Get Mystery Box with random crypto!

የስብዕና ልህቀት

የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የሰርጥ አድራሻ: @human_intelligence
ምድቦች: መዝናኛዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 88.58K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል
⚡ህይወትን የሚያንፁ የስነ-ልቦና ምክሮች
⚡መሳጭ የፍቅር ታሪኮች እና ወጎች
⚡ጥልቅ ማህበራዊ እና ፍልስፍናዊ እይታዎች
⚡ውብ የጥበብ ስራዎች
በፅሁፍ እና በድምፅ/Audio ይቀርባሉ።
#ሼር በማድረግ ወዶጅዎን የዚህ የእውቀት እና የጥበብ ድግስ ታዳሚ እንዲሆኑ ይጋብዙ።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 14

2022-11-13 21:04:42 ግፍ አታቆዩ
አስቂኝ ወግ
በእፀገነት ከበደ

@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
2.5K viewsedited  18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-10 22:58:10
Thought for tonight

Bob Marley was once asked if there was a perfect woman. He replies :

Who cares about perfection?

Even the moon is not perfect, it is full of craters.

The sea is incredibly beautiful, but salty and dark in the depths.

The sky is always infinite, but often cloudy.

So, everything that is beautiful isn't perfect, it's special.

Therefore, every woman can be special to someone.

Stop being "perfect", but try to be free and live, doing what you love, not wanting to impress others"
ከረምሃይም ገፅ የተወሰደ

@Human_Intelligence
2.3K viewsedited  19:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-10 07:07:53 ያን  ጊዜና አሁን

ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … ማድረግ ያቅታችሁ የነበረ፣ አሁን ግን ማድረግ ወደመቻል የመጣችሁትን ቢያንስ አንድ ነገር ጥቀሱልኝ፡፡

ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … በፍጹም አያያዙ ያቅታችሁ የነበረና ሰላማችሁን ይነሳው የነበረ ሰው፣ አሁን ግን አያያዙን በሚገባ ወደማወቅ ብስለት ከማደጋችሁ የተነሳ ተረጋግታችሁና አስቸጋሪነቱን አልፋችሁ የምትሄዱትን ቢያንስ አንድ ሰው ጥቀሱልኝ፡፡

ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … መቆጣጠር ያቅታችሁ የነበረና አሁን ግን በቁጥጥር ስር እስከማድረግ የደረሳችሁትን አንድ የስሜታችሁን ሁኔታ ጥቀሱልኝ፡፡

ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … ብዙ ሞክራችሁ ማቆም ያቃታችሁንና አሁን ግን አቁማችሁት ራሳችሁን ያገኛችሁትን አንድ አጉል ልማድና ልምምድ ጥቀሱልኝ፡፡

ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … መጀመር አቅቷችሁ የተነበረና አሁን ግን ከብዙ ጥረት በኋላ የጀመራችሁትን አንድ መልካም ነገር ወይም ልምምድ ጥቀሱልኝ፡፡

ከዚህ በፊት … ያን ጊዜ … ከሰው እርዳታ ወይም አይዞህ ባይነት ውጪ መወጣት ያቅታችሁ የነበረና አሁን ግን በራሳችሁ ተነሳሽነት የምትወጡትን ሃላፊነት ጥቀሱልኝ፡፡

ከላይ ለተጠቀሱት ስድስት የእድገት ጠቋሚች ቢያንስ ለሶስቱ፣ “አዎን! አለኝ” የሚል መልስ ከሌላችሁ እድሜያችሁ በቆጠረ መጠንና ወራትና አመታት ባለፉ ቁጥር ከዚያው ጋር ሁለንተናዊ በሚባል ደረጃ የማደጋችሁ ሁኔታ አጠራጣሪ ነው፡፡ ይህንን ሁኔታ ዛሬውኑ ለመቀልበስ ካልወሰናችሁና እርምጃ ካልወሰዳችሁ ከጥቂት አመታት በኋላ ትጸጸታላችሁ፡፡

ችግራችሁን ለዩ … የማሸነፊያውን መንገድ እወቁ … የእርምጃ እቅድ አውጡ … ራሳችሁን አሳድጉ … የሚደግፋችሁ ሰው ፈልጉ … ጸሎት አድርጉ … ተንቀሳቀሱ … እደጉ … ተለወጡ!

