Get Mystery Box with random crypto!

የኤፍሬም እይታዎች (መ/ር)

የቴሌግራም ቻናል አርማ ephremvi — የኤፍሬም እይታዎች (መ/ር)
የቴሌግራም ቻናል አርማ ephremvi — የኤፍሬም እይታዎች (መ/ር)
የሰርጥ አድራሻ: @ephremvi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.42K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ የቴሌግራም ገጽ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማ፣ቀኖና እና ትውፊትን የጠበቁ ስርዓተ አምልኮና ትምሕርቶች እንዲሁም ዝማሬዎች ይቀርቡበታል። ክርስቲያናዊ የሆኑ ማህበራዊ ጉዳዮችም ይነሱበታል።
" ያየሁትን እናገራለሁ የሰማሁትን እመሰክራለሁ! "

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-02-25 21:03:24 " አድዋና መንግሥት አድዋና ሕዝብ "
_________
#የአድዋ_በዓል_ትዝብቴ!

እንደ ሀገር ከአድዋ የገዘፈ፤እንደ ዓለምም አስደናቂ የሆነ ከአድዋ የላቀ ብሔራዊ በዓል የለንም።

የአድዋ ድል የዓለም የጭቁን ሕዝቦች ሁሉ ድል ነው።የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ክብር ማኅተም፤ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተጋድሎ ቀንዲል ነው፡፡ የአድዋ ድል የመላው ዓለም ተፈጥሮአዊ ግብር እና ሰብአዊ ክብር የታደሠበት፤ በእውነትና በፍትህ ለነጻነትና ለህልውና አጥንት ተከስክሶ ደም ፈሶ ህያው ደማቅ አኩሪ ታሪክ የተጻፈት፤ በአድዋ ታላቅ ህዝቦች በኢትዮጵያ ጀግኖች ታሪክ የተሰራበት ታላቅ ድል ነው።አድዋ የመላው የጥቁር ሕዝብ ድል ነው፡፡

የአድዋ በዓል በሀገር አቀፍ ደረጃ ብቻ ሳይወሰን የአፍሪካውያን ሁሉ በዓል፤በዓለም ያሉ የጭቁን ሕዝቦች ሁሉ የነጻነታቸው ፋና ወጊ በዓል ተደርጎ መከበር የሚገባው ነው።አድዋ የዓለም የአሸናፊነት ደማቅ ታሪክ፤ የይቻላል መንፈስ ምንጭ ነው። አድዋ ጥቁሮች ቀና እንዲሉ ያደረገ፤ ባርነትን ያስቀረ የነጻነት ምልክት የጥቁሮች የአሸናፊነት ሰንደቅ ምልክት ነው፡፡
አደዋ መሪ አለው፡፡ የጥቁሮች አባት የጀግንነት ምልክት ቆራጥ ለሀገሩ፣ደፋር ለወታደሩ ታግሎ ያታገለ የዓለም የምንጊዜም ድንቅ መሪ አጼ ምንሊክ፡፡ አድዋ ተራራ ነው ጣልያን የተሸነፈበት ብቻ ሳይሆን የነጮች ዕብሪት የተቀበረበት የጥቁሮች አሸናፊነት የተበሰረበት ልዩ ቦታ፡፡ የአድዋውን ድል ያለ አጼ ምንሊክ ማሰብ አይቻልም፡፡ ድሉን ወዶ የድሉን መሪ መጥላት ባንዳነት ነው፡፡

ብናውቅስ አድዋ ክብራችን
ምንሊክ ደግሞ የድንቅ መሪ ምልክታችን፡፡
የአድዋ ነገር እንዳለመታደል ሆኖ የእኛ ድል ሆነና " በእጅ የያዙት ወርቅ..." ሆኖብን በሀገር ደረጃም አኮሰስነው። ጭራሽ ከአጼ ምንሊክ የሚሸሹ መሪዎችን ማየት ጀመርን፡፡

ለምን ይሆን አድዋን የመሰለ ደማቅ ታሪክ እንኳን አንድ አድርጎን በአንድ ስሜት ማክበር የተሳነን?

