Get Mystery Box with random crypto!

Bilal Media & Communication

የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication B
የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication
የሰርጥ አድራሻ: @linkbi7
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2022-11-02 12:31:10 ራስን መሆን!

ለእግርህ የተሰራ ጫማ ትፈልጋለህ እንጂ ለጫማው ስትል እግርህን አፍርሰህ አትሰራውም፤ ታዲያ ለማን ብለህ ነው የማታምንበትን የምታደርገው? ሰዎችን ለማስደሰት ለምን ራስን ትጎዳለህ? ወዳጄ ሁሌም ከራስህ ጋር የምትጣላው ለዛ እኮ ነው። 

ያመንክበትን ማድረግ አላማህን መኖር እየቻልክ፤ ልብህ የሚያምንበት ብዙ ነገር እያለ ለሰዎች ስትል ለምን ነገ የሚቆጭህን ዋጋ አሁን ትከፍላለህ? ራስን መሆን ዋጋ ያስከፍላል ግን ፍሬው ጣፋጭ ነው
35 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 22:11:56 የወደድኳቸውን ብቻ ነው የምፈትነው ሲል አሏህ፣
ሕመሜን እንደ ክብር ቆጠርኩት!

አባ ሑረይራ ረዲየላሑ አንሁ
27 viewsGlamor, 19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 15:06:58 ሳዑዲና ሃሎዊን
~
ሰሞኑን በሳዑዲ ሪያድ ውስጥ ሃሎዊን የሚያከብሩ ሰዎች መታየታቸውን ተከትሎ ጫጫታ እያየን ነው። የሳዑዲ መንግስት ላይ፣ ከዚያም በሱ በኩል አቆራርጦ ዑለማዎቹ ላይ፣ አሁን ካሉትም አልፎ ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ ላይ የሚዘምቱ ሰዎችን በተደጋጋሚ አይቻለሁ። የሆነ ነገር በለጠፍኩ ቁጥር ደጋግመው እየመጡ 'ኮሜንት' ላይ ብዙ ነገር የሚለቀልቁም ገጥመውኛል። "ስለዚህ ግን ትንፍሽ አትሉም" ይላሉ። ብዙዎቹ ከሁኔታቸው መውሊድን በማውገዛችን ቂም ያረገዙ እንደሆኑ ያስታውቃሉ።

ሃሎዊን ምንድነው?
-
የእንግሊዝኛ መዝገበ ቃላት ስመለከት ያገኘሁት እንዲህ የሚል ነው፦
Halloween "የሁሉም ቅዱሳን ቀን" ማለት ሲሆን በአብዛኛው እንግሊዝኛ ተናጋሪ በሆኑ ሃገራት የሚከበር በዓል ነው፡፡ የሚከበረውም በፈረንጆች October 31 ነው። ህፃናት የተለዩ አስፈሪ ልብሶችን በመልበስ በየቤቱ እየዞሩ ከረሜላና መሰል ነገሮችን ይጠይቃሉ።
ምንጭ፦ http://en.wiktionary.org/wiki/Halloween

መነሻው ኬልቲክ አካባቢ ቢሆንም አሜሪካ ከገባ በኋላ ወደሌሎች ሃገራት ተሰራጭቷል። ከህፃናት አልሮ በ"አዋቂዎችም" ይከበራል። የሰይጣን አምልኮ ነው እያሉ የፃፉ አይቻለሁ። ሊሆን ይችላል። እኔ ግን ማረጋገጥ አልቻልኩም። በዓሉ መነሻው የጣዖታውያን ልማድ እንደሆነ፣ ከዚያም ከፊል ክርስቲያኖችና የሁዶች እንደሚያከብሩት፣ ከክርስቲያኖችና የሁዶች ውስጥ እራሱ አጥብቀው የሚያወግዙት እንዳሉ አንብቤያለሁ።

ሃሎዊን በኢስላም
~
በኢስላም የትኛውንም የጃሂሊያ (ኢስላማዊ ያልሆነ) ስርአት በዓል ማክበር አይፈቀድም። ነብያችን ﷺ የመዲና ሰዎች ሲያከብሯቸው የነበሩ የፋርስ ዞራስቲያኒዝም ሃይማኖት በዓላትን መከልከላቸው የሚታወቅ ነው። በተጨማሪም "በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው" ብለዋል። [አቡ ዳውድ፡ 4031] ይሄ እጅግ አስፈሪ ማስጠንቀቂያ ነው።

