Get Mystery Box with random crypto!

Bilal Media & Communication

የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication B
የቴሌግራም ቻናል አርማ linkbi7 — Bilal Media & Communication
የሰርጥ አድራሻ: @linkbi7
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2022-11-10 06:06:44 "ሞት አስፈሪ እጆቹን ሲጭን ሁሉም ነገር ለዛውን ያጣል"
Muawiya
33 viewsGlamor, 03:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-09 23:22:50 #አንድ_አንድ_ወንዶች...
እንደ ሙዝ ልስልስ ብላቹ ገብታቹ ቺኮቹን ስክስ ታደርጉና ቅምስ አድርጋቹ እብስ የምትሏትን ነገር እረፉ...

#አንድ_አንድ_ሴቶች...
መጀመሪያ ላይ ፉክስ ብጥስጥስ ትሉና የኋላ የኋላ ዳቦውን ፍርክስ አድርጋቹ ወንዱ ቁርስ አድርጎ እብስ ሲል እልቅስ የምትሏትን ነገር ተውት
37 viewsGlamor, 20:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-09 19:09:03 የሴቶችን ድንግልና የሚወስደው ማን ነው?
ይህን ፅሁፍ ለማዘጋጀት ያነሳሳኝ አብዛኛውን ጊዜ አንዳንድ ወደ እስልምና እንጣራለን የሚሉ ሰዎች ህግጋቱን ሁሉ ሴቶች ላይ ጫን አድርገው ወንዶችን ብዙም ሲሉ አይሰማም፡፡
ሰሞኑን አላዋቂዎች ብዙ ሲሳለቁ እና እራሳቸውንም መግለጫ ሰጪ አድርገው ሲያዩ ተመልክተናል፡፡ የሴት ልጅ ድንግልና በብዙ መንገድ ይሄዳል፡፡ ለምሳሌ ሴት ልጆችን በገዛ የቅርብ ቤተሰቦቻቸው እና ዘመዶቻቸው በመደፈር ሁሉ ያጡታል፡፡ ሴት ልጆች ሲደፈሩ ያውም ደፋሪያቸው እየታወቀ “በቃ ዝም በይ” አይነት ማስጠንቀቂያዎች ይሰጧታል፡፡ ድንግልና ያለ ግንኙነትም ሊጠፋ የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ ዑለማዎችም ሀኪሞችም ይገልፃሉ። ስለዚህ ድንግልና የሌላት ሁሉ ብልግና ፈፅማለች ማለት ዝቅ ሲል አላዋቂነት ከፍ ሲል ብልግና ነው። በሌሎችም መንገዶች ድንግልና ይሄዳል፡፡
አብዛኛዎቹ ሴቶች ልጅ በነበሩበት ሰኣት በጣም አይን አፋር እና ድንጉጥ ናቸው፡፡ ወንድን መቅረብ አይፈልጉም፡፡ ሴቶቹን ወደ መጥፎ ነገር የሚመሩዋቸው መጥፎ ሴት ጓደኞች እና ምላሳም ወንዶች ናቸው፡፡
መቼም ወንድ ከሌለ ሴቶች በራሳቸው ድንግልናቸውን አጠፉት አይባልም፡፡ አንድ ሴት ልጅ ድንግልናዋን ስታጣ እሷን ብቻ ከመውቀስ በምላሱ አታሎ፣ አጭበርብሮ ድንግልናዋን የወሰደባትን ለምን በደንብ አይኮንኑትም?
