Get Mystery Box with random crypto!

አትሮኖስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የሰርጥ አድራሻ: @atronosee
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 163.71K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-05-10 19:14:15 ለሰባት ወራት አብረን ኖርን፡፡ ለወራት በዘለቀ የነፍስ ግንኙነታችን ስለ ራሴ ያልነገርኳት፣ _ ስለ _ እርሷም _ ያልነገረችኝ _ ነገር _ አልነበረም፡፡ እናትና አባቷን እታውቃቼዉም፣ የተወለደችው ሞሪታኒያ የምትባል አገር ነው፡፡ እስከ ዐሥራ አንድ ዓመቷ ያሳደጋት ፈረንሳዮች የሚያስተዳድሩት የማደጎ ድርጅት ነበር፡፡ ዕድሜዋ ዐሥራ አንድ ሲደርስ ግን የአገራቼው መንግሥት ከቀድሞ ቀኝ ገዣቼው ፈረንሳይ መንግሥት ጋር ባለመግባባቱ፣ ፈረንሳዮች ማሳደጊያውን ዘግተው፣ ልጆቹንም በትነው ሄዱ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኑሮዋ የመከራ ሆነ፡፡ በዋናነት ለቱሪስቶች በእጅ

የተሠሩ ባህላዊ ጌጣጌጦች በመሸጥ፣ በመላላክ፣ልብሳቼውን በማጠብ በኋላም አንዳንድ ታሪካዊ ቦታዎችን በማስጎብኜት ኑሮዋን መግፋት ጀመረች፡፡ ዕድሜዋ 16 ሲደርስ አንድ እንግሊዛዊ ጋር ተኛች፡፡ እርሷ ሰውዬውን ወዳው ነበር። በወቅቱ ብር ሲሰጣት ለእርሷ የፍቅር መግለጫ ነበር የመሰላት፤ ሲቆይ ግን ሌሎችም ጋር ተመሳሳይ ነገር እንደሚያደርግ ደረሰችበት፡፡ የፍቅር ታሪኳ ባጭሩ ተቀጨ፡፡ ሌሎች ቱሪስቶችም ብር እየከፈሏት በድብቅ ይወስዷት ጀመሩ። ያለፈችበትን የድህነት ሕይወት በዚህ መንገድ ማለፍ እንደምትችል አሰበች ዓይታው የማታውቀው ብር ማግኜት ጀመረች፤ እናም ሙሉ ለሙሉ የሴተኛ አዳሪነት ሥራ ውስጥ ገባች፡፡ በሞሪታኒያ ሕግ ሴተኛ አዳሪነት በጥብቅ የተከለከለና በእስራት የሚያስቀጣ በመሆኑ በአንድ ዕድለ ቢስ ምሽት ተደረሰባትና ተያዘች። ለፖሊሶች ያላትን ገንዘብ ገላዋንም ጉቦ ሰጥታ ከእስር ቤት ካስወጧት በኋላ ወደ ሞሮኮ ተሰደደች፡፡ በአንድ በሚያውቃት ፈረንሳዊ ቱሪስት ተረድታ ነበር ወደዚያች ከተማ የደረሰችው። ሰውዬው ወደ ፈረንሳይ እንደሚያሻግራት ቃል ገብቶላት ሞሮኮ እንደደረሱ በአንድ ቅንጡ ሆቴል ለአንድ ሳምንት ያኽል ተዝናንቶባት እንደ ወጣ ቀረ። ከዚያ በኋላ ኑሮዋን በሴተኛ አዳሪነት መግፋት ቀጠለች። ውብ ሰውነቷ ወንዶች የሚሻሙበት ሴት አደረጋት፡፡ እርሷም ገንዘብ ይዘው ጎራ የሚሉ ወንዶችን ከሌሎች ሴቶች ጋር ተሻምታ የምትኖር ሴት ሆነች፡፡ ከዚያ የተረገመ ምሽት በኋላ የምትሠራበት መሸታ ቤት እንዳልሄድ ከለከለችኝ፡፡ ያንን ሥራ ስትሠራ እንዳያት አትፈልግም ነበር፡፡ ሥራዋ ላይ በጣም ቁጡ እና ሞገደኛ ነበረች፡፡ ጋጠወጥ ወንዶች በሚበዙበት በዚያ ጋጠወጥ መሸታ ቤት፣ በቢራ ጠርሙዝ የፈነከተቻቼው፣ እንጀራ ነውና በወንድ ተጣልታ ፊታቼውን በጥፍሯ የተለተለቻቼው ብዙ ነበሩ፤ ራሷ ናት የነገረችኝ፡፡ ለአንተ ብቻ ነው ጨዋ የሆንኩት ትለኛለች፡፡ ድንገት ሰዎች ጋር በእርሷ ምክንያት እንዳልጣላ ትፈራ ነበር፡፡ ከምንም በላይ ግን እኔ ፊት ሌሎች ወንዶች ጋር ስትወጣ እንዳይ አትፈልግም ነበር። በእርግጥ እኔም ያንን ቦታ ሳስበው ይቀፈኛል፤ ይቀፈኛል ብቻ አይደለም ቅናት

