Get Mystery Box with random crypto!

Bilal Media & Communication

የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication B
የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication
የሰርጥ አድራሻ: @linkbi7
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2022-11-23 22:19:24 አንዳንዴ የቃላቶችን አቅም ምትረዳው አንተ ማለት የፈለከውን ትተው በሌላ ሲገልጹ ሌሎቹም ለነርሱ በሚገባቸው ሲረዱት ነው።
17 viewsGlamor, 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-23 14:11:55 ትልቅ እውነት ከዩሱፍ አልቀረዷዊ
~
ከኢኽዋነል ሙስሊሚን አበይት መገለጫዎች ውስጥ አንዱ አይን ያወጣ ግነት ነው። በማጠልሸትም በማወደስም ያለ ግነት።

* የሚጠሉትን አካል የፈለገ መልካም እሴት ቢኖረው እንኳ፣ አየን የሚሉት ጥፋት ራሳቸው ዘንድ በሰፊው የሚገኝ ቢሆን እንኳ በተለየ ያጠለሹታል። ሳር ቅጠሉ እንዲጠላው አድርገው ያንቋሹታል። ኢስላምን ለማጥፋት የሚያሴር እንደሆነ አድርገው ያለ ረፍት ደጋግመው በማንቋሸሽ ገፅታውን ጥላሸት ይቀቡታል።
* የወደዱትን ደግሞ የሌለውን ያልተከሰተውን ሁሉ እየፈጠሩ ያደንቁታል። መልካም ስራዎች ካሉትም ለሌሎች የማያደርጉትን ትንሹን አግዝፈው፣ ጥቂቱን አብዝተው ያራግቡለታል። ጥፋቶቹን ይሸፍኑለታል። ማለፊያ ሰበብ ይደረድሩለታል።

ሺዐ፣ ኻሪ -ጂ፣ ወደ ሺርክ የሚጣራ ቁቡሪ፣ ሌላው ቀርቶ ከሃዲ እንኳ ቢሆን የወደዱትን ሰማይ አድርሶ በመስቀል የታወቁ ናቸው። የሙስሊሙ አለኝታ፣ ኢማም፣ ዘመኑን የቀደመ፣ ... እያሉ ሰማይ ያደርሱታል። ከነብይ በላይ ሁሉ አድርገው ሊያደንቁት ይችላሉ። የሚሞግተኝ ካለ ለያንዳንዷ ንግግሬ መረጃ መጥቀስ እችላለሁ።

ይሄ በፍቅርም በጥልም የተጋነነ ስፍር መስፈር እንደ ቡድን የኢኽዋን መታወቂያ እንደሆነ ዩሱፍ አልቀረዷዊ እንዲህ ሲል ይመሰክራል፦
‌‏"‏وأقول بأسف! لقد كان رجال المباحث أصدق في الحكم علينا من إخواننا الذين عرفناهم وعرفونا وعايشونا وعايشناهم. وهذا مايعاب على كثير من الإخوان، أنهم إذا أحبوا شخصا رفعوه إلى السماء السابعة، وإذا كرهوه هبطوا به إلى الأرض السفلى."
“እያዘንኩ የምናገረው ነገር ቢኖር ከምናውቃቸውና ከሚያውቁን፣ ከተኗኗርናቸውና ከተኗኗሩን ወንድሞቻችን ይልቅ የመንግስት ደህንነት ሰዎች በኛ ላይ የሚናገሩት ይበልጥ እውነተኛ ብይን ነው፡፡ ይህ ብዙ ኢኽዋኖች የሚወቀሱበት ነው፡፡ እነሱ አንድን ሰው ከወደዱት ወደ ሰባተኛው ሰማይ ያነሱታል፡፡ የጠሉት ጊዜ ደግሞ ወደ ሰባተኛው መሬት ያወርዱታል!” [ሲራ ወመሲራ፡ 2/89]
.
ያያያዝኳቸው ምስሎች በቀጠሩ የኳስ ድግስ ላይ የሰለሙ ብለው ያቀረቧቸው ቅጥፈቶች ናቸው። ከስንት አመታት በፊት የወጡ ምስሎችን ፎቶሾፕ እየሰሩ ፕሮፖጋንዳ እየሰሩ ነው። አንዱ የ 2016 ሌላው የ 2018 ምስሎች ናቸው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
15 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-23 14:11:55
13 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-21 16:23:19 #ላስታውስሽ_29