አስገራሚው ሴት ልጅ ስትሰራ ከነበረችው መጥፎ ነገር ቶብታለች ሲባል “እሷ እኮ…. ነበረች…. መጠንቀቅ ነው …. ምን ይታወቃል” እና የመሳሰለውን ትንኮሳዎች ይተበተባሉ፡፡
ወንድ ልጅ ግን ለምሳሌ አንዴ በድፍረት 21 ወይንም 22 አመት የሚጠጋው ወንድ ለጓደኞቹ “ከ180 እስከ 200 ሴቶች ጋር ግንኙነት ፈፅሚያለሁ” እንዳላቸው ሲናገሩ ሰምቻለሁ (የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የእኔ ኡመቶች ወንጀል ይማራል ግልፅ የሚያወጣው ሲቀር ብለዋል፡፡ ወንጀልን እንደቁም ነገር እና ጀብዱ የምታወሩ ሰዎች አላህን ፍሩ)፡፡ ለምሳሌ ይህን ሁሉ ሴት የነካካ ወንድ ቶብቷል ቢባል “አቤት እሱ እኮ ሷሊህ ነው፡፡ አቤት አኽላቁ፡፡ አቤት እሱን ያገኘች” ተብሎ ይለፈፋል፡፡
ለምን?
አላህ በተከበረው ቁርኣን ላይ
- ዝሙትን በተመለከት ተከልከሉ ሲል ለወንዱም ለሴቱም ነው፡፡
- ዝሙት ከፈፀሙ ያላገቡ ከሆኑ 100 ጅራፉ ይገረፉ ሲል ወንዱንም ሴቷንም ነው፡፡
- ዝሙትን የፈፀሙት ያገቡ ከሆነ በድንጋይ ተቀጥቅጠው ይገደሉ ሲል ወንድንም ሴትንም ነው፡፡
ታድያ ለምን ይሄን ያህል ሁለቱንም የሚመለከተውን ህግ ሴቶች ላይ ብቻ ጫን ማለት አስፈለገ፡፡ እንጨት ለምሳሌ በራሱ አይቀጣጠልም እሳት ሲቀላቀልበት ቢሆን እንጂ፡፡ ስለዚህ ወንድ እና ሴት በፈፀሙት ወንጀል አንዱን ብቻ ጠንከር አድርጎ መውቀሱ በተለይ ከኢስላም ውጭ ያሉ ሰዎች “ኢስላም ሴትን ይበድላል” እንዲሉ የሚያደርጋቸው ይህ ነው፡፡
ፍትሀዊ የሆነ ሀይማኖት ይዘን ፍትህ የሌለ አስመስለን አናቅርበው፡፡ ያለ እውቀት መናገር ሁሌም ጣጣው ከሚታሰበው በላይ ነው፡፡
የቶበቱ ሰዎችን አስመልክቶ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ወደ አላህ የተመለሰ ወንጀል እንደሌለበት ነው፡፡” ብለው ሲያበቁ ወደ አላህ የተመለሱ ሰዎችን እያጣጣሉ መናገር መሀይምነትን በይፋ የሚያሳይ ነው፡፡
አስገራሚው ግልፅ ቢድኣና ሺርክን የሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ የሌላቸውን ጥንካሪ እና ድፍረት ወንጀል ላይ የወደቁት ላይ ሲያደርጉት እንመለከታለን፡፡
ወንጀል በድብቅ የሰራ ሰው አይቡ ይደበቅለታል፡፡ ቢድኣን እና ሺርክን በአደባባይ የሚፈፅም ደግሞ በአደባባይ ሙስሊሞች እንዲጠነቀቁት መልስ ይሰጥበታል ይህ ነው ፍትህ እና ሚዛናዊነት፡፡
ዛሬ የቢድኣ ካዝና ለሆኖ ሰዎች ጥብቅና ቆመው እነሱን አናስነካም፡፡ እነሱን የነካ “አይባቸውን እንዳወጣ ነው” ሲሉ ይቆዩና ተደብቀው ወንጀል የሚሰሩ ሰዎችን “ተከታትለን በካሜራ እናጋልጣለን” ብለው ስሜት አምላኪነታቸውን ያሳዩናል፡፡
እንዲህ አይነት መሀይማን ጉዳታቸው እጅጉን የከፋ ነው፡፡