በጋራ ታሪካችን በአድዋ እንኳን ከልዩነት ወጥተን አንድ መሆን አልቻልንም። ከአድዋ የተሻለ ለእኛ የጋራ ታሪክ ምን ይሆን? ።
ላለፉት 30 ዓመታት ኢትዮጵያን የመሩ መሪዎች አድዋን የጋራ ብሔራዊ በዓል አድርጎ ለመቀበልና ለማክበር ለምን ከበዳቸው ? መሪዎቻችን "ለእጅ መታጠብ ቀን" የሚሰጡትን ትኩረት ያህል እንኳን ለአድዋ መስጠት አይፈልጉም።በዓለም ላይ ያሉ ሀገራት የጋራ የሆነ ከመሪ እስከ ተመሪ በጋራ የሚያከብሯቸው የአደባባይ ብሔራዊ በዓላት አሏቸው። በእነዚህ በዓላት ላይ መሪዎች ያለምን ማወላወል ከሕዝቡ ጋር ተገኝተው ያከብራሉ።የደመቀ እንዲሆንም አስቀድመው ይሰራሉ። ነገር ግን ከአድዋ የደመቀ አስደናቂ ታሪክ የተፈጸመበት ሁነት የላቸውም።
አድዋ አሜሪካ ቢሆን? አድዋ እንግሊዝ ቢሆንስ? ...

አድዋ ያልተረሳው በመንግሥት አይደለም በሕዝብ ነው። አድዋ በመንግሥት ተዘንግቷል በሕዝብ ግን ተወስቷል። አድዋን የሚጠሉ መሪዎች አሉን አድዋን የሚወድ ሕዝብ ግን አለን። አድዋ የሕዝብ ነው። መሪዎች ያልፋሉ አድዋ ግን የማያልፍ የማይፋቅ በኢትዮጵያውያን የልብ ጽላት ላይ የተጻፈ አኩሪ ታሪክ ነው።
ሕዝቡ በራሱ አድዋን ያከብራል።ጀግኖቹንም ያወሳል።#የአድዋን_ድል_ባታከብሩም_አድዋን_የሚያከብረውን ሕዝብ ግን አክብሩ! ከእንግዲህ አጀንዳ አትፍጠሩለት። አድዋንም አጼ ምንሊክንም መጥላት ይቻላል፡፡ነገር ግን ታሪኩን ከዓለም የጥቁር ሕዝብ ልብ ላይ መፋቅ አይቻልም፡፡
አድዋ ብዕሩ ደም፣ ወረቀቱ መሬት ሆኖ የተጻፈ ማንም ሊያጠፋው የማይችል ደማቅ የነጻነትና የአሸናፊነት ታሪክ ነው!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኖራለች !

የኤፍሬም እይታዎች!
........................... ...
274 viewsየኤፍሬም እይታዎች, 18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 16:46:34 ✞በሰው ዘንድ ቢሟጠጥ✞

በሰው ዘንድ ቢሟጠጥ ተስፋና ደስታ
እኛስ ፈጣሪ አለን ሁሉን የሚረታ
ተስፋ እንደሌላቸው አንሆንም ከቶ
ክርስቶስ አለልን የሚያሳይ አብርቶ(፪)

ያለቀሱ ሁሉ ይስቃሉ አይቀርም
ይለዋውጠዋል ጌታ መድኃኔዓለም
ማንም ያላሰበው ያልጠበቀውን ድል
ለኛ ለምስኪኖች ጌታ ይሰጠናል
ማንም ያልጠበቀውን ያልገመተውን ድል
ለኛ ለምስኪኖች ጌታ ይሰጠናል
      አዝ = = = = =
ሰዎች ቢጠበቡ ገንዘብ ለመሰብሰብ
ይጠላለፋሉ ባልጠበቁት መረብ
እግዚአብሔርን ይዘው በቅን ካልተጓዙ
ክፋትና ተንኮል ብዙ ነው መዘዙ
       አዝ = = = = =
ድሆች አስለቅሶ ግፍ የሚሰበስብ
ምን ይመልስ ይሆን ጌታ ፊት ሲቀርብ
ለዚህች አጭር ዘመን የሚስገበገቡ
አይረኩም አይጠግቡም ድሆች እያስራቡ
     አዝ= = = = =
የእህል ሽታ ጠፍቶ መሶቡም ቢራቆት
ተስፋችን ሙሉ ነው እኛስ በጌታ ፊት
ይህን ክፉ ዘመን ያሻግራል ጌታ
ከሠራን በኋላ በጸሎት እንበርታ