ሃሎዊን በሳዑዲ
~
ሳዑዲ ውስጥ እስከ ቅርብ አመታት ድረስ የሃሎዊን በዓል አልነበረም። የሚፈልግ ስለሌለ ሳይሆን በመንግስት ስለተከለከለ ነበር። የክልከላውን መላላት ወይም መነሳትን ተከትሎ ግን - በአንድ ዌብሳይት ላይ እንዳየሁት - ከባለፈው ዓመት ጀምሮ እየተከበረ ነው። ይሄ በጣም ዘግናኝ ጥፋት ነው። ጥፋቱ በሳዑዲ ስለተፈፀመ የሚቀየር ብይን የለም። ማንም ለዚህ ወግኖ የሚከራከርም የለም። ከኖረም ባይፈፅመው እንኳ የጥፋቱ አካል ነው።

ለኢኽዋኖ - አሕባሽ መን-ጋዎች!
~
ለብዙኛ ጊዜ ደጋግሜ የምናገረው ነገር ቢኖር ሳዑዲ ውስጥ ከዚህም ውጭ ብዙ ጥፋቶች እንዳሉ እናውቃለን። አንዳንድ ቂላቂሎች እንደሚያስቡት ሳዑዲን ፍፁም አድርገን የምንስል አይደለንም።
ግን እናንተ የመጮሁንም የማስጨሁንም ሞራል ከየት አገኛችሁት? ምዬ እናገራለሁ ከአብዛኛቻችሁ ጩኸት ጀርባ ያለው ለኢስላም መቆርቆር አይደለም። የጩኸታችሁ ቀዳሚ መንስኤ ቡድናዊ ልዩነት ነው። ይሄ በዓል'ኮ ዘንድሮ ብቻ ሳይሆን ቀደም ብሎ ጀምሮ ቱርክ ውስጥ ይከበራል? በዚህ መልኩ አስጩሃችሁት ታውቃላችሁ? ለምን? አንዱ ሳዑዲን በዚህ ሰበብ እያብጠለጠለ በለቀለቀበት ረዥም ፅሑፍ ውስጥ ኳታርን ሲያወድስ አይቻለሁ። እስኪ Halloween in Qatar ብለህ ጉግል ላይ ፈልግ። የእውነት ለዲን መቆርቆር ከሆነ ምክንያታችሁ ምነው ስለ ኳታር እስከዛሬ አልጮሃችሁም?! እነዚህ አካላት በተመሳሳይ ጊዜ ብዙ ፊት የሚያሳዩ፣ በተመሳሳይ ጉዳይ የተለያየ ስፍር የሚሰፍሩ፣ ሃይማኖትን ለፖለቲካዊ ንግድ የሚጠቀሙ ቆሻ - ሻ ፍጥረቶች ናቸው።
ሲጀመር የኢኽዋን አንጃ በምን መለኪያ ነው ከሳዑዲ መንግስት የሚሻለው? የቡድኑ መሪ ዑመር ቲልሚሳኒይ ገንዘብ እየከፈልኩ የፈረንጅ ዳንስ ተምሬያለሁ፣ ሲኒማ ለማየት ብዬ ሁለት ሶላቶችን በአንድ ላይ ጀምዕ እያደረግኩ እሰግድ ነበር አላለም? ቀርዷዊ ነፃነትን መተግበር ከሸሪዐ ይቀድማል አላለም? የቡድኑ መስራች ሐሰነል በናና ዩሱፍ አልቀረዳዊ በተጨባጭ ሐዲሥ የተረጋገጠውን የመህዲን መምጣት አላስተባበሉም? መውዱዲ የደጃልን መምጣት አላስተባበለም? ቱራቢ በርካታ መረጃዎችን ረግጦ የቀብር ቅጣት የሚባል የለም፣ ነኪርና ሙንከር የሚባል የለም አላለም? ነብያት መዕሱም አይደሉም አላለም? የዒሳን ዳግም መምጣት አላስተባበለም? ቀረዳዊና ሙርሲ የክህደት ቁንጮ ለሆኑ ጳጳሶች አላህ እንዲምራቸው ዱዓ አላደረጉም? ሰይድ ቁጥብ ከሶሐቦች አልፎ ነቢያትን አልጎነተለም? ሙስሊሙን ኡማ በጅምላ ከኢስላም እያስወጣ አልፃፈም? ሰዕድ አልከታቲኒ በግብፅ ምርጫ ብናሸንፍ አስካሪ መጠጥ አንከለክልም፣ የብልግና ድረ ገፆችን አንዘጋም አላለም? እስኪ ምናችሁ ተሽሎ ነው ምላሳችሁን የምታሾሉት?
የእውነት ለኢስላምና ለሙስሊሞች ተቆርቁራችሁ ከሆነ ይሄንን እያንሸዋረረ የሚያሳያችሁን ቡድናዊ መነፅር አሸቀንጥራችሁ ጣሉና በስርአት አስተምሩ። ኢስላም በሚያስተምረው መልኩ ከሃሎዊንም፣ ከቫሌንታይኑም፣ ከሳዑዲ ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ሃገራት ብሄራዊ በአላትም፣ ከኢሬቻም፣ ከገናም፣ ከመስቀልም ፣ ከመውሊድም፣ ወዘተ አስጠንቅቁ። ከፊሎቻችሁ'ኮ ለመስቀል ስታፀዱ እናውቃችኋለን! ከፊሎቻችሁኮ ኢሬቻን ለማውገዝ የምትሽኮረመሙ ናችሁ። ከሌሎቻችሁ'ኮ ሉሲን ተከትላችሁ ከሃገር ሃገር ስትዞሩ ነበር። የምን ማስመሰል ነው? እምቢ ብላችሁ ስለ ሳዑዲ ብቻ ከሆነ ማውራት የምትፈልጉት ቢያንስ በሌላ ሃገር የሌለ ጥፋት እየጠበቃችሁ ብትጮሁ ይሻላችኋል! ያለበለዚያ ግን ጧት ማታ ሙገሳ በምትሰፈሩላቸው ሃገራት ውስጥ ያለው ሲወጣ አስመሳይነታችሁ ይጋለጣል።