ፅሁፌን ስጨርስ ሴቶችን እንደነ መርየም ድንግልናችሁን ጠብቁ ስንል፣ ወንዶችንም ልክ እንደነ ኡስማን ኢብን አፋን ሁኑ ከዝሙት ራቁ፡፡ ወንድ እና ሴቶች ሆይ! አላህን ፈርታችሁ ቶሎ ተጋቡ፡፡ በኢስላም ትዳር ትልቅ ቦታ አለው፡፡ ከትዳር ያለ አስገዳጅ ሀጃ በመዘግየታችሁ ምንም የምትጨምሩት ነገር የለም፡፡ የምታጡት ነገር ቢብስ እንጂ፡፡
ስለ ትዳር የበሰሉ ሃያእ ያላቸውን ታላቆችን አማክሩ፡፡

ፀሀፊ ሳዳት ከማል
19 viewsGlamor, 16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-07 19:53:39 #ሀጃጅ #ኢብን #ዩሱፍ አስ-ሰቀፊ ይባላል ጨካኝ የሆነ የጦር አዛዥ
ነበር።ሰዎችን መግደል እንደልብ ይወዳል።
#አንድ #ቀን 3 ሰዎችን አስፈልጎ ካሳሰረ በኋላ በማግስቱ እንዲገደሉ
ወሰኖ መገደያ ቦታው ላይም እራሱ ተገኘ።

ሶስቱም ተንበርክከው የመጨረሻ ትንፋሾቻቸውን በእንባ
እየተሰናበቱ የአንገታቸውን ቆራጭ በፍርሀት ይጠብቃሉ።
ወታደሩም የአዛዡን ትእዛዝ ለመፈፀም ሰይፉን ይዞ አንዲት ቃል
ብቻ በመጠባበቅ ላይ ነው።
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ የሀጃጅ ኢብን ዩሱፍ አስ-ሰቀፊ አይን
አንዲት በምያሳዝን ሁኔታ የምታለቅስ እንስት ላይ አረፈ።
#እዛው #ቁጭ #ባለበት፦"ያችን ሴት አምጧት" ብሎ አዘዘ።
#አጠገቡ #ሲያመጧት፦"ምንድነው እንዲህ ሚያስለቅስሽ" ብሎ
ጠየቃት።
#እሷም፦"አንገቶቻቸው እንዲቆረጥ ያዘዝከው አንዱ ወንድሜ
፣ሌለኛው ልጄ እና የባለቤቴ ሞት አሳዝኖኝ ነው" አለችው።
ለሷ ብሎ አንዳቸውን ሊተውላት አሰበ'ና፦
"ከሶስቱ አንዱን
ምረጪና ውሰጂ ሌላው ይገደላል" አላት።
#ልጇን #ትመርጠላች ብሎ ገምቶም ነበር...
ቦታው በዝምታ ተዋጠ አይኖች ሁሉ እሷ ላይ አረፉ።
ማንን መምረጥ እንዳለባት ለራሷ ፈተና ሆነባት።
ከረጅም ግዜ ማሰላሰል በኋላ ምርጫዋ #ወንድሟ #ላይ #አረፈ።
ሀጃጅ ኢብን ዩሱፍ አስ-ሰቀፊ በጣም በመገረም እንዴት
ወንድሟን ልትመርጥ እንደወሰነች ሲጠይቃት መልሷ ይህ ነበር፦
"ባል በምትኩ ሌላ ማግባት እችላለሁ"

"ልጅም በምትኩ ሌላ መውለድ እችላለሁ"

