Get Mystery Box with random crypto!

Bilal Media & Communication

የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication B
የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication
የሰርጥ አድራሻ: @linkbi7
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 20

2022-08-15 21:16:51 "አፈቅርሻለሁ" የሚለዉ ቃል
ምንም እንኳ አጭርና ቀላል ቢሆንም
ልብን ሰርስሮ የመግባት ጉልበቱ
ግን.... ሐያል ነዉ፡፡
ሐቢቢ ...! ፍቅርህን በገለፅክላት ቁጥር
በርሷ ዉስጥ ያለህ ቦታ ይበልጥ እየጨመረ
ይሄዳል፡፡ ስለዚህ... በዚህ ዉብ ቃል
ሚስትህን አስፈንድቃት!!
(አ ፈ ቅ ር ሻ ለ ሁ)
94 viewsGlamor, 18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-13 21:21:40
ተወዳጁ #ቲክቶከር ወንድም ኦሳም ስለ ዳሩል አርቀም የሰራው ቲክቶክ ቪዲዮ ነው


ሁላችንም እንየው #ሼር እናርግ
128 viewsGlamor, 18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 22:44:58 በዝምታ ላለመታነቅ
ውስጣችን ላይ ያለውን አውጥተን
ልንፅፍ እንችላለን ።

አንዳንዴም መፃፍን አብዝተን
በቃላቶቻችንም ልንታነቅ
እንችላለን ።

ተናገርንም ፃፍንም
ልባችን ውስጥ ግን የሚቀሩት
ብዙ ናቸው ።
M
69 viewsGlamor, 19:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 20:20:31 የሴት ልጅ ክብር

ሴትን ልጅ ማብቃት

[ክፍል 4]


የመጨረሻው ክፍል

በርግጥ ያንቺ ልዑል የሰው ልጅ ሊሆን ይችላል። ያ ግን የህይወት አጋርሽ እንጂ አዳኝሽ ሊሆን አይችልም። እሱም የዐይን ማረፊያሽ እንጂ የህይወትሽ ማቆያ ሳንባሽ አየር አይደለም። አየርሽ አምላክሽ ነው። መዳኛሽም እሱ ነው። ምሉዕነትሽ የሚረጋገጠውም ወደሱ ስትቀርቢ እንጂ እሱ ወደፈጠረው ነገር ስትቀርቢ አይደለም። ለልዑልም ሆነ ለፋሽን፣ ለውበትም ለስታይልም በመቅረብ አይደለም።


ስለሆነም እንድትነሺ እፈልጋለው እፈልጋለሁ። ተነስተሽ ለዓለም ሁሉ የማንም ባርያ እንዳልሆንሽ የፋሽን ፣የውበት ፣የወንድ ፣ ባርያ እንዳልሆንሽ አስረግጠሽ መንገር ይኖርብሻል። ባርነትሽ ለአላህና ለአላህ ብቻ ነው። ወደዚህ ዓለም የመጣሽው አምላክሽን ለማስደሰት እንጂ በገላሽ ወንዶችን ለማስደሰት እንዳልሆነ ተነስተሽ ለዓለም ሁሉ በራስ የመተማመን መንፈስ ፈገግ ብለሽ "እገዛ አያስፈልገኝም፤ አመሰግናለሁ።" ልትያቸው ይገባል።

ወደዚህ አለም የመጣሽው በአደባባይ ለቅራቅንቦዎቻቸው ማሻሻጫና ለማሳያ እንዳልሆነ ንገርያቸው። ሰውነትሽን ለአደባባይ ገበያ የሚቀርብ እንዳልሆነ አሰውቂያቸው።ከሰውነት ደረጃ ዉርደሽ የምትታዪ ቁስ እንዳልሆንሽ አለም ሁሉ ይወቅ። እግሮችሽም የጫማ መሸጫ መለኪያ አይደሉም። አንቺ ነፍስ ያለሽ ሰው ነሽ፣ አዕምሮ አለሽ፣ የአላህ ባርያና አገልጋይ ነሽ። ክብርሽ የሚለካው በነፍስሽ ውበት ነው፤ በልብሽ ጥራት እና በመልካም ስነምግባርሽ ነው። ስለሆነም የነሱ የውበት መለኪያ አምላኪ መሆን የለብሽም። የነርሱ ፋሽን ተከታይም አትሁኚ። መከተል እና እጅ መስጠት ያለብሽ ነገር ይሁን።