በርግጥ ለኛም ቢሆን የሳዑዲ ጥፋት ይለያል! ምክንያታችን ግን እንደናንተ የገነፈለ ጥላቻ አይደለም። አዎ ከሌሎቹ በበለጠ ሳዑዲ ላይ ይሄ መሆኑ ያመናል። ተሽለው መገኘት እንዳለባቸው ስለምናምን። ለሃገሪቱ ካለን መቆርቆር። የኢስላምና የሙስሊሞች ምልክት (symbol) በመሆኗ።
የአሕባሸና የኢኽዋን ጩኸት ግን "ከፍየሏ በላይ ነው።" የተጠራቀመ ቂም ስላላቸው አጋጣሚ እየጠበቁ ከሳዑዲ መንግስት አልፈው ዑለማዎች ላይ ዘመቻ ለመክፈት ነው አድብተው የሚጠብቁት። የሙዚቃ ኮንሰርት ሲካሄድ ልክ ዑለማዎቹ የፈቀዱ ይመስል እነሱም ላይ ጭምር ይዘምታሉ። ልክ በግልፅ ሙዚቃ የሚፈቅደውን ቀረዷዊን ሲያንቆለጳጵሱ እንደማናውቃቸው። ልክ ቱርክና ኳታር የሙዚቃ ድግስ፣ ከዚህም አልፎ ብዙ ነገር እንደሌለ። ይሄው በቅርቡ ለሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ኳታር ውስጥ የሙዚቃ ድግስ እየተዘጋጀ እንደሆነ አልጀዚራ እየዘገበ ነው። ሪያድ ሲሆን እንደምታወግዙት ደውሐ ሲሆን ታወግዙታላችሁ? አታደርጉትም። ምክንያቱም መስፈሪያችሁ የሚታወቅ ነው። حصانة إخوانية
.
ሁኔታችሁን እያየሁ ልመለስ እችላለሁ፣ ኢን ሻአ'ላህ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
51 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 12:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-30 07:28:43 < " የአዕምሮ ባርነት ሲሉ ምን ለማለት ነው። በየትኛው መንገድ ነው በአእምሮ ባርነት ውስጥ የተዘፈቅነው? >