ነገር ግን ወንድም ምትክ የለውም" አለችው።
ይህን ሲሰማ ሀጃጅ ተደነቀባት በዚህ ንግግሯ ሶስቱም ምህረት
ተደረገላቸው።

አዎ ወንድም ምትክ የለውም የወንድምን ውድነት ወንድሙን
የተነጠቀ ያውቀዋል።
አላህ ወንድሞቻችንን አይንጠቅ
37 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-07 10:59:18 ገና ሰው ከፈጅር ሶላት እየተመለሰ 3 ትንንሽ ልጆቹን ከፊት ይዞ፣ ቦርሳዎቻቸውን ተሸክሞ እየተዋከበ ሲሄድ አየሁት። ባቅራቢያ የመንግስት ትምህርት ቤት ስለሌለ ራቅ ወዳለ ሰፈር መሄድ አለባቸው። ለዚያ ነው በማለዳ መውጣቱ። የትራንስፖርት መክፈል ስለማይችል ነው በሌሊት የሚያዋክባቸው። እያስብኩት ቤቴ ገባሁ። ብዙ ነገር መጣብኝ። ለማስተማር ያለውን ቁርጠኝነት አሰብኩ። በዚህ ዘመን አለመማር እድሜ ልክ የሚዘልቅ ትልቅ ጠንቅ ነው። በዚህ በኩል ራሱን እያንገላታ፣ አካሉ አልቆ ለልጆቹ ትልቅ ውለታ እየዋለ ነው። ልጆች ይህንን ውለታ ይረዱ ይሆን? ለዲናቸውስ ይሄን ያህል ቦታ ይሰጥ ይሆን? አላህ ያግዘው። ለታክሲ የተቸገረው ሰው ቤት ውስጥ ኑሮው እንዴት ይሆን? ሳስበው ጨነቀኝ። ከሱም የባሰ ብዙ አለ። ግን በያካባቢያችን መቸገሩን የማይናገር ችግር ክፉኛ የሚያንገላታው ስንት ሰው አለ?! የጎረቤት ሐቅ እንዳያስጠይቀን እናስብ ይሆን? ለማንኛውም ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፦
ليس المؤمنُ الذي يشبعُ وجارُه جائِعٌ إلى جنبهِ
"ጎረቤቱ ከጎኑ እየተራበ የሚጠግብ ሰው አማኝ አይደለም።" [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 5382]

ሸይኹል አልባኒይ ረሒመሁላህ በዚህ ሐዲሥ ስር እንዲህ ይላሉ፦
"ሃብታም ጎረቤት ጎረቤቶቹን እየተራቡ መተው ሐራም እንደሆነ በሐዲሡ ውስጥ ግልፅ መረጃ አለ። እናም ረሃብን የሚያስውግዱበት ያህል ሊሰጣቸው ግዴታ አለበት። ታርዘው ከሆነም እንዲሁ ሊያለብሳቸው ይገባል። ሌሎችም እነዚህን የመሳሰሉ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ እንዲሁ።" [አሶሒሐ፡ 1/230]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
43 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-06 18:58:29 አንፍረድ!
[የረጅም ግዜ ብሶት የወለደው... ]
:
ከቅርብ ግዜ ወዲህ ከሕልማቸው ተስፋን ያጡ ወጣቶች እንዲሁም ጎልማሶች ሐያታቸውን በራሳቸው ሲቋጩት እያየን ነው። (እየተለማመድነው ነገር...)

በሰው ተከቦ ሰው እንደማጣት፣ ለመራመድና ለመጠንከር በመጣጣር ውስጥ ከድባቴ (depression) ጋር መታገል እጅግ ፈታኝ ነው። ያደክማል... ለዛም ነው ደፍረው "ጌታዬ ያንተ ቀጠሮ አያሻኝም በቅቶኛል" ሲሉ እጅ የሚሰጡት.... ስታወራው ዝም የሚልህ ወዳጅህ፣ ሲርቅህ የራሱ ጉዳይ ያልከው ወንድምህ፣ በስህተቱ ምን አገባኝ የምትልለት ጓደኛህ እንደሰማይ የራቀው ተስፋውን ይበልጥ እያራቅክበት እንደሆነ ተረዳው። አንተን ችግር አይነካህም ማለት አይደለም አውቃለሁ። ግን ደሞ ያንተ ብሶት፥ ነገ ራሱን አጥፍቶ ከምትገናኘው የፀፀት ጅራፍ ይቀላልና... ረጅም እድሜህን አብሮህ በመከራና በደስታ ሲጋራህ የነበረ ወዳጅህ ሲርቅ ጠይቀው.... "ሁሌ ለምን እኔ?" የሚለውን የፉክክር ቃል ተወው...

