✞በሰው ዘንድ ቢሟጠጥ✞ በሰው ዘንድ ቢሟጠጥ ተስፋና ደስታ እኛስ ፈጣሪ አለን ሁሉን የሚረታ ተስፋ እንደሌላቸው አንሆንም ከቶ ክርስቶስ አለልን የሚያሳይ አብርቶ(፪) ያለቀሱ ሁሉ ይስቃሉ አይቀርም ይለዋውጠዋል ጌታ መድኃኔዓለም ማንም ያላሰበው ያልጠበቀውን ድል ለኛ ለምስኪኖች ጌታ ይሰጠናል ማንም ያልጠበቀውን ያልገመተውን ድል ለኛ ለምስኪኖች ጌታ ይሰጠናል አዝ = = = = = ሰዎች ቢጠበቡ ገንዘብ ለመሰብሰብ ይጠላለፋሉ ባልጠበቁት መረብ እግዚአብሔርን ይዘው በቅን ካልተጓዙ ክፋትና ተንኮል ብዙ ነው መዘዙ አዝ = = = = = ድሆች አስለቅሶ ግፍ የሚሰበስብ ምን ይመልስ ይሆን ጌታ ፊት ሲቀርብ ለዚህች አጭር ዘመን የሚስገበገቡ አይረኩም አይጠግቡም ድሆች እያስራቡ አዝ= = = = = የእህል ሽታ ጠፍቶ መሶቡም ቢራቆት ተስፋችን ሙሉ ነው እኛስ በጌታ ፊት ይህን ክፉ ዘመን ያሻግራል ጌታ ከሠራን በኋላ በጸሎት እንበርታ መዝሙር ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ ☞https://t.me/ephremvi https://t.me/ephremvi "እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ" ማቴ ፳፰ ፥ ፳ 651 viewsየኤፍሬም እይታዎች, edited 13:46