             መዝሙር
   ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
☞https://t.me/ephremvi
https://t.me/ephremvi

"እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ"
             ማቴ ፳፰ ፥ ፳
651 viewsየኤፍሬም እይታዎች, edited  13:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 14:51:07 1ኛ የጾሙ መጠሪያ ስያሜዎች

ሀ.ዐቢይ ጾም
የባሕርይ አምላክ በሆነዉ በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተ በመሆኑ ዐቢይ ወይም ታላቅ ጾም ይባላል፡፡

ለ.ጾመ ሁዳዴ

በጥንት ጊዜ ገባሮች ለባለ ርስት የሚያርሱት መሬት ሁዳዴ ተብሎ ይጠራ ነበር፡፡ እኛም ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስን እያሰብን የምንጾመው በመሆኑ ጾመ ሁዳዴ ተብሏል፡፡

ሐ.የካሳ ጾም

አዳምና ሔዋን ከገነት የተባረሩት ለውርደት ሞት ለሲዖል ባርነት የበቁት በመብል ምክንያት ነው፡፡ በመብል ምክንያት የሞተውን የሰው ልጅ ጌታችን በፈቃዱ በፈጸመው ጾም ካሰው፤ መንፈሳዊ ረሃብን በረሃቡ ካሰለት፡፡ ስለዚህም የካሳ ጾም ተባለ፡፡

መ.ጾመ ኢየሱስ

ጾመ ኢየሱስ ይባላል ይህም ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ጾሞ ጹሙ ብሎ ስላዘዘን።

ሠ.የቀድሶተ ገዳም ጾም

ጌታችን ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ በመጾም ከከተማ ርቆ ከሰው ተለይቶ በብሕትውና መኖርን ቀድሶ የሰጠበት፣ የመጥምቁ ዮሐንስና የነቢዩ ኤልያስን ገዳማዊነት የባረከበት በመሆኑ የቀድሶተ ገዳም ጾም ተብሏል፡፡

ረ.የመዘጋጃ ጾም

ሕዝበ እሥራኤል የፋሲካውን በግ ከመመገባቸው በፊት ዝግጅት ያደርጉ ነበር፡፡ እኛም ትንሣኤን ከማክበራችን፣ ሥጋና ደሙን ከመቀበላችን በፊት በጾምና በጸሎት ዝግጅት የምናደርግበት በመሆኑ የመዘጋጃ ጾም ተብሏል፡፡

2ኛ የዐቢይ ጾም ሳምንታት ስያሜዎች

፩ኛ)የመጀመሪያው እሑድ(ሳምንት)፥ ዘወረደ (ሙሴኒ፣ ጾመ ሕርቃል) ይባላል፡፡  አምላክ ከሰማይ መውረዱን፣ ሰው መሆኑንና መስቀሉን ስለሚያወሳ ነው፡፡

፪ኛ. የሁለተኛው እሑድ፥ ቅድስት ይባላል፤ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው።

፫ኛ. የሦስተኛው እሑድ፥ ምኲራብ ይባላል፤ በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኲራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡

፬ኛ. ዐራተኛው እሑድ፥ መፃጉዕ ይባላል፤ ድውያንን መፈወሱን፣ ዕውራንን ማብራቱን፣ የሚያነሣ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡

፭. አምስተኛው እሑድ፥ ደብረ ዘይት ይባላል፡፡ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሁኖ ያስተማረው ትምህርት፥ የዳግም ምጽአትን ነገር የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡

፮. ስድስተኛው እሑድ፥ ገብርኄር ይባላል፡፡ የጌታውን ብር ተቀብሎ ያተረፈበት፣ በጌታውም ፊት ምስጋናን ያገኘው ሰው ታሪክ ይዘመርበታል፡፡

፯. ሰባተኛው እሑድ፥ ኒቆዲሞስ ይባላል፡፡ በሌሊት ወደ ጌታ እየመጣ ይማር የነበረውን የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡

፰. ስምንተኛው እሑድ፥ ሆሣዕና ነው፡፡ ጌታ በአሕያ ውርንጭላ ሆኖ ሆሣዕና በአርያም እየተባለ ወደ ቤተ መቅደስ የገባበት ዕለት መታሰቢያ ነው፡፡
 ከሠርክ ሆሣዕና እስከ ትንሣኤ ያለው ሰባት ቀን ሕማማት ይባላል፡፡- የጌታን መከራና ስቃይ እንዲሁም ሞት የምናስታውስበት ሳምንት ነው ፡፡

ጾሙን የበረከት ጾም ያድርግልን

#አተማሩበት Share ያድርጉ
የኤፍሬም እይታዎች
1.1K viewsየኤፍሬም እይታዎች, 11:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 20:34:32 ችግርህን ሳይሆን አምላክህን ተመልከት!
✞.......................✞..................✞

#ከተራራ_ለገዘፈ_ችግርህ_እግዚአብሔር_መልስ_አለው፡፡
................................................
የተወደዳችሁ ወዳጆቼ እንደምን ከረማችሁ፡፡ሰሞኑን በቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ በደረሰው ፈተና ብዙዎቻችን በሀዘን ተውጠን ነበር፡፡ ይኼንን ድርጊት በዘመናችን በመከሰቱ የተወለድንባትን ቀን እስከ መርገም ደርሰን ነበር፡፡ ችግሩ እንደ ተራራ ገዝፎ ሲያይ ጠላት ተዋህዶ ያበቃላት ቤ/ክንም የምትጠፋ መስሎት የደስታ ፉከራ ለመፎከር የደስታ ነጋሪትም ለመጎሰም ሲዘጋጅ አባቶቻችን እንዲህ አሉን " ሥስት ቀን ማቅ ልበሱ ጹሙ ጸልዩ" መልሳችን ከአምላክ ዘንድ ነው፡፡ በማለት ተናገሩን እኛም በአንድ ልብ ሆነን "የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ" ብለን እየዘመርን ወደ አምላካችን አለቀስን አምላካችንም መልስ ሰጠን፡፡ ፈጣን መልስ ለምን ያገኘን ይመስላችሗል ? መልሱ አጭር ነው፡፡ ችግራችን ሳይሆን አምላክችንን ስለተመለከትን ነው፡፡በጉልበታቸው የተመኩ የተሸነፉት እኛ ጉልበታችንን እግዚአብሔርን ስላደረግን ነው፡፡ የጠፋን የመሰላቸው በዝተን፤ የወደቅን የመሰልናቸው ቆመን የተመለከቱን ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታችን ራሳችንን ስላዋረድን ነው፡፡ ጠላት በአራት አቅጣጫ ሊውጠን ቢያሰፈስፍ ሰልፉ የእግዚአብሔር ከሆነ አሸናፊዎች እኛ ነን፡፡ ለዚህ ታሪክ በደንብ ማስረጃ የሚሆነን ቀጣዩ ምሳሌ ነው:-
"በአንድ ወቅት ለመውለድ ቀኗ የደረሰ አንዲት ነፍሰ ጡር አጋዘን ጥቅጥቅ ባለ ደን ውስጥ ከሚገኝ አንድ ምቹ ቦታ ጠጋ አለች ።ቦታው ዙሪያውን በሳር ተሸፍኗል። በቅርብ ርቀት እየተምዘገዘገ የሚፈስ ዥረት አለ ።
ያለችበት ቦታ ምቹና ነፃ ይመስላል ። በስቃይ የታጀበው ምጥ ድንገት ጀመራት ። ደመናው በቅፅበት መልኩን ቀይሮ የአካባቢውን ድባብ ለወጠው ። በመብረቅ የተመታው ደን በእሳት ተያያዘ ። ሰማዩ በነጎድጓዳማ መብረቅ እየታረሰ ነው ።

አጋዘኗ ወደ ግራ ስትመለከት ፣ ግራ እጁን ከደጋኑ እምብርት ላይ አኑሮ በቀኝ እጁ ቀስቱን ወጥሮ ወደርሷ ያነጣጠረ አንድ #አዳኝ ተመለከተች ።
ወደ ቀኝ ስታማትር ርሃብ ያሰከረው አንበሳ በቅርብ ርቀት ወደ እርሷ እየተጠጋ መሆኑን
አስተዋለች ። ይህች ነፍሰ ጡር አጋዘን ማድረግ የምትችለው ምንድን ነው ?