ዶ/ር እዮብ ማሞ
2.7K viewsedited  04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-10 06:55:51 የወደፊት ሲደምቅ!

“ለወደፊቱ ራእይ የሌለው ሰው ሁል ጊዜ ወደኋላው ይመለሳል” (Kevin Gates)

ካለፈውና ካከተመለት ነገር ትምህርትን አግኝቶ ወደፊት ከመገስገስ ይልቅ እሱን እንደገና እያሰቡ የመጨናነቅ፣ የመረበሽና ተስፋ የመቁረጥ ሁኔታ የሚያጠቃችችሁ ከሆነ ምናልባት የወደፊት ራእይ ያለመኖሩ ምልክት እንዳይሆን ጠርጥሩ፡፡

የወደፊታችሁ እየፈዘዘ ከሄደና ማየት ከተሳናችሁ የኋላችሁና ያለፋችሁት ነገር መድመቅና መጉላት ይጀምራል፡፡ በሌላ አገላለጽ የአንዱ መድመቅ የሌላኛው መደብዘዝ ነው፡፡ ምርጫው ግን በእጃችሁ ነው፡፡

ያለፈ ጉዳት … ያለፈ የተሳሳተ ውሳኔ … ያለፈ ክስረት … ያለፈ ተጀምሮ የተቋረጠ ነገር … ያለፈ ጎድቶንና ትቶን የሄደ ሰው … እየተመላለሰ ስሜታችሁን ቀውስ ውስጥ የሚጨምረው ከሆነ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚቀርፍላችሁ ብቸኛ ነገር የወደፊታችሁን ራእይ ማየትና እሱ ላይ ማተኮር ነው፡፡

የወደፊት ራእያችሁ ካለፈው ታሪካችሁ ሊጠነክርና ሊደምቅ ይገባዋል፡፡

ያለፈው ታሪካችሁ ከሚሰጣችሁ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ይልቅ የወደፊታችሁ የሚሰጣችሁ የመጓጓት ስሜት ሊያይል ይገባዋል፡፡

ዶ/ር እዮብ ማሞ
2.8K views03:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-07 23:51:24 ድንበር ላይ የተረሳ ኪዳን
ገጣሚ መርዕድ ተስፋዬ

@Human_Intelligence
424 views20:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-30 14:52:03 ምላስ እና ሰበር-2
የበእውቀቱ ስዩም አስቂኝ ወግ
ከዘነጡማ እንደ ታከለ ኡማ


@Human_Intelligence
4.7K viewsedited  11:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 22:59:12 ምላስ እና ሰበር
የበእውቀቱ ስዩም አስቂኝ ወግ
የኢትዮጵያ ህዝብ እና የሴቶች ቦርሳ የማይችለው የለም!!


@Human_Intelligence
8.2K viewsedited  19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 09:04:55 ስቃይን መጋፈጥ

ምንጭ ፦ ደስታን የማግኘት ጥበብ
ትርጉም ፦ ዳኜ መላኩ

በቡድሀ ጊዜ ካይሳኦታሚ የተባለች አንዲት ምስኪን እናት አንድ ልጇን በሞት ተነጠቀችና ከባድ ሀዘን ወደቀባት፡፡ ይህቺ ምስኪን እናት የመጽናኛ ልጇ ሞት የምትቋቋመው አይነት አልነበረምና እጣ ፈንታዋን በጸጋ መቀበል ተሳናት፡፡ እናም ልጇን ከሄደበት አለም የሚመልስ መድሀኒት ፍለጋ አዋቂ፣ ጠቢብ ካለበት ስፍራ ሁሉ መዞር ጀመረች፡፡ ከአንዱ ጠቢብ ወደ ሌላው እየዞረች የሞትን መድሀኒት ስታጠያይቅ ሰዎች ወደ ቡድሀ ይመሯትና ቡድሀ ዘንድ ትቀርባለች፡፡

እንደ ባህሉ እጅ ነስታ ስታበቃም ቡድሀን ‹‹ልጄን ከሞት የሚመልስ መድሀኒት ልታገኝልኝ ትችላለህ?›› ስትል ትጠይቃለች።

ቡድሀም ምንም ሳያቅማማ ‹‹አዎን..... አንድ የማውቀው መድሀኒት አለ›› ይልና አክሎም ‹‹ሆኖም መድሀኒቱን ለመስራት የሚያስፈልገው ቅመማ ቅመም መገኘት አለበት›› ይላታል፡፡