ስለሆነም ሴት ልጅ የት እና እንዴት መብቃት ይችላሉ ለሚለው ምልሽ ለመስጠት ወደ አላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ባልደረባ ንግግር መመለስ ያስፈልጋል። እውነተኛ ነፃነት እና መብቃት የሚረጋገጠው አንድን ሰው ከሌሎች ገዢዎች፣ ከሌሎች አለቃዎች እና መለኪያዎች ነፃ በማውጣት ነው።


እንደ ሙስሊም ሴትነታችን ከዝምተኛው ባርነት ነፃ ወጥተናል። ክብራችንን በውበትና በፋሽን የሚለካ ማህበረሰብ አንፈልግም።ለመከበር እንደ ወንድ መሆን አያስፈልገንም። እንዲያድነን እና እንዲያሟላልን ብለን የምንጠብቀው ልዑል አያስፈልገንም። ጥቅማችን፣ ክብራችን፣ ደህንነታችን እና ምሉዕነታችን በባሮች ላይ ጥገኛ አይደለም።

....በባሮች ጌታ ላይ እንጂ


....

°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
° በዳሩል አርቀም °
° የተዘጋጀ °
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
ምንጭ(ልብህን አስመልስ ከሚለው መፅሀፍ)
.
.
.
.
ተፈፀመ!!!
29 viewsGlamor, 17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 19:25:15 ትዕግስት ማጣት ነው ...ወይንስ የእምነት መጓደል እንዲ ባንቺ ብልጭልጭታ እንድናብድ የሆነው ያውም እኮ የውሸት ሆነሽ ሳለ ... እ ጀነት እየፈለግን በዛው ልክም እረፍትን የመፈለጋችን ምክኒያት ምን ይሆን? ስለ ጀነት ምን ነበር ያልከኝ "ፈላጊዋ ግን እንዴት ሊተኛ ቻለ " አደል እምም

( glamor)
31 viewsGlamor, 16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 17:16:03 የሴት ልጅ ክብር

ሴትን ልጅ ማብቃት

[ክፍል ሶስት]

ያኔ በርግጥ ባሮች ነበርን። ግና ነፃነት እንዳለን አስተማሩን። የርሱ ቁስና ዕቃ ነበርን፤ ግና እነርሱ እድገት ነው ብለው አማለሉን። በህወት ውስጥ የኛ አላማ ማሳያና ማሻሻጫ፣ እንዲሁም ወንድን ልጅ መሳብ እና ውብ መስሎ መታየት እንደሆነ ስላስተማሩን የኛ ገላ የተፈጠረው ለመኪናቸው ማሻሻጫ መሆኑን ማመን ግድ ነበር ። ግና ይህን ሁሉ ሲሉ ውሸታቸውን ነበር።

ገላሽም ሆነ ነፍስሽ የተፈጠሩት ለሌላ ከፍ ላለ ነገር ነው። አላህ በቁርኣኑ እንዲህ ይለናል ፦يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَٰكُم مِّن ذَكَرٍۢ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَٰكُمْ شُعُوبًۭا وَقَبَآئِلَ لِتَعَارَفُوٓا۟ ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌۭ
<<እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡>>(አል-ሑጁራት 13)