የሚሰማው እንደሌለ ማሰብ፣ የኑሮ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች፣ የቤተሰብ ብዙ መጠበቅ፣ (ዛሬ እንደሰማነው ከሆነ) ብድር፣ በስራ ላይ ውጤታማነትን ማጣት፣ በፍቅር ግንኙነት ስኬታማ አለመሆን ና የመሳሰሉት ተደማምረው እጅን ወደአንገት ያሰድዳሉ። ከአጀል መድረስ ጋ አንነካካም፣ የሆነው ሆኖ ግን ሰበቢያው ያሳስበናል።

በየካፌው የዞራችሁ መሆናችሁ፣ ፈገገ ማለቱ አሊያም ፊቱ መውዛቱ ለደህንነቱ ማረጋገጫ አይደለም። ብቻዬን ልሁን ሲልህ እሺ ማለትህ መልካም ጓደኝነት አይሆንም። ሐጃህ ያውጣህ ማለትም የሙእሚን ባህሪ አልነበረም። ጠንካራ ነበርና የዛሬ የውስጥ ብሶቱን ጠንክሮ ያልፈዋል ማለት አይደለም። ሺህ ጓደኞች አሉት፣ የሚያወራው ሰው አያጣም ስትል በቸልታ አትለፈው። ሺህ ሰዎች ኖረውት አንድ  አዳማጭ የሌለው እልፍ ነው።

በሩሑ ላይ ጨክኖ የሔደ ሰው እዚያ ያደረሰውን ችግር ማሰብ ይቻልሐል? የኔ ያልከው፣ አውቀዋለሁ የምትለው ጓደኛህ ምን አሳር ቢገጥመው ነው እንዲህ ያደረገው? (ሐሳቡ አይኖርህም )
ችሎ ችሎ ሲያመልጥህ ... ፀፀት አይበቃህም። የሱ ጓደኛ መባልህ ሐሳቡን ካላቀለለው ወዴት ነው ጓደኝነትህ? ጓደኝነት ሰጥቶ መቀበል አይደለምና ፍርድህን ለአላህ አኑረህ ለጓደኛህ ኑረው።

ሳይረፍድ... እየሳቀ ሳያታልልህ... ድብርቱ አቅሉን ሳይወስደው...  እየፋፋ ሳያመልጥህ... ነብሱን ቁማር ሳይበላ... ፀፀት ደጃፍህ ሳይዘልቅ... ኑሮህን ሐዘን ሳይወርሰው.... ለጓደኛህ ጓደኛ ሁን!


@yeruh_weg
17 viewsGlamor, 15:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 22:11:14 ድሮ ድሮ በሩቁ ሳውቃት፣ እሷን በሆንኩ ብዬ እመኝ ነበር… የምሰማው የህይወቷ ድሎት፣ ምናል እንደሷ በኖርኩ ያስበለኝ ነበር… ነገር ግን ቀረብ ብዬ ከኛ የተደበቀውን የህይወቷን ቁምስቅል በራሴ ስሰማው… ለካ እኔ ነበርኩ በድሎት ስኖር የከረምኩት…

መድ
48 viewsGlamor, 19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 17:09:18 ይልቅ የኢኽዋን ቁንጮዎችን ከሳዑዲ መሪዎች ጋር አነፃፅራለሁ። ባለስልጣናትን ከሃይማኖት መሪዎች ጋር ማነፃፀሩ ልክ ባይሆንም የኢኽዋን የሃይማኖት ቁንጮዎች ከአንድ ብልሹ ባለስልጣን የማይሻሉ የጥመት መሪዎች ናቸው። በሃይማኖት ስም እኮ ነው ጥመታቸውን እየረጩ ያሉት!! እነዚህ የሳዑዲ ዑለማዎችን የሚያብጠለጥሉ ሳይሞቅ ፈላዎች እጅግ ሰቅጣጭ የሆኑ የቀርዷዊን ጥፋቶች በስሱ እንኳ ሲነቅፉ አይታችኋል? ፈፅሞ!
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
24 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 14:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 17:09:05 እነዚህ ናቸው ስለ ዑለማእ ክብር የሚደሰኩሩት
~
ሰሞኑን በሰዑዲ ዐረቢያ የሃሎዊን በዓል መከበሩን ተከትሎ የኢኽዋንና የአሕባሽን ጥምር ዘመቻ ስናይ ነበር። ከላይ ያያያዝኩት በዘመቻው ላይ ከፊት ረድፍ ከተሰለፉት ውስጥ ነው፡፡ ፅሑፉ በጥላቻና በድንቁርና የተለወሰ ነው። ነጥብ እየመዘዝኩ ምላሽ እሰጣለሁ፦