ያንገበግበኛል፡፡ ሥራውን ተይው ልላት አስብና “የማያዋጣ በል ቅንድብ ይስማል እንደሚባለው” ይሆንብኛል፡፡ ሰው ቤት ተቀጥራ ለመሥራት ብዙ ሞክራ ነበር፤ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላት ሴት መቅጠር አልፈለጉም። ይህች ሴት ጋር በባህልም ሆነ በቋንቋ አንገናኝም፡፡ ሞሪታኒያ ከምትባል አገር የተገኜች ሴት አፈቅራለሁ ብዬ ላስብ ይቅርና ከዚያ በፊት ሞሪታኒያ የምትባል አገር የት ናት? ቢሉኝ እምላለሁ! አላውቃትም ነበር፡፡አንድ ቀን የት ነች ሞሪታኒያ? ብዬ ጠዬቅኋት “እዚሀ ነች'ኮ” አለችኝ በአገጯ እየጠቆመች፡፡ እውነትም እዚያው ነበረች፡፡ ሰው አገሩን ይመስላል እንዴ? ሞሪታኒያ በምዕራብ በኩል አትላንቲክ ውቂያኖስ የሚያዋስናት፤ በሰሜን ደግሞ ንዳዳሙን የሰሃራ በርሃ ተንተርሳ የከተመች አገር ናት። በእሳትና ውሃ መኻል ያለች አገር የፈጠረቻት፤ እሳትና ውሃ የሆነች ልጅ ጋር ነበርኩ።

ሞሮኮና ሞሪታንያ ነገረ ሥራቼው እንደ ኢትዮጵያና ኤርትራ ነው። ሲላቼው ታሪክ አጣቅሰው፣ አንዱ የአንዱን ድንበር ይገባኛል ይላሉ፡፡ እንዲያውም ሞሮኮ የሚለያቼውን በርሃ ተሻግራ ሙሉ ሞሪታኒያ የታላቋ ሞሮኮ አካል ነበረች ትል ነበር፤ ማለት ብቻ አይደለም ሞሪታኒያን እንደ አገር እውቅና ሳትሰጣት ቆይታለች፡፡ ቅኝ ገዥዎች በመኻል _ ገብተው ከናካቴው አለያዩዋቼውና _ አረፉት፡፡ ከቅኝ ግዛት ፈረንሳይኛ ቋንቋና ድህነት የተረፋቼው ሕዝቦች የሚኖሩባት አገር ናት፡፡ ይህች ከድፍድፍ ነዳጅ እስከ ወርቅ፣ ከብረት እስከ ዩራኒዬም፣ የተቼራት አገር ሕዝቦቿ ባገኙት ቀዳዳ እንደቀረው አፍሪካዊ ሁሉ የስደትን ጽዋ ይቀምሳሉ፤ ርግማን ነው። ስደት የሚባለው ነገር ምኑን ከምኑ እንደሚቀላቅለው ሳስብ፣ የሆነ ጢማም ተንኮለኛ ሳይንቲስት ይመስለኛል፡፡ ቁጭ ብሎ ዓለምን እንደ ላብራቶሪ ብልቃጥ ፊቱ አቅርቦ፣ እኛን ነዋሪዎቿን ከዚያና ከዚህ እያነሳ የሚጨምረን እና እስክንዋሃድ የሚወዘውዘን፤ የሚበጠብጠን፡፡ ስደት ትርምስ ነው፡፡ ስደት መለያዬት ነው። ደግሞም ስደት መቀላቀል