(ነሱሀ አወል)

ሊያወራሽ የፈለገ ሁሉ ሚያወራሽ...ሊያውቅሽ የፈለገ ሁሉ የሚያውቅሽ ሰው አትሁኚ...ለነገሮችሽ ሁሉ ቦታ ምረጪ...መከበርሽን የሚያወርድ ቦታ በአካልም በቃልም አትገኚ...አንቺ የተከበርሽ ሴት ነሽ...ለፈለገሽ ሁሉ የምትገኚ..ላወራሽ ሁሉ ከንፈርሽን የምታላቅቂ አይደለሽም...እንዲያከብሩሽ ስትፈልጊ ቅድሚያ ራስሽን አክብሪው።
30 viewsGlamor, 13:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-20 20:10:20
ይሄ አይደል ሰበቡ?
....በመሀላችን እየገባ አንዳችን ለአንዳችን ምን እንደሆን ያስረሳን...ልክ ደህና አላህን ፈሪ (የተባለውን) ሰው መላውን አጥቶ ረሀብ ሲቆላው ምግብ ሰጥቶ ጌታውን የነሳው:ጀነትን በብልጭልጯ ቀይሮት እንደማለት ነው ....!

በሌላ ጎን ዱንያ ተደፍታባቸው...ቤታቸው ጨለማ የሆኑትን በብርሀን የሚሞላ...አኼራንም በማስተካከል ሂደት ጉልህ ሚና የሚጫወት ብር
ሱብሀነላህ "የበሽታው መድሀኒት ራሱ በሽታው ነው! " ሚሉት ነገር ለገንዘብ ብቻ እስኪመስለኝ አጂብ

(Glamor)
51 viewsGlamor, 17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-20 12:00:40 ኳስ የዘመናችን ጣዖት
~
ዛሬ ላይ ኳስ ከተራ መዝናኛነት አልፏል።
* በአላህ መንገድ ላይ የማይወጣው በቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር ወጭ ይወጣበታል። ሚሊዮኖች እየተራቡ፣ በክህ -ደት ሰባኪዎች እየተጠለፉ ከግለሰቦች እስከ መንግስታት ለዚህ ቆሻሻ ነገር ግን የማይገመት ወጭ ያወጣሉ።
* ዘረኝነት ይንፀባረቅበታል።
* በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ አስካሪ መጠጥ ይተዋወቅበታል።
* የጭፈራና የዘፈን ድግስ ይቀርብበታል።
* እጅግ በርካቶች ለሱ ሲሉ ግዴታ የሆነባቸውን ሶላት ያሳልፋሉ።
* እጅግ በርካቶች ለሱ ሲሉ ጎረቤት ይበጠብጣሉ፣ የወላጅ ሐቅ ይጥሳሉ፣ እርስ በርስ ይጋጫሉ፣ ለሱ ሲሉ ይወዳሉ፣ ይጠላሉ።
* የመገናኛ አውታሮች፣ ማህበራዊ ሚዲያዎች፣ ጋዜጦችና መፅሔቶች፣ ግለሰቦች፣ በቤትም በውጭም፣ በየጎዳናው፣ በየ ካፌው፣ ቆመው ተቀምጠው፣ ... ለዲንም ይሁን ለዱንያ በሚጠቅም ጉዳይ ላይ ከሚጮሁት እጅግ በላቀ ስለዚህ ርካሽ ነገር ሆኗል ውትወታቸው። እንዲያውም ቀላል የማይባሉ ጥራዝ ነጠቆች ስለ ኳስ መተንተንን የንቃት ማሳያ አድርገውታል። ስለ ኳስ አለማወቅን ፋራነት አድርገውታል። ከዚህ በላይ ምን ዝቅጠት አለ?!
* በዚህ ቆሻሻ ነገር የተነሳ እጅግ በርካታ ወጣቶቻችን ከሃዲዎችን፣ የሉጥ ህዝቦችን ተግባር የሚፈፅሙ፣ ለሱ ጥብቅና የሚቆሙ ርካሽ ፍጡሮችን እንዲያደንቁ ሆነዋል። ደካማ ሰበብ እየደረደሩ ራሳቸውን አደንዝዘዋል።
* ከዚህ ሁሉ በኋላ አንዳንዶች ጂሃድ ሊያስመስሉት ሲዳዳቸው ይታያሉ። ኳስ በዚህ በመከራ በተከበበ ህዝብ ላይ የተከፈተ ወደን የተቀበልነው ጦርነት ነው።
ይሄ ሁሉ እውነታ በገሃድ ፈጦ የሚታይ ከመሆኑ ጋር ቢያንስ ሸሩን በመቀነስ ላይ እንኳ ዱዓቶች እየሰሩ አይደለም። የዱዓት ትልቁ በሽታ ሰፊው ህዝብ የወደቀባቸውን ጉዳዮች ለመጋፈጥ ወኔ ማጣት ነው። መሬት ላይ ባለው ተጨባጭ (ዋቒዕ) መሸነፍ። አትጠራጠር ወንድሜ! ኳስ ከዘመናችን ብዙ ዓይነት ጣዖቶች ውስጥ አንዱ ጣዖት ሆኗል። አደራ! ሌላው ቢቀር ቢያንስ ለዚህ የቦዘኔዎች ስራ ብለን ሶላት ከወቅቱ የምናሳልፍ እንዳንሆን እንጠንቀቅ። ለዚህ የጂላጂሎች ስራ ብሎ መስጂዶቻችንን ማራቆት የሚያሳፍር ጉዳይ ነው። ስለዚህ ነፍሲያችንን እንርገጥ። ተቅዋን እናስቀድም።