<< " ይህን በቀላሉ ለመረዳት " ሴት" ን መመልከት ትችላለህ። ሴት በአእምሮ ባርነት ከሚሰቃዩት መሀል ግንባር ቀደሟ ናት። ቅጥ ያጣው የዘመናዊ አስተሳሰብ ነፃነት ከየትኛውም ህብረተሰብ በላይ የጎዳው ሴትን ነው። በየትኛውም ዘመን ሴት ታፍራና ተከብራ የምትኖረው የእምነት መፅሀፎች ላይ እና እምነታቸውን በትክክል በሚተገብሩ አማኞች ህሊና ውስጥ ብቻ ነው። በዘመናችን ሴቶች መኖር የሚፈልጉት በሰዎች አስተሳሰብና በየዘመኑ በሚሰጣቸው ፍቺ እንጂ በእምነታቸው መመርያና ፍቺ አይደለም። ይህን ቅድሚያ እንዳያስተውሉ አዕምሯቸው በቁስ ጥገኛ እንዲሆን ተደርጓል። እምነት የሌላቸው ሰዎች በግልፅ እምነት የለንም ሲሉ ይኮነናሉ ነገር ግን አማኝ ነን የሚሉ ሰዎች ከእምነት መመርያቸው ውጪ ሲሆኑ እምነታቸውን እየተቃወሙና መመርያው ትክክል አይደለም እያሉ እንደሆነ አያስተውሉም። የአእምሮ ባርነት ውስጥ እንዳለን ለመገንዘብ ሴትን የወሲብ ምልክት ማድረጋችን መመልከት እንችላለን። አንድ ወንድ አንዲትን ሴት ሲመለከት ከሰውነት አካላቶቹ በሙሉ ቀድሞ ፈጣን ምላሽ (Active response) የሚሰጠው ብልቱ ነው። ስልኳን ለመቀበል፣ ለመግባባትና ሌሎች ብዙ ጥሩም ይሁን መጥፎ ነገሮችን ለማድረግ የሚያስበው ብልቱ ምላሽ ከሰጠ በኋላ ነው። ለምን ብለን ብንል የአዕምሯችን ቅኝ ገዢዎች የጫኑብን አስተሳሰብ ነው። ሴት አዕምሮዋ በባርነት እንደሚማቅቅ የምታውቀው ስትደፈር ምንም ባለማለቷ ነው። የሙዚቃው ኢንዱስትሪ ይደፍራታል፣ የፋሽን ኢንዱስትሪው ይደፍራታል፣ የፊልም ኢንዱስትሪው ይደፍራታል፣ የመዝናኛው ኢንዱስትሪ በዘመናዊ መንገድ በወርቅ አልጋ አስተኝቶ በአደባባይ ይደፍራታል። በዚህ ረቂቅ በሆነ ደፈራ ሴቷም ደስተኛ ነች። ለመደፈር እንደ መስፈርት የሆኑትን ክብደቷን፣አካላዊ ቁመናዋን መልኳን በማቆንጀት ጊዜዋን ማባከንና አዕምሮዋ ሳይዳብር በእንጭጩ መተው ስኬት እንደሆነ አምናበት ቀና ብላ ትሄዳለች። መልኳን እንጂ ማንነቷን ማቆንጀት ተራ እንደሆነ በአዕምሮዋ ቅጅ ገዢዎች የተበሰረላትን ብስራት አሜን ብላ ተቀብላለች። ስለ ሴት ጥብቅና እንቆማለን ብለው የሚሉት እንኳ ይህን እውነት መመልከት ተስኗቸዋል። በተሰጣቸው ፍቺ ተስማምተው ሌሎችን ለማሳመን ይጥራሉ። በባርነት ለምትማግዳቸውና በባርነታቸው ለሚደሰቱት የፆታ እኩልነት፣ Affirmative action እያልክ የበታችነትን የሚሰብክ እድል መፍጠር፣ ተቋም ማቋቋም ስላቅ ነው። በሀሳብ ባርነት የተጠፈነገ አዕምሮ ስለ መፅሀፍ ሽፋን እንጂ በመፅሀፉ ውስጥ ስላሉት ገፆችና በገፆቹ ውስጥ ስለ ሚከተቡት ነገሮች አይጨነቅም። ሁላችንም እንዲህ እየኖርን ነው ገፅታችንን እውነት እየቀባን ውስጣችን ግን ባዶ ውሸት። ብንደኸይ፣ ብንገዳደል፣ ብንወነጃጀል አይገርምም። ምክንያቱም በባርነት በወደቀ አዕምሮ ሚዛናዊነት፣ አዲስ ሀሳብና ፈጠራ እንዴት ብሎ ሊኖር ይችላል? " >>
        ~~
56 viewsGlamor, 04:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-28 23:15:24 ዑመር ሞቷል? አልሞተም? የህፃኑ ጥያቄ