ስለዚህ አንቺ ሴት ልጅ ሆይ የተከበርሽ ነሽ ። ግና ከወንድ ልጅ ጋር ባለሽ ግንኙነት አንፃር ማለትም እነርሱን ከመሆን አሊያም እነርሱን ከማስደሰት አንፃር አይደለም ክብርሽ የሚለካው። እንደ ሴት ልጅ ያንቺ ክብርና ደረጃ የሚለካው በወገብሽ ቁጥር ወይም በሚያደንቅሽ ወንድ ብዛት አይደለም። እንደ ሰው ልጅ ያንቺ ክብርና ደረጃ የሚለካው ከፍ ባለ መለኪያ ነው። በመልካምነት እና ለአላህ በሚኖር ፍራቻ ነው። በምድር ላይ ያንቺ የመፈጠር ዓላማ የፋሽን መፅሄትቶች ከሚሉት ከፍ ያለ ነው። ማራኪ እና ለወንዶች ቀልብ ሳቢ ሆኖ መታየት አይደለም።

የኛ ምሉእነት የሚገኘው ከአምላካችን ጋር በሚኖረን ግንኙነት ነው ።ግና አሁንም ከልጅነታችን ጀምሮ እኛ ሴቶች በወንድ ልጅ እስካልተሟላን ድረስ ሙሉ የሰውነት ደረጃ ፈፅሞ ልንደርስ እንደማንችል ነው የተነገረን። እንደ ሲንደሬላ ታሪክ ሁሉ ልዑል ወንድ መጥቶ እስካላዳነን ድረስ እኛ ረዳት የለሽ ደካሞች እንደሆንን ነው ማህበረሰባችን ያስተማረን። እንደ ምርጥ እንቅልፍ ሁሉ ልዑሉ መጥቶ በስሱ ካልሳመን በስተቀር የኛ ህይወት ሙሉ በሙሉ ሊጀመር እንደማይችል ነው የተነገረን ። ማወቅ ያለብን ነገር የትኛውም ልዑል ሕይወታችንን ሊያሟላው አይችልም ። የትኛውም ጀግና አያድነንም። የሚያድነን አላህ (ሱብሀነሁ ወተዓላ) ብቻ ነው።
....

°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
° በዳሩል አርቀም °
° የተዘጋጀ °
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
ምንጭ(ልብህን አስመልስ ከሚለው መፅሀፍ)

.... የመጨረሻው ክፍል ይቀጥላል





60 viewsGlamor, 14:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 19:24:22 የሴት ልጅ ክብር

ሴትን ልጅ ማብቃት

[ክፍል ሁለት]

እሷ ያላስተዋለችው ነገር ቢኖር አላህ (ሱብሀነሁ ወተዐላ) ወንዶችንም ሆነ ሴቶችን በተመሳሳይነታቸው ሳይሆን በልዩነታቸው ለሁለቱም ክብር የሰጠ መሆኑን ነው ። ግና ወንዶችን እንደሰውነት ውሀ ልክ የተቀበልናቸው እንደሆነ የሴት ብቻ የሆነ ነገር ሁሉ ዝቅ ብሎ አሊያም ምንም ሆኖ ይታየናል ። የስስ ስሜት (እዝነት) ባለቤት መሆንና የተሟላ የእናትነት ባህሪን መላበስ ድክመትና ልፍስፍስነት ይመስለናል። የወንድ ነው ተብሎ በሚታሰበው በአካላዊ ሻካራነት እና የሴት ነው ተብሎ በሚታወቀው ከፍ ያለ ርህራሄ መካከል በሚደረገው ጦርነት ወንዳወንድነት ተመራጭና የበላይ ሆኖ መታየቱ ይገርማል።


ወንድ ልጅ ያለው ነገር ሁሉ ጥሩ ነው ብለን የምናስብ ከሆነ የራሳችንን ሚና እንዘነጋለን። በሁሉ ነገር ውስጥ ከወንድ ልጅ አንፃር ምላሽ ምንሰጥ ነው የሚሆነው።ወንድ ልጅ የሆነ ነገር ካለው እኛም እንዲኖረን እንፈልጋለን። ወንድ ልጅ የመጀመሪያው የሶላት ሶፍ ላይ የሚሰግድ ከሆነ ያ ቦታ ለኛም ምርጥ ሆኖ ይታየናል።ስለሆነም በመጀመሪያው ሰልፍ ላይ ለመስገድ እንመኛለን። ወንድ ልጅ ኢማም ከሆነ ፤ኢማም የሆነ ሰው ለአላህ የቀረበ እንደሆነ ይሰማናል፤ እናም ሶላት ካልመራን ፣ካላሰገድን እንላለን። በአንድ የሆነ ቦታ ላይ የተሳሳተ ግንዛቤ በመያዛችን በዚህች ምድር ላይ የመምራት እድል መሰጠት አንድ ሰው አላህ ዘንድ ያለው ደረጃ ከፍ ያለ ነው ብለን እናስባለን።