ከዚህ አጣብቂኝ ለመውጣት ምን አይነት ብልሃት መዘየድ ይጠበቅባታል ? አደገኛ ምጥ ላይ ነው ያለችው ! ልጇን በሰላም ትገላገል ይሆን ?
ነው ወይስ በእሳት የሚንቀለቀለው ደን ሁሉንም ያጠፋቸው ይሆን ? አዳኙ የወጠረው ቀስት ህይወቷን ይነጥቃት ይሆን ? ከአንበሳው መንጋጋ ውስጥ ገብታ ህይወቷ አሰቃቂ በሆነ መልኩ ይቀጠፍ ይሆን ?
.
በእሳት እየተንቀለቀለ ያለው ደን እንቅስቃሴዋን አገተው ፤ እየተወረወረ የሚፈሰው ወንዝ መራመድ እንዳትችል ገደባት ። የአንበሳው እጣ ላለመሆን መስዋዕትነት መክፈል እንዳለባት ደመ ነፍሷ ነገራት ። ከተወጠረው ቀስት መሸሽ አማራጭ የሌለው መፍትሄ መሆኑን አመነች ።
ልጇን በሰላም የመገላገል ጉጉቷ ቅስሟን ሰበርው

ነገር ግን ከተደቀኑባት ዘርፈ ብዙ አደጋዎች ለመዳን የሚያስችል ብልሃት አጣች ።የእርሷንም ሆነ የልጇን ውድ ህይወት በሚቀጥፉ አደጋዎች መከበቧ መላ ለመዘየድ ፋታ አሳጣት ። ታዲያ ከዚህ ሁሉ ውስብስብ ፈተና ለማምለጥ መንገዱ ምን ይሆን ???

አማራጭ እንደሌላት ስተረዳ ትኩረቷ ልጇን መገላገል ላይ ብቻ ሆነ ። ከህልፈቷ በፊት
ህይወት መስጠት የምትችልበትን እድል መጠቀም መረጠች ። ምጧ እጅግ ተፋፋመ ።
ስቃይዋ በረታ ። ሰውነቷ ተርገፈገፈ ።እግሮቿ ተለጠጡ ። በፈተናዎች ተከባ በሞት ወጥመድም ተከባ ሳለ ፈጣሪዋ ትዝ አላት #ቋንቋዋን ወደ ሚሰማ አምላክ ጮኸች፡፡ እግዚአብሔርም ተዓምራትን ገለጠ ።

መብረቁ ቀስቱን ከወጠረው አዳኙ አይኖች ላይ ተንፀባረቀ ። ቀስቱ ኢላማውን ስቶ ስጋ ካማረው አንበሳ ጉሮሮ ላይ ተሰካ ። እፎይ !

ካረገዙት ዳመናዎች የሚንቧቧ ውሃ ወረደ ። በእሳት የሚነደው ጫካ ረጠበ ። እፎይ !

ከለምለማማው መስክ ላይ አንድ ድምፅ ተሰማ ።
ጫካው አዲሱን ድምፅ ለመጀመሪያ ጊዜ ተቀብሎትእንደ #ገደል__ማሚቶ አስተጋባው ።
የዥረቱ ሃይል ጨመረ ።አንበሳውም ተዘረረ ።
ዳመናዎች ተቀደዱ ። የወንዙ ሙላት አዳኙን በስጋት ናጠው ። በመብረቅ ታጅቦ የሚዘንበው ዝናብ አስጨነቀው ። ጫካውን ጥሎ እግሬ አውጪኝ አለ ። ከለምለሙ መስክ ላይ የሚሰማው ቀጭን ድምፅ ማስተጋባቱን #ቀጠለ

ያ ድምፅ የወጣው እናቷ ከተፈጥሯዊ ምጥ የበለጠ አስቸጋሪ ፈተና ውስጥ መግባቷን
ሳትመለከት ውቡ መስክ ላይ ከተወለደችው ግልገል አጋዘን አንደበት ነበር #እናት የአብራኳን ክፋይ በእቅፏ አስገባች ። ጠረኗን ከልጇ ጠረን አጋባች ።