ዛሬ ሚስቴ በሩን ስትከፍትልኝ ፊቷ ላይ የሀዘን ድባብ ይታያል።
"ምን ተፈጠረ?"አልኳት።"ልጁ,,," አለችኝ።በፍጥነት ወደ ሶስቱ ልጆቼ ክፍል አመራሁ።አንገቱን ሰብሮ አልጋው ላይ ቁጭ ብሏል።እንባወቹ ትንንሽ ጉንጮቹን አርሰውታል።እቅፍ አድርጌ "ምን ሆንክብኝ ልጄ?!" አልኩት።መልስ ሊሰጠኝ አልፈቀደም።ግንባሩን በጄ ደባበስኩ፤አልታመመም።ጥያቄየን ለእናቱ ደገምኩላት ምን ሆኖ ነውበእምቢታዋ ፀናች።ህፃኑ ፊት መናገር እንዳልፈለገች ስረዳ ወደኛ መኝታ ክፍል እንድትሄድ ጠቆምኳት።ህፃኑን ደበስበሰ አድርጌ ወደሷ ዘንድ ሄድኩ።ዛሬ የገጠማትን ስትነግረኝ በደንብ ገባኝ።የታሪኩን መጀመሪያ እሷም አታውቀውም ነበር።የመጨረሻውን ክፍል ብቻ ነው ያየችው።ሙሉ ታሪኩን ባጭሩ እንዲህ አጫወትኳት።
፠ ሁሌ ከመተኛቴ በፊት ከሶስቱ ልጆቼ ጋር ማምሸት ያስደስተኝ ነበር።ረዥሙን ሰውነቴን አጭሯ አልጋቸው ላይ አሳርፌ ከመሀከላቸው ስሆን የሚሰማኝ ደስታ ልክ የለውም።እነሱም በጣም ይደሰታሉ።ታዲያ ታሪክ ሳላወራላቸው በፊት አይተኙም ነበር።አስማ ስለነቢዩሏህ ዩሱፍ ሰምታ አጠግብም፤ፋጢማ ደግሞ ስለ ነቢዩሏህ ሙሳና ፊርዐውን ወይም በሷ አጠራር ስለመልካሙ ሰውየና ስለ መጥፎው ሰው።ህፃኑ ልጄ ግን የተወራለትን ታሪክ ሁሉ በስርአት ያዳምጥ ነበር።
አንድ ምሽት እንደተለመደው የሙሳ ወይስ የዩሱፍ ስል ሁለቱ የየራሳቸው ምርጫ እንዳወራላቸው ሲወተውቱኝ ህፃኑ ልጄ
"_#ስለ_ዑመር_ብኑል_ኸጧብ "
በማለት አስደመመኝ።እንዴት ዑመርን አወቀው?! በፍጹም ስለዑመር ታሪክ አውቼለት አላውቅ!!! ኧረ እንዲያውም ስሙን እንኳ እሱ ፊት ጠርቼ አላውቅም።ለማንኛውም እንዳይከፋ ብዬ ትዝ ያለኝን ታሪክ አወራሁለት።በሌሊት ተነስተው ከተማውን ሲያስሱ አንዲት ልጆቿን ለማስተኛት ምግብ አስመስላ ውሃ እያበሰለቸ ያለችን ሴት አይቶተው እያለቀሱ ተመልሰው በወገባቸው ዱቄት ተሸክመው ራሳቸው አብስለው እንደመገቧቸው ነገርኩት።ደስ ብሎት ተኛ።
በማግስቱ"ዛሬ እኔ ነኝ የምተርክላችሁ" አለ።"እርግጠኛ ነህ?"አልኩት እየቀለድኩ።"አወ" ሲል መለሰል በኩራት መንፈስ።ትላንት ያወራሁለትን ታሪክ ቅንጣት ሳያዛንፍ እንደ ሪከርደር ደገመልኝ።በጣም ገረመኝ።በሚቀጥለው ቀን ስለዑመር እንዳወራለት በጠየቀኝ መሰረት የግብፅ አስተዳደር የነበረው የዐምር ብኑል ዓስ ልጅ የመታው ግብፃዊ ዑመር ጋ ሄዶ ሲከሰው ዑመር ዐምርንም ልጁንም አስመጥተው ቂሷሱን እንዲከፍል እንዳደረጉት ነገርኩት።
በዚህ መልኩ ወር አካባቢ አሳለፍን።አንዳንዴ ስለ ዑመር ተቅዋ
–ሌላ ጊዜ ስለ ፍትሀዊነቱ
–አልፎ አልፎ ስለ ጀግንነቱ ስለ ዙህዱ አወራለት ነበር።አንድ ምሽት "ዑመር ሞቷልን?"ሲል ጠየቀኝ።"አወ"ልለው አሰብኩና ልቡ በዑመር ፍቅር እንደተሞላ አስብኩና መልስ ሳልሰጠው ወጣሁ።በማግስቱ ጥያቄውን ደገመልኝ።አሁንም አረሳስቼ ወጣሁ።ከዛን ቀን በሁዋላ ከልጄ ጥያቄ ለመሸሽ ስል ከልጆቼ ጋ የማምሸት ልምዴን አቆምኩ።
ዛሬ ከእናቱ ጋር ወደ ከተማ ሲወጡ አንዲት ህፃን ልጅ የታቀፈች ሴት ልጇን የምታበላበት ሳንቲም እንዲሰጧት ሰወችን ስትለምን አየ።ህፃኑም "አይዞሽ! አሁን ዑመር ኢብኑል ኸጧብ ለንቺም ለልጅሽም ምግብ ይዞልሽ ይመጣል" አላት።በአካባቢው የነበሩ ሰወች በግርምት እናቱና እሱ ላይ አፈጠጡባቸው።እናቱም የተወሰነ ብር ለሴትዮዋ ካስጨበጠቻት በሁዋላ ልጁን ይዛ ከአካባቢው ተሰወረች።ትንሽ እንደሄዱ አንድ ጡንቻው የፈረጠመ ሰው አንዱን ደካማ ሲደበድበው ያየው ልጄ አላስችል ብሎት "ሰወች ሆይ! ዑመር ብኑል ኸጧብ ደካማውን ሰውየ እንዲያግዘው ጥሩት!"እያለ ጩኸቱን አቀለጠው።ሰወች በህፃኑ ተደንቀው አተኩረው ተመለከቱት።እናቱ ሌላ ጉድ ሳይመጣብኝ ብላ የወጣችበትን ጉዳይ እንኳ ሳታሟላ ወደ ቤት ለመመለስ ተገደደች።እየተመለሱ ሳለ ሌላ ለማኝ አገኛቸው።አሁንም ለሱ ሳንቲም ሰጥታ አለፈች።ቤት ሲደርሱ የዘበኛው ሚስት ባሏ በጠና እንደታመመ የሚታከምበት ገንዘብ እንደሌለውና እርዳታ እንደሚያስፈልገው ስትነግራት ህፃኑ አስገራሚ ጥያቄ ጠየቃት።
–"ዑመር ኢብኑል ኸጧብ ሞቷል???"
እናቱ ደንግጣ መልስ ሳትሰጠው ወደ ቤት ገባች።
ወደ ሳሎን ሲገቡ ቴሌቪዥኑ ተከፍቶ ነበር።ጋዜጠኛ አይሁዶች መስጅደል አቅሷን እንደተቆጣጠሩትና ሰጋጆችን ሲደበድቧቸውና ሲያንገላቷቸው እንደነበር እየዘገበ ነበር።የዚህን ጊዜ ልጄ "ዑመር ብኑል ኸጧብ ሙቷል ማለት ነው"አለና በጣም እየጮኸ ያለቅስ ጀመር።
ዑመር ብኑል ኸጧብ ሞተ
ዑመር ብኑል ኸጧብ ሞተ
ዑመር ብኑል ኸጧብ ሞተ"
ይህን እያወራን ሳለ ልጄ ከክፍሉ ወጣና ወደኔ እየተጠጋ "ዑመር ብኑል ኸጧብ ሞቷል አይደል?" አለኝ።እኔም "እናትህ