ማሳሰቢያ፦
- ያወራሁት ስለ ኳስ እንጂ ስለ ቀጠር አይደለም።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
56 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-19 21:37:36 #የኔ እይታ 22

ከአንድ አመት በፊት አንድ ጓደኛዬ በጣም ያስጨነቃት ጉዳይ እንዳለ እና ዱአ እንዳደርግላት ደውላ ነገረችኝ።እስከዛሬ የሚገጥማትን ነገር ካወራችኝ በኋላ ስለነበር ዱአ አርጊልኝ የምትለኝ ያኔ ሀጃዋን ሳትነግረኝ ስትቀር ግራ ተጋብቼ"እና ምን እንደሆንሽ ሳትነግሪኝ ነው እንዴ?"አልኳት ለመጀመሪያ ግዜ ሀጃዋን ከኔ መደበቋ አስገርሞኝ።
"ልቤ በጣም ተሰብሯል! እራሴን ጠልቼዋለሁ። እውነት የምትወጂኝ እና የምታስቢልኝ ከሆነ እስከዛሬ ካደረግሽልኝ በተለየ ሁኔታው ከልብሽ ዱአ አድርጊልኝ!"አለችኝ እያለቀሰች
"እሺ ግን ንገሪኝ ምን እንደሆንሽ እያስጨነቅሽኝ ነው"አልኳት እምባዬ ጉንጬ ላይ እየፈሰሰ(አንድ ነፍስ ከሆንን ቆይተናል)
"አቦ አታስጨንቂኝ በቃ አላህ ጋር ተጣልቼ ነው"አለችኝ ሁሌም አላህ ጋር ያለን ግንኙነት ሲበላሽ እንደዚህ ነው የምንባባለው።
"እሺ አብሽሪ አላህ ልብሽን ይጠግነው"አልኳት አላህን ማመፅ ያለውን ህመሞ እያሰብኩ።ከነገረችኝ ቀን በኋላ ለራሴ ወንጀል ተነስቼ የማላውቀውን በተከታታይ ለይል ሰላት እየሰገድኩ በእምባ ታጥቤ አላህ ከወንጀል እንዲያፀዳት እና ነውሯን እንዲሰትርላት ለመንኩት።
ከ 3 ወር በኋላ "ዱአሽ ደርሷል ከአላህ ያጣላኝን ወንጀል ካቆምኩ ወር አለፈኝ።አሁን አላህ ፊት ቁሜ ዱአ ማድረግ አልሳቀቅም!አላህ እንደማረኝ ነው የሚሰማኝ" አለችኝ።
"አላህ ባንቺ ልመና ምክንያት ነው የማርኳት ያለኝ ይመስል በደስታ ሰከርኩ።
ከአንድ ወር በኋላ መስጂድ ቀጥራኝ......የፍርሀት በሚመስል ድምፅ" ምን እንደምልሽ አላውቅም ግን ያንን ወንጀል በምሰራበት ሰአት አላህ ጋር ለካ ቅርብ ሁኜ ነበር። አሁን ከወንጀሉ ስርቅ እና እንደማረኝ ሳስብ አላህ ጋር የነበረኝ ጥብቅ ግንኙነት ጠፋ። እሰግዳለሁ፣ቁርአን አነባለሁ፣ ዱአ አደርጋለሁ...ግን ያኔ ማረኝ፣ነውሬን ሸሽግልኝ፣ከዚህ ወንጀል አውጣኝ እያልኩ በእምባ ታጥቤ ስለምነው ምንም እንኳን በወንጀል ብበሰብስም ከወንጀሌ ተፀፅቼ የማነባት የእንባ ጠብታ አላህ ጋር ታቃርበኝ ነበር"