ገላዋን በፍቅር # ላሰች ። የህይወትን ሀሁ ማስተማር ጀመረች ።
⚂ ከአንበሳ መንጋጋ ልትገባ የነበረችው ሚስኪን ነፍስ በፈጣሪዋ እገዛ #አርነት ወጣች ።
በሚንቀለቀል የደን እሳት አመድ ለመሆን ቋፍ ላይ የነበረችው ነፍሰ- ጡር ነፍስ በፈጣሪዋ እርዳታ ሌላ ነፍስ ሰጠች ።
የቀስት ኢላማ ውስጥ ገብታ የነበረችው የዋህ ነፍስ በፈጣሪዋ ወሰን የለሽ ጥበብ
ታግዛ እድሜዋ ቀጠለ ።
⚂አሰፍስፈው የነበሩት አዳኞች ድምጥማጣቸው ጠፋ ።
⚂የጦርነት ቀጠና የነበረው አካባቢ የሰላም አየር ተነፈሰ ጫካው አዲስ በመጣችው ግልገል አጋዘን ድምፅ ደምቋል ። እናትና ልጅ ለዘመናት
ተጠፋፍተው የተገናኙ ይመስል በሃሴት እየተፍለቀለቁ አካባቢውን ነግሰውበታል ።
አንበሳው ከጎናቸው ተዘርሯል ። የአንበሳውን ስልጣን አጋዘኖቹ ወረሱት ።

ከዙፋኑ ላይ ተሰየሙ ። የጫካ ንግስናውን ነጠቁ ። አክሊሉን ደፉ ። ኢላማዋን ስታ ጉሮሮው
ውስጥ በተሰነቀረች ቀስት የአንበሳው ስልጣን አከተመ ። አዳኙም ሆነ አንበሳው የአጋዘኗን
ስጋ ቢጎመዡም ያልታሰበው ተከሰተ ።
በላተኞች #እርስ__በርስ ተባሉ ። እናት እና ልጅ ለምለሙ መስክ ላይ በሰላም ተንጎማለሉ

ንግስናን የሚሰጠውና የሚነሳው ፈጣሪ ነው ።
የእርሱ ስራ እንዲህ ነው ። ፈጣሪህ በጉልበታቸው ተማምነው ሊበሉህ የተነሱ አካላትን መንጋጋ ያራግፋል ። ከተራራ የገዘፈ ችግርህን ያንኮታኩታል ። ወዳንተ የሚወደሩ አጥፊ ቀስቶችን ያኮላሻል ። በራስህ አስቸጋሪ የህይወት ውጣ ውረድ ተወጥረህ በዙሪያህ ተደራራቢ ፈተናዎች ሲደቀኑብህ በጭንቀት መርገፍገፍ ሰዋዊ ባህሪ ነው ።

ቅድሚያ ለየትኛው መስጠት እንዳለብህ እስኪያቅትህ ድረስ በፈተና መዛል የማይቀር ነው ።
ከቁጥጥርህ ውጭ ያሉ ነገሮችን መጋፈጥ አስቸጋሪ ቢሆንም በቁጥጥርህ ስር ያሉትን
መጋፈጥ ግን አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ።
ህይወት ከውስጥና ከውጭ በሚመነጩ ፈተናዎች የተከበበች ነች ። የምትችለውን
ከሰራህ ቀሪውን መከራ የጥበብ ባለቤት የሆነው #አንድየ እግዚአብሔሬ ጣልቃ ገብቶ ነፃ እንደሚያወጣህ ልበ ሙሉነት ይሰማህ እመን የማይታለፍ የተባለውን ችግር ያሳልፍሃል።

አስቸጋሪና ውስብስብ የተባሉ ፈተናዎችን የምናልፈው በእኛ ብርታት ሳይሆን ጥብበኛው እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ስለሆነ ነው፡፡
የሚጠብቀን አይተኛም አያቀላፋም !
....
@የኤፍሬም እይታዎች
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
873 viewsየኤፍሬም እይታዎች, 17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 19:42:08 Channel photo updated
16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 11:36:17
ውዱ ወንድሜ መምህር ዐቢይ ተፈቷል
........... .................... ........ ...........
አንተ የእውነት ሰው፤ ለቤተክርስቲያን ስትል የወጣትነት ዘመንህን የገበርክ ከተሐድሶ እስከ ዘረኞች ቤተክርስቲያን ላይ በደረሰው ፈተና ራስህን መስዕዋት ድርገህ ያቀረብክ:: ይኼ ሁሉ መከራ ሰለ ሃይማኖትህ ነው፡፡ የቅዱሳን አምላክ ዋጋህን ይክፈልህ!!
706 viewsየኤፍሬም እይታዎች, edited  08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 20:01:37
-በአባቶቻችን ጥበብ በተሞላበት አካሄድ፣ በገዳማውያን ጸሎት፣ የምእመናን ልቅሶ መነበረ ጸባዖት ደርሶ መልስ አሰጥቶናል፡፡
ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ!