እናቲቱ ልጇን ከሞት የሚመልስ መድሀኒት በመኖሩ እፎይ ትልና በተስፋ ‹‹ምንድን ነው የሚያስፈልገው? ምን ላምጣ?›› ስትል ትጠይቃለች።

‹‹አንድ ጭብጥ የሰናፍጭ ፍሬ ማምጣት ይኖርብሻል›› ይላታል ቡድሀ፡፡

እናትየው የሰናፍጭ ፍሬውን ካለበት ፈላልጋ እንደምታመጣ ቃል ገብታ ትነሳለች። ሆኖም ቡድሀን ተሰናብታ ልትወጣ ስትል አንድ ማስጠንቀቂያ አክሎ ይነግራታል። ‹‹ሰናፍጩን ማምጣት ያለብሽ ሞት ገብቶ ከማያውቅበት ቤት ነው፡፡ ልጁን፣ ሚስቱን፣ ወላጆቹን ወይም አገልጋዮቹን በሞት ካልተነጠቀ ሰው ቤት ነው ሰናፍጩ መምጣት ያለበት» ሲል ያስጠነቅቃታል፡፡

እናትየው በዚሁ ትስማማና የሰናፍጭ ፍሬውን ማፈላለግ ትጀምራለች። ከቤት ቤት እየዞረች ታጠያይቃለች፡፡ በየገባችበት ቤት የጠየቀቻቸውን ሰናፍጭ ለመስጠት ቢስማሙም በቤታቸው ውስጥ ሰው ሞቶባቸው እንደሆን ስትጠይቅ ሁሉም በሞት የተነጠቁትን ይነግሯታል፡፡ አንዳንዶቹ ልጃቸውን፣ አንዳንዶቹ ወላጆቻቸውን በሞት አጥተዋል፡፡ አንዳንድ ቤት ውስጥ ባል ወይም ሚስት ስትሞት ቤቶች ውስጥ ደግሞ ሰራተኛና የሴት አገልጋዮች በህይወት የሉም፡፡ እናቲቱ በየቤቱ እየገባች ብትጠይቅም ሞት ቀድሟት ያልገባበት ቤት ልታገኝ አልቻለችም፡፡

ካይሳኦቶሚ ሞት ያልደረሰበት ቤት እንደሌለ ስትረዳ፣ በርግጥ ሞት በርሷ ላይ ብቻ የወደቀ ሀዘን እንዳልሆነ ተገነዘበች፡ ሁሉም ሰው የሚወደውን አጥቷል። ሞት በሁሉም ላይ የሚደርስ የህይወት እጣ ፈንታ ነው፡፡ ይህን በማየት ካይሳኦቶሚ የልጇን ህይወት አልባ አካል ይሁን ብላ ተቀብላ ወደ ቡድሀ ተመለሰች፡፡ ቡድሀም በታላቅ ርህራሄ እንዲህ ሲል አጽናናት

‹‹ልጅሽን በሞት ያጣሽው አንቺ ብቻ አይደለሽም፡፡ የሞት ህግጋት በምድራዊ ፍጡራን ላይ ሁሉ የተጣለ ነውና ከቶውኑ ቋሚ የሆነ የለም።"

«የእናቲቱ ጉዞ በርግጥ ከምድራዊው ሀዘንና ስቃይ ነጻ የሆነ ሰብአዊ ፍጡር እንደሌለ የሚያመላክት ንግርት ነው፡፡ ይህን እውነታ መገንዘብ ውስጣዊ መረጋጋትን የሚያሰርጽ ታላቅ ሀይል አለው። ስቃይ የሁሉም ሰው እጣ ፈንታ መሆኑን ማወቅ ብቻውን ሀዘንና ህመማችንን ባያስወግደውም ይህንን ተፈጥራዊ እውነታ መቀበል ችግርና ህመምን በመታገል የምናተርፈውን ተጨማሪ ስቃይ ይቀንሳል።

