገድ ገብተሽ መውጫው ህይወትሽን እንዳያመሰቃቅረው ስለራስሽ ስጊ...ለራስሽ ብለሽ ጥንቁቅ ሁኚ ፣ ስለአንቺ ካንቺ በላይ የሚያስብ የለም...ተጠንቀቂ!..እባክሽን!
81 viewsGlamor, 16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 15:51:29
ወንድም ሙባረክ ( ሀፊዘሁሏህ)
bi:lu

በ ጥበብ ቤት እና በኡሚ አዋርድ እንዲሁም ሌሎች መድረኮችም ላይ ፕሮግራም በመምራት የምናውቀው ወንድም ሙባረክ እጅግ ሚገርም የህይውት ታሪኩን በ ሚምበር ቴሌቭዥን አካፍሎናል::


ሀቂቃ እጅግ በጣም የቆራጥነት ተምሳሌት እንዲሁም የ አላማ ፅናት የታየበት ከ ትምህርት ቤት ቆይታው እስከ ማዕከላዊና ቂሊንጦ ማረሚያዎች እንዲሁም በ እስር ቤት ውስጥ ስለተከናወነው የ ኒካህ ፕሮግራሙ በስፋት የዳሰሰበት ድንቅ ዶክመንተሪ ነው!!!

ሰሞኑን እየተደጋገመ ስለሆነ እንድታዩት ጋብዛለሁ ባረከላሁ ፊኩም

ሌሎች ፅሁፎቼን መከታተል ለምትፈልጉ @linkbi7 ጆይን በሉ
842 viewsibnu rebah, 12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 15:23:31 አሁን ካነበብኩት
ኣንድ የሀብታም ልጅ ችስታ

ታገባና ከዛ ወደ ቤተሰቧ ቤት ዚያራ ትሄዳላች ከዛ አባቷ እንዴት ነው ኑሮ ሲላት አሪፍ ነው ግን ክክ
በልቼ አላቅም በቃ ሁሌ ስጋ ሰለቸኝ ትለዋለች ከዛ አባትየው
ባልዋ ጋር ይደውልና አንተ ምንድነው ልጄን በስጋ ምታሰለቻት ብሎ ቀወጠው ባል እሺ ይስተካከላል ይልና ለአባቷ ስልክ ዘጋ ከዛ ግራ ይገባውና ፈገግ አለ ለካ ሁሌ ሚያበላት ክክ ነው ሚስት ግን የባልዋን ሚስጥር በዚ መልኩ ጠበቀች ለት ያሁን ጊዜ አንድ አንድ ሴት ግን የባልዋን የአለጋ ላይ ሚስጥር እንኩዋን አትደብቅም
90 viewsGlamor, 12:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 07:38:59 ተጎድቶ ማዘንና ጎድቶ ማዘን እጅግ የተለያዩ ሀዘኖች ናቸው… ምን ነበር ባደረኩት ኖሮ ብሎ መፀፀት እና ምነው ባላደረኩት ብሎ መፀፀትም እጅግ የተለያዩ ፀፀቶች ናቸው … ስለ ትላንት ትዝታዎች ማሰብና ስለነገ ህልሞች ማሰብ እጅግ የተለያዩ ሀሳቦች ናቸው …
ረድኤት( ሎርዲና )

94 viewsGlamor, 04:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-11 21:33:59
((ድሮስ ከኢኽዋን ምን ይጠበቃል¡))
[ግም ለግም አብረህ አዝግም]¡

ሸይኽ ሙቅቢል ረሒመሁሏህ እንዲህ አሉ፦

"مفلسون من العلم ،ومفلسون من الدعوة "
#ኢኽዋነል_ሙስሊሞች ከእውቀትም ዳሃ ከዳዕዋም ዳሃ ናቸው!!

#ሸይኽ አልባኒም ረሒመሁሏህ እንዲህ ብለዋል፦
لا تجد في الإخوان المسليمن عالما
ከኢኽዋነል ሙስሊሚን አንድም አሊም (አዋቂ) አታገኝም!

https://t.me/+P0oqYHoAKo80NmNk
96 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 17:00:46 السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ውድ ወንድሞችና እህቶች እንደምናችሁ?

እኛን ጨምሮ በርካታ ወንድምና እህቶቻችሁ ብችግር ላይ ነው ያለነው።
እኛ በኦሮሚያ ክልል እየኖርን የምንገኝ ወገኖቻችሁ አሁን በዚህ ሰአት በታጠቀ ሃይል ንብረታችን እየተዘረፈና እየተሰቃዬን እንገናለን።
በኦሮሚያ ክልል ቡኖ በደሌ ዞን መኮ እና ጮራ ወረዳ፤በኢሉባቦር ዞን ዳሪሙ፣አልጌ ሳች፣ዶረኒ  በተባሉ ወረዳዎች ውስጥ እኚህ የታጠቁ ሃይሎች እየተዘዋወሩ የጥፋት ስራ ሲሰሩ የህግ አካሎች እኚህን አጥፊዎች እንኳን ሊከላከሉ ይቅርና ከቢሯቸው ውስጥ ይህን ሃይል አስግብተው ለህይወታችን ፈራን በማለት ህዝቡን ሜዳ ላይ ጥለውት ሄደዋል።
ንብረትን ከማጣትም በላይ በዚሁ ምክንያት ብዙዎች ህይወት እስከማጣትና ለስነ-ልቦና ጉዳት እየተጋለጡ ነው።

ከዚህ የከፋው ደግሞ አንዳንድ የአካባቢው ተዎላጆች "ውሻ በቀደደው ጅብ ይገባል" እንዲሉ ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው አብረው የኖሩትን ወንድሞቻቸውን ንብረት መዝረፋቸው ነው።

እኛ ይህ ችግር ከመከሰቱም በፊት ቢሆን ፍትህ እና ነፃነት አግኝተን አናውቅም።
ነገር ግን ያሁኑ በጣም አስቸጋሪ ነገር ነው።

ስለዚህ በሃገር ውስጥና በውጭ የምትኖሩ ወንድምና እህቶቻችን
እምንጠይቃችሁ ከዚህና መሰል ችግር አላህ እንዲገላግለን ዱዓ በማድረግ እንዲታግዙን ነው።

ያአላህ እኛን የናፈቀን ፍትህ ነው።
እኛን እኛን የናፈቀን ነፃነት ነው።

ያአላህ ፍትህን ስጠን!
ሰላምህን አንተ አምጣልን!
56 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 14:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