"በቅርቡ በቤተ ክርስቲያናችን ተከስቶ የነበረው ችግር በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሰረት ተፈቷል"
---የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ

- "ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሦስቱ አባቶች መመለስ እግዚአብሔርን ታመሰግናለች"--- ብፁዕ አቡነ አብርሐም

@የታሰሩት አገልጋዮችና ምእመናን ይፈቱ፡፡ ፍጻሜውን ያሳምርልን
855 viewsየኤፍሬም እይታዎች, 17:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 07:42:54 ነነዌና እኛ !
..............
ነነዌ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ታሪካቸው በስፋት ከተጻፈላቸው የሜሶፖታምያ ከተሞች አንዷ ናት፡፡

ብዙ የሥነ መለኲት ምሁራን ከዛሬዋ የሞሱል ከተማ በተቃራኒ ከባግዳድ ሰሜን ምዕራብ 350 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ እንደ ነበረች ይስማማሉ፡፡

ምንም እንኳን በ4000 ቅ.ል.ክ. ገደማ በናምሩድ በኩል ብትቆረቆርም 《ዘፍ.10፡11-12》 የአሦራውያን ዋና ከተማ የሆነችው ግን በ1400 ቅ.ል.ክ. ነው 《2ነገ.19፡36》፡፡ በከተማዋ በጣም ታዋቂ የነበረው የጣዖት ቤተ መቅደስ የአስታሮት ቤተ መቅደስ ይባላል፡፡
በዚህች ከተማ የሚኖሩት ሰዎች የሚሠሩት ክፋትና ኃጢአት እጅግ ከመብዛቱ የተነሣ ጽዋው ሞልቶ መጥፊያቸው ስለ ደረሰ ለፍጥረቱ ርኅራኄ ያለው እግዚአብሔር ግን ንስሐ ይገቡ ዘንድ ነብዩ ዮናስን ልኮላቸዋል፡፡

ይህ ነብይ ከአሕዛብ ወደ አሕዛብ የተላከ ነብይ ነው፡፡ አላላኩም አንድ ነብይ ወደ እስራኤላውያን ተልኮ እንደሚያደርገው ለመገሰጽ ሳይሆን ወደ ንስሐ ይጠራቸው ዘንድ ነበር፡፡


ነገር ግን ነብዩ ወደዚያች ከተማ እንዲሄድ በእግዚአብሔር ቢታዘዝም ወደ ተርሴስ ሲኮበልል እንመለከተዋለን፡፡

☞ቅዱስ ጄሮም ነብዩ ለምን እንዲህ እንዳደረገ ሲናገር፡-


“ዮናስ አሕዛብን ከመጥላቱ የተነሣ ሳይሆን መዳን ከእስራኤል እየራቀ መሆኑን በትንቢት መነጽር ሲመለከት ወደ ነነዌ አልሄድም አለ፡፡

ይኸውም ሙሴ ይህን ሕዝብ ከምታጠፋው እኔን ከሕይወት መጽሐፍህ ደምስሰኝ ያለው ዓይነት ነበር 《ዘጸ.32፡31-32》፡፡

ቅዱስ ጳውሎስም “ስለ እነርሱ እርሱ ቢረገም እንደሚመርጥ እንደሰማነው” ብሏል 《ሮሜ.9፡3》፡፡


በእርግጥም በዘመነ ሐዲስ አሕዛብ በክርስቶስ አምነው ሲጠመቁ እስራኤል ግን መጻሕፍትን ብቻ ይዘው ቀርተዋል፤ እስራኤል ነብያትን ብቻ ይዘው ሲቀሩ አሕዛብ ግን የነብያቱን የትንቢት ፍጻሜ ይዘዋል 《ማቴ.12፡42》፡፡
ልብና ኩላሊት ያመላለሰውን የሚያውቅ አምላክ ግን ዮናስ ላለመታዘዝ ብሎ እንዳላደረገው ስላወቀ በልዩ ጥበቡ ሲወስደው እናያለን፡፡