"ህመምና ስቃይ በሁሉም ላይ የሚደርስ የህይወት ገጽታ ቢሆንም ምንም ጉዳት እንዳልደረሰብን ሁሉ በቀላሉ ልንቀበለው እንችላለን ማለት አይደለም። አሳዛኝ የህይወት ዱብዳዎችን ማስተናገድ በእጅጉ ከባድ ነው። ይህ በመሆኑም ሰዎች ስቃያቸውን ለማምለጥ የሚረዱ የተለያዩ ዘዴዎችን ፈብርከዋል። አንዳንድ ጊዜ ስሜትና አስተሳሰባችንን የሚያደነዝዙ መድህኒቶችን በመጠቀም ከስቃያችን እፎይ ለማለት እንሞክራለን። አንዳንዴም የህይወት እውነታዎቻችንን የሚያስረሱ አልኮልና አደንዛዥ እጾችን በመጠቀም ከችግራችንም ከራሳችንም ለማምለጥ እንማስናለን። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ከስሜታዊ ስብራቶቻችን ለመሸሽ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ውስጣዊ የሆነውን ስነ ልቦናዊ ትግል እናካሂዳለን፡፡ አንዳንዴም ችግራችንን በመካድ ስቃዩን ላለመጋፈጥ ስሜታችንን በውስጣችን እናዳፍናለን፡፡ ወይንም ችግሩ መኖሩንን እናምንና ህመሙን ላለማሰብ አእምሯችንን ጎጂና ትርጉም አልባ በሆኑ ጉዳዮች እንጠምዳለን፡፡ ብዙዎቻችን ደግሞ ችግራችንን ላለመቀበል ጥፋታችንን በሌሎች ላይ አላከን ሰዎችን እንወቅሳለን፡፡››

‹‹ስቃይ ተፈጥሯዊ እውነታ ነው፡፡ ለጊዜው ልናስታግሰው ብንችልም ለዘላለሙ ልናስወግደው አንችልም፡፡ ፈውስ እንዳላገኘ ቁስል ውስጥ ለውስጥ እየመረቀዘ በየጊዜው እዥ ያነባል፡፡ በየጊዜው የሚሰጠው መድሀኒት ውጪውን ቢያደርቀውም ውስጡ መግል እንደቋጠረ ይቀራል።

«ምናልባት ስቃይን በአልኮልና በአደንዛዥ እጽ ለጊዜው መሸሽ ይቻል ይሆናል፡፡ ሆኖም በዚህ የማያቋርጥ የሽሽት ሂደት የሚፈጠረው ግላዊና ማህበራዊ ጉዳት ወደ አልኮል ከመራን ስቃይ የባሰ ህመምና ችግር ይፈጥራል፡፡ ስቃያችንን ላለመቀበልና ለማዳፈን በውስጣችን የምናካሂደው ስነ ልቦናዊ ትግል ህመማችንን በጥቂቱ ሊያስረሳን ቢችልም ችግሩ ሳይፈታ ተቀምጦ ይቀራል፡፡

ስቃይ ከሰው ልጅ ህልውና ሊወገድ የማይችል ተፈጥሯዊ ገጽታ መሆኑን በመግለጽ ቢጀምሩም፣ አቀራረባቸው ከዚህ ስቃይ ነጻ መውጣት የምንችልበት መንገድ እንዳለ የሚጠቁም ነበር፡፡ ሆኖም በዳላይ ላማው እምነት ሁሉም ነገር እውነታውን ተቀብሎ ከመጋፈጥ ይጀምራል፡፡

‹‹በእለት ተእለት ህይወታችን ውስጥ ችግሮች መከሰታቸው የማይቀር ነው፡፡ በማንኛውም ሰው ህይወት ውስጥ ከሚከሰቱ ሊወገዱ የማይችሉ ችግሮች ውስጥ በዋነኝነት የሚጠቀሱት እርጅና፣ ህመምና ሞት ናቸው ስለነዚህ ችግሮች አለማሰብ ችግሮቹን በማስረሳት ጊዜያዊ እፎይታ ሊሰጠን ቢችልም ችግሮቹን ከመሸሽና ከመራቅ ይልቅ ፊት ለፊት መጋፈጡ የችግሮቹን ጥልቀትና የሚያስከትሉብንን ጉዳት በትክክል ለመገንዘብ ያስችላል፡፡