ሙስሊሟ ሴት በዚህ መልኩ ራሷን ዝቅ ማድረግና መጉዳት የለባትም ።ውሃ ልኳ አምላኳ ነው ደረጃዋን የሚያስቀምጥላት ፣ክብሯን የሚመዝንላት ፣የሚመዝናት ወንድ ልጅ አያስፈልጋትም።ከወንድ ልጅ አንፃርም ራሷን መመዘን የለባትም።


ግልፁን ለመናገር እኛ ሴቶች ክብራችንን የምናወርደው ያልሆነውን ነገር ለመሆን ስንሞክር ነው። በርግጥም ወንድ ልጅ መሆን አንፈልግም። እኛ ሴቶች በርግጥ እውነተኛ ነፃነት ላይ ልንደርስ የምንችለው ወንዶችን መምሰል ስናቆምና በአምላካችን የተሰጠንን ውበትና ልዩነታችንን ስናከብር እና ዋጋ ስንሰጠው ብቻ ነው።

ሌላው በስፋት የተሰራጨውና ለሴት ልጅ እንደአለቃና መሪ ሆኖ የተቀመጠው የማንነቷ መለኪያ "ውበት" የሚለው ነው ። ከልጅነታችን ጀምሮ እኛ ሴቶች በማህበረሰባችን የተሰጠን ግልፅ የሆነ ት/ት አለ።"ቀጭን ሁኚ"፣"አማላይ ሁኚ"፣"ሳቢ ሁኚ"...ካልሆነ ምንም ዋጋ የለሽም የሚል መልዕክት ።

ስለሆነም ለዚሁ ስንል ሜክአፕ መቀባት፣ ቁምጣ እና ሚኒ መልበስ እንዳለብን ተነገረን። ህይወታችንን ፣ሰውነታችንን እና ክብራችንን ቆንጆ ሆኖ ለመታየት ስንል አሳልፈን መስጠት እንዳለብን ታዘዝን። የቱን ያህል ብንሰራና ብናደርግም ክብር የሚኖረን ወንዶችን በምናስደስተውና ለነርሱ ቆንጆ ሆነን በምንታየው ልክ መሆኑን እከማመን ደረስን። ስለሆነም ነው ፊታችንን ለመዋቢያ ዕቃዎች እንዲሁም ሰውነታችንን ለማስታወቂያ ለመሸጥ ያቀረብነው ።

....

°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
° በዳሩል አርቀም °
° የተዘጋጀ °
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
ምንጭ(ልብህን አስመልስ ከሚለው መፅሀፍ)





73 viewsGlamor, 16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-31 16:55:11 የሴት ልጅ ክብር

ሴትን ልጅ ማብቃት

[ክፍል አንድ]

የአላህ መልክተኛ (አለይሂ ሰላቱ ወሰላም)
ባልደረቦች የእስልምናን መልዕክት ለማድረስ ብለው ወደ አንድ ከተማ ሲገቡ ከመልክተኛው የተቀበሉትን መልዕክት ውብ በሆነ መልኩ ነው ሚያስተላልፉት ።እንዲህ ይላል የእርሳቸው መልዕክት ፦"እኔ የመጣሁት ከባሮች ባርነት የባሮች ጌታ ወደ ሆነው ባርነት ነፃ ላወጣችሁ ነው "
------------------------------------------------
በዚህ አረፍተነገር ውስጥ አንድ የሆነ ምርጥ መልዕክት አለ። በቃላቱ ውስጥ የተደበቀ ሲሆን ሁሉንም በተለይ ተጎጂ የሆነውን የማህበረሰብ ክፍል ለማብቃት እንዲሁም ወደ ነፃነት ለመድረስ ትክክለኛው ቁልፍ ነው።