1- "ሳዑዲ የሚለው ስያሜ ከ1932 ጀምሮ የመጣ እንጂ ኢስላም ውስጥ የሌለ ቢድዓ እንደሆነና በነብያችን (ሰዐወ) ወቅት ስሟ ሒጃዝ እንደነበር ... " ይላል።

መልስ፦

ሀ. እንደምታዩት የሃገራትን ስያሜ ሱናና ቢድዐ እያለ ሊከፍል እየዳዳው ነው። ስለ ቢድዐ ያለው ግንዛቤ ይሄው ነው በቃ። ከአቅምህ በላይ ስለሆነ ጉዳይ ከመፈትፈት ይልቅ ቢያንስ የቢድዐን መሰረታዊ ግንዛቤ ብትለይ ይሻልህ ነበር።
ለ. "ሳዑዲ የሚለው ስያሜ ቢድዐ ነው" ሲል የቢድዐ አደጋ የሚያስጨንቀው አይመስልም? በየትኛው ቢድዐ ላይ ነው ስትዘምቱ የታያችሁት? በሺርክ የተጨማለቁ ድግሶችን አይደልንዴ በትንንሽ ነገር መለያየት የለብንም እያላችሁ የምትከላከሉት? የቀርዷዊ ዓለም አቀፍ ማህበርኮ ምክትሎቹ ሺዐና ኻሪ-ጂ ናቸው። እኮ እናንተም ስለ ቢድዐ?
ሐ. ደግሞም ሳዑዲ ማለት ለሒጃዝ የተሰጠ አቻ ስያሜ አይደለም። ከ1932 በፊትም በኋላም ሒጃዝ ሒጃዝ ነው። ሒጃዝ ከ0ረቢያ ልሳነ ምድር ውስጥ አንድ ክልል እንጂ ድፍን አካባቢውን የሚገልፅ አይደለም። ሒጃዝ በዛሬዋ ሰዑዲያ ምዕራባዊ ክፍል ያለው ግዛት ነው። ሰዑዲያ የሚለው ስያሜ ከዚህ ግዛት በብዙ እጥፍ የበዛ ነው። በሰዑድ ስም መሰየሙም በጥላቻ ስለተሞሉ እንጂ ይህን ያህል የሚያነጋግር አልነበረም። ሁሌ የምትዘምሩለት የኦቶማን ተርክ ኤምፓየር እኮ በመስራቹ ዑሥማን ጋዚ ስም ነው የተሰየመው። ለማንኛውም ስለምታወሩት ጉዳይ እንኳ ያለምንም የእውቀት እርሾ በባዶ አትፃፉ። ጥላቻ እውቀት አይሆንም።