‹‹በጦርነት ውስጥ ስለ ጠላትህ ትጥቅና የውጊያ ስልት ትኩረት ላለመስጠት ብትሞክር ተገቢውን ዝግጁነት ከማጣትም ባሻገር በፍርሀት ትታሰራለህ፡፡ ሆኖም የጠላትህን አቋም፣ ትጥቅና የውጊያ ብቃት ጠለቅ ብለህ ብትመረምር በተሻለ ዝግጅትና ቁርጠኝነት ውጊያውን ትጀምራለህ፡፡ ስለ ጦርነት በቂ እውቀት የሌለው፣ ሽጎጥና ቦምብ አይቶ የማያውቅ ወታደር እራሱን በበቂ ሁኔታ ሳያዘጋጅ ለጦርነት ቢሰለፍ ምናልባት ገና ሳይመታ በድንጋጤ እራሱን ሊስት ይችላል፡፡ ሆኖም የሚገጥመውን ሁኔታ አስቀድሞ ሲያስብበት ከሁኔታው ጋር አብሮ ለመሄድ ይቀለዋል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ችግሮችህን ከመርሳት ይልቅ ፊት ለፊት ለመመልከት ብትሞክር ችግርህን በተሻለ መልኩ የመፍታትና የማስተናገድ እድል ይኖርሀል፡፡››

@Zephilosophy
@Zephilosophy
10.8K views06:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 20:46:23 ያልተፈተሹ ባህሪያት

“ትዕግስት ስጠኝ ብለን ስንጠይቅ፤ የሚሰጠን እረጅም ሰልፍ ነው” ትላለች ጸሀፊ ትሬሲ ማክሚላን። ትዕግስትን ስንጠይቅ የሚሰጠን ትዕግስትን የምንለማመድበት መድረክና ትዕግስትን የምናዳብርባቸው ሁኔታዎች እንጂ ትዕግስት ልክ እንደተሰጥዎ ከላይ አይቸረንም። ለዛሬ ጽሁፌ መነሻ የሆነኝ ሀሳብ እንደሚከተለው ነው።

አንዳንዴ እራሳችንን ባላሰብነው ሁኔታ ውስጥ እናገኘውና ከራሳችን የማንጠብቀው ባህሪ ሲንጸባረቅብን እንደነግጣለን። ለወትሮ እኮ እንዲህ አልነበርኩም በማለት ግራ ይገባናል። ተሳድበን የማናውቅ ሰዎች በሆነ አጋጣሚ ሌላውን ሰው ስናጥረገርገው፤ ትዕግስተኛ ነን ብለን የምናስብ ሰዎች ቀጠሮዋችን እረፈደ ብለን የታክሲውን ሹፌር ስናመናጨቀው፤ ቂመኛ አይደለሁም ስንል የከረምን ሰዎች የወደድነው ሲከዳን ለበቀል ስናደባ፤ በደላችንን ይቅር በለን እያልን ጠዋት ማታ እየጸለይን የበደሉንን ሰዎች ይቅር ማለት ሲከብደን፤የሌሎች ሰዎች ማግኘት ያስደስተናል የምንል ሰዎች እኛ የተመኘነውን ሌላው ሰው ላይ ስናየውና ሲከፋን፤ ፈራጅ አይደለንም ስንል ከርመን የእኛ ህልውና ሲነካ የፍርድ ወንበር ላይ ቁጢጥ ስንል፤ ባህሪያችን ለገዛ እራሳችን እጅግ ግራ ያጋባል።

ማንነታችን የሚገለጸው እኛ ስለራሳችን ባለን አመለካከት ወይም ሌሎች ሰዎች ስለኛ ባላቸው አመለካከት ሳይሆን፤ እኛ ለሁኔታዎች በምንሰጠው ምላሽ ነው። ሰው እንቃለው የሚል ሰው ባያጋጥምም ፤ ሰው እጠላለሁ የሚል ሰው ስምተን ባናውቅም ሰው የሚንንቅና የምንጠላ ሰዎች ግን አንጠፋም። ከእኔ ከእራሴ ጭምር በውስጣችን መጥፎ ስሜት ያድራል ብለን ማሰቡ ይከብደናል፤ ይከብደናል ብቻም ሳይሆን ለማሰብም አንፈልግም። እውነታው ግን ከዚህ የተለየ ነው። “እኔ” ብለን የምንጠራው ማንነት በአብዛኛው የተገነባው ባልተፈተሹ ባህሪያቶቻችን ነው። ስለራሳችን ስናወራ በአብዛኛው የምናወራው በሀሳብ ስለገነባነው ማንነት እንጂ፤ በተግባር ስለምነተገብረው ባህሪዎቻችን አይደለም።