አስቀድሞ ታላቅ ነፋስን በመርከቢቱ ላይ አመጣ፤ ዮናስን የሚውጥ ታላቅ ዓሣ አሰናዳ፤ ቀጥሎም ዓሣው በየብስ እንዲተፋው አደረገ፡፡
ዮናስ ወደዚያች ከተማ ከደረሰ በኋላ ግን ምንም እንኳን የሦስት ቀን መንገድ ዙሮ መስበክ ቢጠበቅበትም የአንድ ቀን መንገድ ያህል ወደ ከተማይቱ ውስጥ ሊገባ ጀመረ፤ ጮኾም በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች አለ።

የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ፤ ለጾም አዋጅ ነገሩ፥ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ (ጥቁር) ለበሱ። ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፤ እርሱም ከዙፋኑ ተነሥቶ መጐናጸፊያውን አወለቀ ማቅም ለበሰ፥ በአመድም ላይ ተቀመጠ። አዋጅም አስነገረ፥ በነነዌም ውስጥ የንጉሡንና የመኳንንቱን ትእዛዝ አሳወጀ፥ እንዲህም አለ፡- “ሰዎችና እንስሶች ላሞችና በጎች አንዳችን አይቅመሱ፤ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ፤ ሰዎችና እንስሶችም በማቅ ይከደኑ፥ ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩኹ፤ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።
እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይጸጸት እንደ ሆነ፥ ከጽኑ ቍጣውም ይመለስ እንደ ሆነ ማን ያውቃል? በማለት፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስም ያዘዘን ይኼንኑ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሀሳብ መነሻ በማድረግ ነው፡፡


” ሰው ወዳጁ ጌታም ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውን አየ፤ ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም።

በእርግጥም እግዚአብሔርን የሚፈራ ልቡና የትምህርት ጋጋታ አያስፈልገውም፤ የቀናት ብዛት አያስፈልገውም፡፡

እኛ ክርስቲያኖችም ይህን በማዘከር “ንስሐ ብንገባ እንደ ነነዌ ሰዎች ጥቁር ለብሰን ብናለቅስ ከተቃጣው ማንኛውም መቅሰፍት በቤተክርስቲያን ላይ የተደቀነውም ፈተና እርሱ ይታደገናል ” በማለት ነው የሦሥቱ ቀን ሱባኤአችን፡፡ ይህ ጾም በየዓመቱ ከዓብይ ጾም መግቢያ ሁለት ሳምንት አስቀድማ ካለችው ሰኞ ጀምሮ እስከ ረቡዕ ድረስ “ጾመ ነነዌ” በማለት እንጾማታለን፡፡ ዘንድሮም ዓብይ ጾም የካቲት 13 ስለሆነ ከሰኞ ጀምረን እስከ ዛሬዋ ዕለት ድረስ በድርብ መልኩ ጸሎተ ምኅላ ጨምረን ማቅ ለብሰን እንደነነዌ ሕዝቦች ጾመናል ጸልየናል፡፡

ይህ የሱባኤ ቆይታችን እግዚአብሔር የመረጠውን ዓይነት ጾም ሆኖ የእናት አባቶቻችን ልቅሶ ተመልክቶ የሕጻናቱን ልመና ተቀብሎ አምላክ ከተቃጣው ማንኛውም ዓይነት ፈተናም እንድናመልጥ ሰውን በመውደድ ሰው የሆነው ክርስቶስ ይርዳን አሜን!

ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን የተሰዉ የሻሸመኔ ሰማዕታት ደም መንበረ ጸባዖት መልስ ያሰጠን፡፡ አሜን

የኤፍሬም እይታዎች
...............
1.3K viewsየኤፍሬም እይታዎች, 04:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 21:03:55
1.2K viewsየኤፍሬም እይታዎች, 18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 22:39:13
1.3K viewsየኤፍሬም እይታዎች, 19:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