2- "ስዑድ የአንድ አምባገነን ቤተሰብ ስም መሆኑ ልብ ይሏል" ይላል።

መልስ፦

ሀ- አዎ ይሄ ስያሜ ዛሬ ላለው ሃገር በመጠሪያነት የዋለው በመስራቹ ንጉስ ዐብዱልዐዚዝ ዘመን ነው፣ ረሒመሁላህ። ከነ ክፍተታቸው ጀግና ናቸው፣ የጀግና ቤተሰብ። ከየትኛውም ሀገርና ቡድን በተለየ ለተውሒድ፣ ለኢስላም ሰፊ ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል። ከሃገራቸው አልፈው በመላው አለም ተውሒድን ለማሰራጨት እጅግ ብዙ ገንዘብ ያፈሳሉ። ጠላት ሳይቀር ይህን ተገንዝቦ "የሳዑዲ ፔትሮ ዶላር" እያለ እያላዘነ ነው። ከመላው አለም ወጣቶችን እየተቀበሉ በዩኒቨርሲቲዎቻቸው ያስተምራሉ። ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች፣ ኢስላማዊ ጉዳዮች፣ ደዕዋና ኢርሻድ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት፣ በመልካም ማዘዝ ከመጥፎ መከልከል ባለስልጣን መስሪያ ቤት፣ የታላላቅ ዑለማዎች ምክር ቤት፣ የሐጅ እና ዑምራ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት፣ ወዘተ ለኢስላም ምን ያክል ትኩረት እንደሚሰጡ ህያው ምስክር የሆኑ በመንግስት የሚመሩ የሀይማኖት ተቋማት ናቸው። እስኪ በየት ሀገር ነው የነሱን የሚያህሉ እንዲህ አይነት ተቋማት ያሉት?
ንጉስ አልፎ ሌላ ንጉስ በተተካ ቁጥር ደስ የማይል መላላት በየዘመኑ እያየን ነው። በዚህ ነገር ውስጣችን እጅጉን ይደማል። ከመሆኑም ጋር እነሱን በማብጠልጠል ላይ የተሰማሩት የኢኽዋንና የአሕባሽ አንጃዎች ከነሱ ሊሻሉ ነው? አመድ በዱቄት ይስቃል!
ለ- በተረፈ አምባገነን ስርአት ነው ስትሉ ምንድነው የምትፈልጉት? ዲሞክረሲ የለም ልትሉ ነው? እንኳንም አልኖረ። በኢስላም መመዘኛ ዲሞክረሲ ፈፅሞ ከአምባገነን ስርአት የተሻለ አይደለም። ደግሞስ ሰርክ የምትዘምሩለት የኦቶማን አስተዳደር የለየለት አምባገነን እንደነበር ማን በነገራችሁ?

3- "የቀብር አምልኮ (ሽርክ ከመሆኑ ጋር) ላይ ብቻ የሚጮኹና ቤተ-መንግስት ውስጥ ያሉ ህያው አምባገነኖችን ቀዳሽና አወዳሽ አላህ ላይ ያለምንም ስልጣን አሻራኪ የነበሩ፣ በባለስልጣናት ዙፋን አስጠባቂ ዓሊሞችና እስር ቤት ለዓመታት እንዲማቅቁ ተደርገው የሚሞቱ ዓሊሞች መሃል ያለውን ልዩነት ማስተዋል ያሻል።"

መልስ፦

ለትናንቱም ለዛሬውም ፅሑፌ ቀዳሚው መነሻዬ ይሄን መሰል እርኩስ ውንጀላ ነው። ደጋግሜ እንደገለፅኩት የነዚህ ነውረኛ አካላት ዋናው ማጠንጠኛ የሳዑዲ ስርአት አይደለም። የሳዑዲ ዑለማዎች እንጂ። እንደምታዩት ዑለማዎቹን ነው "አምባገነኖችን ቀዳሽና አወዳሽ አላህ ላይ ያለምንም ስልጣን አሻራኪ" እያለ የሚገልፀው። በዚህ መልኩ ቆሻሻቸውን ሲደፉ እያየ "ዑለማዎቹን ማን ነካ?" የሚል እንቅ -ልፋም አለ። ከዚህ በላይ ምን ይበላቸው?! እኮ እነ ኢብኑ ባዝ፣ ዑሠይሚን፣ ፈውዛን፣ ዐባድ፣ ... ናቸው አምባገነኖችን እያመለኩ በአላህ ላይ የሚያሻርኩት?! በኢስላም ታሪክ እንደዚህ የኢኽዋን ቡድን ባለጌና ነውረኛ መንጋዎችን የሰበሰበ መኖሩን እጠራጠራለሁ።