"እና ወደ ወንጀሎ መልሳት ብዬ ደግሞ ለይል ሰላት ልስገድ?"አልኳት ብስጭት ብዬ
"አላውቅም ግን አላህን ከወንጀል አርቀኝ እያልኩ ያለቀስኩባቸው አመታት በጣም ደስ ይሉ ነበር። የአመታት ዱአዬ ውጤት አላህ ጋር የነበረኝን ቅርበት ያሳጣኝ መሰለኝ!"ስትለኝ ግራ ተጋብቼ "ሰው እንዴት ከወንጀል ከነፃባቸው ግዚያቶች ይልቅ ወንጀል ውስጥ የነበረበት ግዜ አላህ ጋር የተሻለ ሊሆንለት ይችላል?"አልኳት በመገረም
"አየሽ ላንቺ ዱአ አድርጊልኝ ብዬ የነገርኩሽ ለአመታት ብቻዬን እያለቀስኩ አላህን መሀርታ ከጠየቅኩ በኋላ ነው። ከነበርኩበት ወንጀል መውጣት ከብዶኝ ላንቺ ከነገርኩሽ ከትንሽ ግዜ በኋላ የአመታት ልመናዬ እና ያንቺ ዱአ ተጨምሮ ነው መሰል ከነበርኩበት ወንጀል ተላቀቅኩ። ከዛ በኋላ አላህን እያለቀሱ መለመን፣ በወንጀል ስብር ብሎ ከአለማት ጌታ ፊት በሀፍረት መቆም ሳቆም ልቤ ደነዘዘ። ከሰወች ሁሉ ወንጀኛ እንደሆንኩ እንዲሰማኝ ያረገኝ የነበረው ወንጀል ከኔ ሲርቅ እራሴን እንደ ጥሩ የአላህ ባሪያ እያሰብኩ ከተውበት እና ቅጣቱን ፈርቶ ከማልቀስ ተዘናጋሁ። ወደነበርኩበት ወንጀል መመለስ ባልፈልግም ያኔ ተሰብሮ ከጌታው ደጅ የማይጠፋውን ለተውበት የተገራ ልቤን ማጣቴ ግን በጣም አሳዝኖኛል" አለችኝ። ምን እንደምላት ግራ ገብቶኝ ዝም አልኩ።

ከወዱዱ ጌታ ከአንተ ለመቃረብ፣
በማያልቅ ፍቅርህ ዘላለም ለመኖር፣
ልክ እንደ መላዕክት አንተን አለማመፅ፣
ልክ እንደ አቢዶች ለይሉን ሀይ ማድረግ
ብቸኛው ጦሪቃ ይመስለኝ ነበረ።
ዛሬ ነው የገባኝ፤ ድንበርህን አልፎ፣
በወንጀል በስብሶ፣ ሰላም ከሞላበት
ከመስጂዱ ወለል በአፉ ተደፍቶ፣
ወንጀሌ ከበደኝ፣አንተን ማመፅ በቃኝ!
ነውሬን ሸሽግልኝ፣ ለሰው አታጋልጠኝ!
ብሎ ከአንጀት ማልቀስ፣በፀፀት መገረፍ፤
ወደ አንተ እንደሚያቀርብ፣ሰደቃ እንደመስጠት፤