እኔ እንዲህ ነኝ ብሎ በድፍረት መናገሩ ከባድ የሚሆነውም ለዚህ ነው፤ ሁላችንም ያልተፈተኑ ባህሪያቶችን አጭቀን ስለምንቀሳቀስ። አብዛኛው ባህሪያቶቻችንና አስተሳሰቦቻችን በቲዎሪ ደረጃ እንጂ በሙከራ የተረጋገጡ አይደሉም። መልካምነታችን፤ ትዕግስተኛነታችን፤ ፍትሃዊነታችን፤ ሰው አክባሪነታችን፤ እውነተኛነታችን ተገቢውን ፈተና አላለፉም። ፈተና ስል እውነተኛ ባህሪዎቻችንን እንድናጸባርቅ የሚያስገድዱን ሁኔታዎችን ነው። ጊዜ ስለተረፈን ከኋላችን ያለውን ተሰላፊ ከፊታችን ስላስቀደምነው ትዕግስተኛ ልንባል እንችላለን? በፍጹም!!! የማንኛችንም መልካምነትና ጥንካሬ በመልካም አጋጣሚዎች ሊረጋገጥልን አይችልም። በፈተናዎችና በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ የምናሳያቸው ባህሪያቶች ይበልጥ እኛን ይገልጹናል።

ለዚህ ነው አንዳንዴ ውሳኔዎቻችንና ድርጊቶቻችን የሚያስደነግጡን። ተፈትነን ያገኘናቸው ባህሪዋቻችን ስላልሆኑ ልንጠቀምባቸው በሚገባን ቦታ ይጠፉብናል። ይህንን ማወቁ ምን ይጠቅምናል? ለሁለት ነገር ይጠቅመናል ብዬ አስባለው። አንደኛው ከውሸተኛ ማንነት ቀስ እያለ ያላቅቀናል፤ ሙሉ በሙሉ መላቀቅ ለሰው ልጅ ቢከብድም። የሚሰማንን ስሜት በካድን ቁጥርና “እኔ እኮ እንዲህ አይደለሁም” በማለት እራሳችንን በተከላከልን ቁጥር ባህሪያችንን ማሻሻል አስቸጋሪ ይሆንብናል። ከእራሳችን ጋር እየተቆራረጥን በቅዠት አለም ውስጥ መኖሩን እንለምደዋለን።በሌላ በኩል ማንነትና ባህሪያችንን ለሁኔታዎች ከምንሰጠው ምላሽ ተነስተን መዳኘት ከቻልን፤ ከእውነተኛ ምንነታችን ጋር እንቀራረባለን። የትኛው ባህሪያችን ላይ ይበልጥ ማሻሻል እንዳለብን ግልጽ ይሆንልናል። ስለራሳችን ባህሪ እርግጠኛ ሆኖ መናገሩ የሚያስከፍለው ዋጋ አለ፤ እሱም ወደ እውነት የሚወስደውን ጎዳና ያጠብብናል።እውንተኛ ማንነታችንን ለማወቅ ከፈለግን ስለራሳችን የምናስበውን ሳይሆን፤ ለሁኔታዎችና ለአጋጣሚዎች የምንሰጠውን ምላሽ ልናስተውል ግድ ይለናል። ሁለተኛው ጥቅም “እኔ ብሆን ኖሮ” በሚለው የፍርድ ዱላ እርስ በራሳችን ከመፈነካከት ያድነናል።

“ የሰው ባህሪያት በሁኔታዎችና በአጋጣሚዎች አይፈጠርም፤ በሁኔታዎችና በአጋጣሚዎች ይጋለጣል እንጂ”- ዚግ ዚግለር


@Human_Intelligence
15.8K viewsedited  17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-15 18:29:31 አይዞህ ልቤ

ድንገት ቢከፋ ባይቀና ኑሮ በዚች አለም
ጊዜ የማይፈታው ምንም የለም

ጊዜም አሁን ነው ትላንት ሆኖ ቀሪ
የነገን ቀን ሰሪ

አመት ያህላል ቀን እየዞረ
ዛሬም እራሱ ነገ ነበረ
የጊዜ ሚዛን አይላወስም
#ዛሬን የሌለ ለነገ አይደርስም

ሳዝን አልውልም ሳላቅ ማደሬን
የኔነው በቃ አልሰጥም #ዛሬን

#share
@Human_Intelligence
15.3K views15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