4- "ሸሪዓ ቁረጠው ፍለጠውና ቅፍደዳ አይደለም። እንደዚያ አለመሆኑን ሐረሞቻችን ላይ የተጠመጠው ይህ ቤተሰብ ህዝቡን አፍኖ ጥቂት ነፃነት ሲሰጠው በቀጥታ እንደታየው የሸይጣን አምላኪ ባልሆነ ነበር። ከዚህ ስርዓት ይልቅ ምዕራቡ ውስጥ ያሉ ሙስሊሞች ስለ ሸሪዓ አብዝተው ይሰራሉ" ይላል።

መልስ፦

ተመልከቱ ይህንን የተሳከረ ትንታኔ! በመጀመሪያ ሃሎዊን ያከበሩት የሳዑዲን ህዝብ 1% አይሆኑም። እንዴት እነዚህን መነሻ አድርጎ ህዝብን በጅምላ "የሸይጣን አምላኪ" ብሎ ይገልፃል? ጥላቻ አውሮት እንጂ አሁን ይሄ ለህፃን የሚሰወር ጉዳይ ነው? ደግሞስ ተመሳሳይ ስሌት ተጠቅሞ የቱርክን ህዝብ "የሸይጣን አምላኪ" ብሎ ይገልፃል? እኮ ከሳዑዲ በበለጠ ምዕራቡ ውስጥ ያሉ ሙስሊሞች ስለ ሸሪዓ አብዝተው ይሰራሉ? ምን የሚሉት ፍርደ ገምድልነት ነው? በዚህ ቅጣምባሩ በጠፋው ግንዛቤህ ነው ህዝብን ከህዝብ የምትመዝነው?

5- "ተስፋ አስቆራጭና የቂያማ ነገ መሆንን ብቻ ሳይሆን እንደ ኡማ ፈሳድና ጃሂሊያን ታግሎ ልክ እንደ ኳታር የኢስላምን መርሆች ዳግም ማምጣትን ማሰብም ከአንድ ሙስሊም የሚጠበቅ የድል ተስፈኝነት ምልክት ነው" ይላል።

መልስ፦

ሀ. ሳዑዲን ያብጠለጠለው ብእር ለኳታር የሚጨፍርበትን ምክንያት እናውቀዋለን። ይሄ አስመሳይ አካሄድ ከቁንጮዎቹ የተወሰደ ድግምት ነው። እንዲህ የንፍቅና አካሄድ እየሄዱ ነው ስለ ድል የሚዘምሩት። "እናያለን" አለ እውር!
ለ. አንዳንዶች "እንዴት ሳዑዲንና እነ ቱርክና ኳታርን ታወዳድራለህ?" ብላችኋል። መቼ ስራ ፈታሁና! የማይወዳደር ነገር ላይ ምን አደከመኝ?! "እና ከሳዑዲ ለመከላከል ለምን እነሱን ትጠቅሳለህ?" ነው ሎጂካችሁ። እያወዳደርኩ ቢሆን ስለ ቱርክ አንድ መፅሐፍ እፅፍ ነበር። የማላደርገው የሚይዝ ይዞኝ ነው። እውነቱን ለመናገር ክፉም አልመኝላቸውም። ስማቸውን የምጠቅሰው ሳዑዲን ለመተቸት የሚያነሱት ጥፋት ሁሉ በነዚህ ሃገራት ውስጥ በሰፊው ከመኖሩ ጋር በሳዑዲ ዑለማዎች ላይ የሚዘምቱት የኢኽዋን መንጋዎች የነዚህ ሃገራት ቀዳሽ አወዳሽ ስለሆኑ ነው። ስለሆነም የትችታቸው እውነተኛ መነሻ ለዲን መቆርቆር ሳይሆን ቡድናዊ ጥላቻ የወለደው እንደሆነ ለማሳየት ነው የምጠቅሰው። በዚያ ላይ እያወዳደሩ ያሉት ራሳቸው ናቸው። በልጁ ፅሑፍ ላይ ራሱ ማወዳደሩን ታያላችሁ።
24 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 14:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 17:09:00
21 viewsرَاحِمَا بِنْتْ حَيْرَدِنْ☞, 14:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