እርጉዝ ነች ከሁለት ወር በሁዋላ በአላህ ፈቃድ ዑመርን ትወልዳለች" አልኩት።"ዑመር ብኑል ኸጧብን?" አለኝ።"አወ ዑመርን "አልኩት።ፊቱ ጥርስ በጥርስ ሆነ።እየሳቀ መጣና ተጠመጠመብኝ።
"ዑመር ኢብኑል ኸጧብ
ዑመር ኢብኑል ኸጧብ "እያለ።
እኔም እንባየን እያበስኩ "ረዲየሏሁ ዐንከ ያ ዑመር!" አልኩኝ።
-አወ ዑመር ኢብኑል ኸጧብ ሞቷል–
እሱ የላቀበት ኢስላም ግን አልሞትም!!!
-ዑመር ሙቷል እሱ የሰራበት ቁርኣን ግን አልሞተም!!!
-ዑመር ሙቷል እሱን የወለደች ህዝብ ግን አልሞተችም!!!
-ዑመር ሙቷል በአላህ ፈቃድ ግን ሺህ ዑመር ይወለዳል!!!
ይህ ጥሪየ ነው፦ልጆቻችሁን በኢስላማዊ ተርቢያ አሳድጉዋቸው።ዑመር የሚወለደው ዑመር ከተወለደበት ህዝብ ነውና !!!

ሱብሀነሏህ
72 viewsGlamor, 20:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 20:23:48 .11 አላህ ከኛ-ጋር ነውን ?

መ.11 አላህ በመስማቱ፣ በማየቱ፣ እና በዕቀቱ ከኛ-ጋር ነው. ከፍ ያለው አላህ እንዲህ ይላል: "እንዳትፈሩ እኔ ከናንተ ጋር ነኝ እሰማለሁ እመለከታለሁ(ሁሉንም ነገር)" (ሱረቱ ጣሀ 20:46)
የአላህ መለዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡ “እናንተ ሰሚና ቅርብ የሆነዉን አላህን ነው የምታመልኩት/የምትጠሩት እሱም አላህ ከናንተ ጋር ነው።" (i.e, ከናንተ ጋር ነው ሲባል በእውቀቱ ማለት ነው)
(ሙስሊም ዘግበዉታል)
س١٢ - : مَا هِيَ فَائِدَةُ التَّوۡحِيدِ ؟
ج١٢ - : فَائِدَةُ التَّوۡحِيدِ هِيَ الۡأَمۡنُ فِي الۡآخِرَةِ مِنَ الۡعَذَابِ وَالۡهِدَايَةُ فِي الدُّنۡيَا وَتَكۡفِيرُ الذُّنُوبِ. قَالَ تَعَالَى ﴿ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَلَمۡ يَلۡبِسُوٓا۟ إِيمَـٰنَهُم بِظُلۡمٍ أُو۟لَـٰٓئِكَ لَهُمُ ٱلۡأَمۡنُ وَهُم مُّهۡتَدُونَ ﴾ (سورة الأنعام) (بِظُلۡمٍ: أَيۡ بِشِرۡكٍ).
وَقَالَ ﷺ: (حَقُّ الۡعِبَادِ عَلَى اللهِ أَنۡ لَا يُعَذِّبَ مَنۡ لَا يُشۡرِكُ بِهِ شَيۡئًا) (مُتَّفَقٌ عَلَيۡهِ).
ጥ.12 የተውሂድ ጥቅሙ ምንድነው ?