ምን መሰለህ ...አንተ ወይም እኔ ከፈጣሪያችን ውጪ አንድ ነገር እንዲገዛን ከፈቀድን ፤ ስኬታችንን ደስታችንን ጥቅማችንን ከዚያ ነገር አያይዘን በዝምታ ነገሮችን የምንቀበል ከሆነ ያጎጂ የሆነ ባርነት ነው። ያ ራሴን የስኬቴ እና የውድቀቴ ሁሉ ፈላጭ ቆራጭ ወሳኝ አድርጎ የሚያቀርበው ነገር እኔን የሚቆጣጠር አለቃዬ ነው የሚሆነው ማለት ነው ።

ሴትን ልጅ ሊገዛ የሚችልና አለቃዋ የሆነ ነገር በየጊዜው የተለያየ መልክ ይዞ ዘመናትን ተሻግሮ ዛሬ እዚህ ላይ ደርሷል። ለረጅም ዘመን ለሴት ልጅ መለኪያ ተደርጎ በስፋት የሚታወቀው ወንድ ነው። ግና ብዙን ጊዜ እኛ የምንረሳው ነገር ቢኖር አላህ ለሴት ልጅ ክብር የሰጠው ከእሱ(ሱብሀነሁ ወተዐላ) አንፃር ባላት ግንኙነት እንጂ ከወንድ ልጅ ጋር ባላት አቀራረብ አይደለም ። ግና ምእራባውያን የሴትነትን ነፃነት አቀንቃኞች አምላክን ከስፍራው በማንሳታቸው እንደ መለኪያ የቀረው ወንድ ልጅ ብቻ ነው ። ስለሆነም ምዕራባውያን የሴትነት ነፃነት አቀንቃኞች ወንድ ልጅን መለኪያቸው ለማድረግ ተገደዱ።ይህን በማድረጋቸውም ምክንያት ለሴት ልጅ የተሳሳተ መለኪያ ለመቀበል ቻሉ። ሴት ልጅ "ሙሉ ሰው " የምትሆነው እንደመለኪያዋ እንደ ወንድ ልጅ ስትሆን ብቻ ነው አሉ።

-----------------------------------------------
ወንድ ልጅ ፀጉሩን አጭር አድርጎ ሲቆረጥ ሴቷም ካልተቆረጥኩ አለች።እነኚህን ነገሮች ያሰበችው ወዳና ከመጀመሪያው አስባበት ሳይሆን "መለኪያ /ውሀ ልክ" ነው ተብሎ የታሰበው ወንድ ልጅ ስለተሳተፈበት ብቻ ነው።

.....

°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
° በዳሩል አርቀም °
° የተዘጋጀ °
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
ምንጭ(ልብህን አስመልስ ከሚለው መፅሀፍ)





82 viewsGlamor, 13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 11:37:24 ቅርባችን መሰሎን ልንዳስሰው ስንዳዳ ስንቱ ደብዛው ጠፍቶ አስደነበረን .......!? ስንቱ ተጣግቶን እንዳልነበር ልንጨብጠው ስንሽት እንደጉም ብንንንን...... አለ ፤ ሰንቱ.....!?ለምልከታ ቅርብ የመሰለ ለመዳሰስ ሲሹ ግና ዉሉ ማይጨበጥ ስንት አስማተኛ ህልም አለ ?
ስንቴ አምነኸህ ስትጠጋው፡ ስንቴ ነው የከዳህ ግን?

samiya T


14/02/14
40 viewsGlamor, 08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 08:54:37 ( ነሱሀ አወል)

.........

" ከአለም ጩኸት መሸሽም እረፍት አለው...እስቲ አንዳንዴ ዝም እንበልና ጆሮአችንን ላለማድመጥ አንጠቀመው...አይሻልም?...ከነፍሳችን ጋር በሹክታ ብናወጋስ...መጯጯሁ ቢቀርብንስ? " እላለሁ

http://t.me/Nesuhaawel_poem
46 viewsGlamor, 05:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