ይሄ ስሜት ተሰምቷችሁ የምታውቁ ትኖሩ ይሆን?

rehima Hussein
34 viewsGlamor, 18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-19 14:53:17 እንባችንን ዉጠን፣ ዉጠን የት አደረስነዉ ...? በእለት እየፈላ ሁለመናችንን የገሻሸረዉ እሱስ ቢሆን...⁈
49 viewsGlamor, 11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-18 06:49:30
​​ለሰዎች ደግ ስትሆን እንደወንዝ ሁን

#ወንዝ መርጦ አያጠጣም። አጎንብሶ ሊጠጣ ለወደደ ሁሉ ሳይሰስት ያጠጣል። ደግነታችን እንደወንዝ ይሁን ሳንመርጥ ለለመነን ሁሉ እጃችንን እንዘርጋ ።

ወንዝ ወደፊት ብቻ የሚሄድ ወደኋላ የማይመለስ ሲሆን ቀጣይነቱን ይመሰክራል የኛም ደግነት እንዲሁ ዛሬ ተጀምሮ ነገ የማያበቃ ሁል ጊዜ እንደወንዝ የሚፈስ መልካምነት በጎነት ይኑርህ።

ሌላው የወንዝ ውበቱ ዝቅ ብሎ ሳይጮህ መፍሰሱ ነው። ዝቅ ብሎ ሌሎችን ከፍ እንደማድረግ ምን ውብ ነገር አለ? ይህንን አደረግኩኝ፤ እንዲህ ደግ ሰራው እያሉ መጮህ የደግነትን ክብር ይነካል እንደወንዝ በዝምታ ለሌሎች መልካም መሆን ነው እውነተኛው ደግነት ነው፡፡

ለሃሳብ አስታያየት @bilugolden
17 viewsibnu rebah, 03:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-17 00:07:37 አደገኛ !!

አንድ ስለ ራሱ ዝቅተኛ አመለካከት ያለው ሥራ አስኪያጅ የደረጃ
ዕድገት አግኝቶ ወደሌላ የተሻለ ቢሮ ቢዛወርም አዲሱን ቢሮውን ሊላመደው
አልቻለም፡፡ ቢሮው ተቀምጦ ሳለ በሩ ተንኳኳ፡ ይህን ጊዜ በሥራ
የተጠመደ ለመምሰል ስልኩን አንስቶ መቀበጣጠር ጀመረ፡፡ የእንግዳውን
መቆም ምንም ሳይመስለውም የስልኩን እጄታ ከጆሮው እንደለጠፈ
ሲል ቆየና በመጨረሻ
በተደጋጋሚ “ምንም ችግር የለም! በአኔ ይተማመኑ”
“ደህና ይሁኑ!” በማለት የስንብት ቃል አሰምቶ ስልኩን ከዘጋ በኋላ
እንግዳውን “ምን ልታዘዝ?” አለው፡ እንግዳውም “እኔ እንኳን የመጣሁት
ስልኩን ለመስራት ነው” ብሎት ቀጥታ ወደ ስራው ገባ፡፡
ከዚህ ምን እንማራለን? ማስመሰሉ ለምን አስፈለገ? ምን ለማሳየት
ወይም ምን ለማግኘት ብለን ነው እንዲህ የምንሆነው? መዋሸት ምን
ይጠቅመናል? በሀሰት ጠቃሚ ሰው ብንመስል ምን እናተርፋለን? ሁሉም
እንደዚህ ዓይነት ስሜቶች የሚመነጩት ራስን ዝቅ አድርጐ ከመመልከት ነው ።

መጽሐፍ


በፍጹም ራስህን ዝቅ አድርገህ እንዳትመለከት !! በፍጹም !!
45 viewsGlamor, 21:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