መ.12 የተውሂድ ጥቅም በኣኺራ ከቅጣት ሰላም መሆን, በአዱኒያ/በምድር ላይ ሂዳያ/ ቀጥተኛዉን መንገድ መመራትና እንዲሁም ከወንጀል ምህረትን ያስገኛል:: ከፍ ያለው አላህ እንዲህ ይላል: 

“እነዚያ ያመኑት በእምነታቸዉም በደልን(ሽርክን) ያልቀላቀሉ እነዚያ ለነሱ ሰላም አላቸው እነሱም ወደ-ቀጥተኛው መንገድ የተመሩ ናቸው።" (ሱረቱ አል-አንዓም 6: 82)

የአላህ መለዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡

“አላህ ዘንዳ ለአንድ ባሪያ ያለው ሀቅ በሱ በአላህ ላይ ምንም ከላጋራ ላይቀጣው ነው".
ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበዉታል

ኢንሻ አሏህ ይቀጥላል
https://t.me/HidayaTv
https://t.me/HidayaTv
82 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 07:18:36 አንዳንድ ውሻ የሰው እግርን ለመንከስ ሲያስብ እየላሰና እየተላፋ ያዘናጋል!!! ከዛም ንክሻውን ይፈጽመዋል! ያኔ በራሳችን መገረም ሳይኖርብን አይቅርም! ለምን ቢሉ አሳንሰን ያየነው አካል ከኛ ተሽሎና በልጦ ስለተገኘ!!!
108 viewsGlamor, 04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-22 20:12:50
ብለዋቹሀል
125 viewsGlamor, 17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 19:17:17 #እንደራስ_2

(ነሱሀ አወል)

የሆነ ትልቅ ግንብ ነገር ነው። በመሰላል እየወጣሁ ይመስለኛል። ድንገት ከግንቡ አጋማሽ ከመሬት ራቅ ያለ ቦታ እንዳለሁ መሰላሉ ይሰበራል። እና መሬት ላይ እፈጠፈጣለሁ። አንዳንዱ ምፅ! እያለ ከንፈሩን ይመጣል። አንዳንዱ ' ምን አቀበጣት' ይለኛል። እኔ ግን በአይኔ ሳማትር የነበረው የመሰላሉ መሰበር አለመሰበር ላይ ነበር።

እኔም 〖 እህቴን〗 እያልኩ ጩኸቴን አቀልጠው ጀመር። ሰው ግራ ተጋብቶ ራሴን ወዳለማወቅ ደረጃ የደረስኩ አይነት ስሜት የተሰማው ይመስላል። አላመመኝም ሳይሆን እይታየ ያለው መሰላሉ ላይ ነበር። መሰላሉ ደግሞ እሷ ነች እሷ!።

〖መሰላሌን አድኑልኝ ከዚህ ወዲህ ምን ብየ ነው ዳግም የምወጣው ምን ብየ ወደ ላይ እራመዳለሁ እባካችሁ መሰላሌን〗
በዚህ መሀል ነበር በፊቴ ላይ የተረጨው ውሀ ቅዝቃዜ የቀሰቀሰኝ።

❮ ምን ሆነሻል?❯

〖 መሰላሌ 〗 ብየ በእጆቼ ደረቴን እንደደገፍሁ ሳለ

❮የምን? መሰላል የኔ ❯አለችኝ

〖መሰላሌ አለሽ አ? አልሃምዱሊላህ ተሰብረሽ ያላዳኑሽ እኔን ለማዳን ሲጣደፉ ማያት ሲያም በአላህ ኡፍፍፍፍፍ 〗በረጅም ተነፈስሁና እቅፍ አደረግኳት።

❮ግራ አጋባሽኝ እኮ ከቅዠትሽ አልነቃሽም መሰለኝ አውርተሽ አላቆም ስትይኝ እኮ ወላሂ የደነገትሁት አደነጋገጥ ❯ ብላ ከት ብላ ስቃ ❮ወይ መሰላል❯ አለች።

ብታይ ብየ ያለሁትን ሁሉ ዘከዘኩላት። ተናደደች።

❮እኔ መሰላልሽ አይደለሁም። እኔ ሳልኖር መኖር እኔ ወድቄ መራመድ እኔ ኖሬ አንቺ መኖር እንዳለ አስቢ እሺ ። መቆም ማለት ራስችን ችለሽ መቆም ነው እንትና ከሌለች ውሀ በላኝ እገሌን ካልጠገኑት መሰበሬ ጠና ብሎ ነገር የለም። መሰላልሽ የራስሽ ጥረት ነው የራስሽ ጥንካሬ የራስሽ የምታልፊያቸው ፈተናወች የራስሽ ብዙ ብዙ ነገር ደግም ተነስተሽ ጠግነሽ የምትወጪበት የራስሽ የሆነ ነገር ገባሽ?

ዝም አልኩ።

ታውቂያለሽ ነገ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አይታወቅም። ደግሞ እኔም እንደሰው ብዙ ችግር ይገጥመኛል። ብዙ ውድቀት ስወድቅ ሌላ ሰው ይዤ መውደቅ ለኔ ሽንፈት ነው ሊያውም የኔ የምለውን ሰው። ምፈልገው ስወድቅ ልትደግፊኝ ልታበረችኝ አንቺም ስትዝይ ላጠነክርሽ እንጂ ተያይዞ መውደቅ ብሎ መውደድ የለም። አንድ አባት ሲሞት የአባቱን ህልም የሚያሳካ ልጅ እንጂ ከአባቴ ወዲህ አለም አበቃች የሚል መሆን የለበትም። ተስፋ በሰወች እጅ ላይ የተንተራሰ አይደለም። ተስፋ አላህ ነው።መኖር በእርሱና ለእርሱ ነው። እና የተደገፍሽበት ምርጉዝ ካንቺ የበለጠ ደካማ መሆኑን እወቂ። ብርቱ መሆን የምትችይው ጌታሽን ስትገደፊ ብቻ ነው። አንድ ማወቅ ያለብሽ ነገር ደግሞ በህይወትሽ ማንም ሰው ላይ መንተራስ የለብሽም ህልምሽም፣ መቻልሽም፣ ስኬትሽም በአእምሮሽና አእምሮሽን በተፈረ ብቻ ሊንተራስ ይገባዋል። መሰላልሽን ስትፈልጊ ማለት ያለብሽ ሰው አይደለም። ፈጣሪሽን ነው። ❯ ብላኝ የለበስኩትን ብርድ ልብስ ፊቴ ላይ ወረወረችው።

〖 አውቃለሁ ማረፊያም መደገፊያም አላህ ነው። ግን ዱንያ ላይ ሲሆን ሰው ያስፈልገኛል። አስፈላጊዋ ሴት ደግሞ አንቺ ነሽ...እህቴ! 〗እንባወቼን በግድ ታቀፍኳቸው።
ሊዘንቡ ጥቂት ነው የቀራቸው።

❮ አው ነገር ግን እስከ መደገፍ እስከ ተስፋ መሆን አትድረሺ ያ ማለት መጥፎ ነገር ቢከሰት የሚከተለው ምን ሊሆን ነው። ከወደቀችው እህትሽ ጋር መውደቅ?እ?❯

〖 ቲሽ! ምን ሆኜ ነው ። ሁሉም ነፍስ ለራሱ መጠየቁን መዘንጋቴ...ስለምወድሽ መሰላሉ አንቺ መሰልሽኝ...መሰላሉ የራሴ ውድቀት ሊሆንም ይችላል ዳግም ጠግኜ የምወጣበት ለነፍሴ የተበጀ ፈተና...ግን እወድሻለሁ〗

ዝም ብላ ወጣች ልቧ በድብልቅልቅ ስሜት የተወረረ ይመስለኛል።

⨳ መደገፍ በአላህ ላይ ሲሆን ምንኛ ተደላደለ ⨳
147 viewsGlamor, 16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-16 21:40:58 ሒጃብ የሚለበሠው ለአልላህ ተብሎ እንጂ ለሠው አይሁን መንገድ ላይ ስትሄዱ የምታውቁትን ሰው ስታዩ ማስተካከል ምናምን ብንቆጠብ የተሻለ ነው ባረከልላሁፊኩም

ነገ ሰኞ ነው ተማሪ ከሁለት ቀን መለያየት በኋላ የሚገናኙበት ነው እና አጅ ነቢ(ባእድ) ወንዶች/ሴቶች ለመጨበጥ ሲመጡ ልባቸው ንፁህ የሆነው ሀቢቢ ሠለልላሁዐለይሂ ወዐላ አሊሂ ወሰለም እንዳሏቸው በላቸው
"እኔ ሴቶችን አልጨብጥም" በልና ዘላለማዊ እርካታን ተጎናፀፍ ሀቢቢ ቢከብድህም አድርገው

Ustaz suleyman
133 viewsGlamor, 18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