የሆነ ሆኖ እንደዚያ ስወድቅ ስነሳ አልሳካ ያለኝን ወደ አውሮፓ የመሸገር ሕልም፤ ገላዋን ሸጣ፣ ያጠራቀመቻትን ጥሪት አሟጣ፣ ስደቴን ባላሰብኩት ፍጥነት ያሳካችልኝ ይቺ ሴት ነበረች ብል ማን ያምናል?! የአገሬ የሰርግ ቤት ዘፋኝ “ምን ያለው አማጭ ነው የተክለፈለፈ ማሩን ከወተቱ ቀላቅሎት አረፈ!'' ያለው እንዲህ ያለ ነገር ቢገጥመው ይመስለኛል፡፡ ራስህን ወተት እልክ አልባልና፣ ብልም ግን እውነት አለኝ - ወተትም እንደ እኔ አልተናጠ!! አጥባቂ ሃይማኖተኛ ቤተሰብ ውስጥ ነው ያደግሁት፡፡ እንኳን ሴተኛ አዳሪነትን የቤት ልጆች ነን የሚሉ ሴቶች ጋር በፍቅር መቀራረብ በሩቅ የምፈራ ነበርኩ፤ ግን ሕይወት እንዲህ ነውና እዚች ልጅ ጋር የጦፈ ፍቅር ውስጥ ወደቅሁ። ከቀለበት ውጭ ልክ እንደ ባለ ትዳር ነበር አኗኗራችን፡፡ ዛናታ ሕልም አልነበራትም፣ የመሰደድም ወደ አገሯ የመመለስም ዕቅድ አልነበራትም፣ በአገሯ ይኼ ሥራ ነውር ነው፤ ግን ደግሞ ሕይወት ነውር አታውቅም፡፡ ያቺ መልካም ሴት እኔ ጋር እስክንገናኝ ምንም ዕቅድ አልነበራትም፤ በቃ ሴተኛ አዳሪ ናት...ትሠራለች ትኖራለች፡፡ እኔን ካገኜች በኋላ ግን ተስፋ ጀመረች፡፡ መጀመሪያ እኔ ከወጣሁ በኋላ ልትከተለኝና አውሮፓ ልንኖር አቀድን፡፡ ስለምንወልዳቼው ልጆች አወራን ... የመጨረሻ ቀን ምሽታችን፣ አሳዛኝ ግን ደግሞ በተስፋ የተሞላ ነበር፡፡ በሌሊት ባሕር ወደምንሻገርባት ጀልባ የሄድነው አብረን ነበር። የመጨረሻ ቃሏ ምን ነበር “ፈጣሪ ይከተልህ!" ብላ ከብር የተሠራ ጫፍና ጫፉ እንደ እባብ ጭንቅላት የተድበለበለ ቀጭን “ብራዝሌት' ግራ እጄ ላይ አጠለቀችልኝ፡፡ “በእኔ አገር ባህል ይኼ ከክፉ መንፈስ ይከላከላል ብለን እናምናለን” አለችኝ፡፡ የእናቴ አምላክ እና የዚች የሰው አገር ሰው አምላክ ተባብረውም ቢሆን አንድ እኔን አንከብክበው ይህችን ውሃ ማሻገር ያቅታቼዋል!? እያልኩ ነበር አርባ ሰባት ስደተኞች በጫነች አሮጌ ጀልባ ባሕር የቀዘፍኩት። እንዲህ ነበር ዛናታ ጋር የተለያዬነው። ብሯን ለመሳፈሪያ፣ አምባሯን ለማስታወሻ፣ ሰውነቷን ለወንድነቴ መጀመሪያ አድርጋ በብዙ ፍቅር ሸኜችኝ።

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
5.4K viewsTsiyon Beyene, 16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-03 21:59:40 ‹‹ቆይ ግን እስከአሁን ስልኳንም እንኳን ማግኘት አልቻልክም?››

‹‹ምን አገኛለሁ፤አንድ ቀን ሳሪስ አካባቢ ካለ የህዝብ ስልክ ትደውልልኛለች፣ በሌላ ቀን ደግሞ ከካሳንቺስ ይሆናል፣ ሲያሰኛት ደግሞ ከቦሌ ትደውልልኛለች፡፡››

‹‹ግን ለእሷ ያለህ ስሜት ከአድናቆት አልፎ ወደ ፍቅር እንደተመነደገ ነግረሀታል?››

‹‹መቶ ጊዜ ነዋ፡፡››

‹‹እና ምን አለችህ?››

‹‹ብታየኝ ልትጠላኝ ለማፍቀሩ ምን አቅነዘነዘህ ?›› ::

‹አይ ሁሴን! እውነቷን እኮ ነው፡፡ መቼስ አንድ ችግር ሳይኖርባት እራሷን ይሄን ያህል አትደብቅም፤ለዛውም እንዲህ በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያላት ተስፈኛ ደራሲ ሆና...፡፡ እኔም እንደ እሷ የምመክርህ አንድ ነገር ቢኖር እርሳትና የቤት ልጅ ሲያምርህ ኤደንን ፣የቡና ቤት ሲያምርህ ደግሞ ትንግርትህን እየላስክ እንደቀድሞህ ኑሮህን በደስታ ዘና ብለህ ኑር ብዬ ነው፡፡ ሁለቱም ካስጠሉህ ደግሞ መቼም አንተን የማትመኝ የአዲስ አበባ ወጣት የለችም፤ እንኳን ዝና ታክሎበት ቀርቶ እንዲሁም ቁመናና መልክህ የሆሊውድ አክተር አይነት ነው፡፡››

‹‹ኡፍ! ለምን አይገባችሁም፤ እሷን እኮ ነፍሴ ነው ያፈቀራት፡፡በቃ ህልሜ ሆናለች፣ሀይማኖቴ አርጌያታለሁ፣ፈፅሞ ተስፋ አልቆርጥም፣ልረሳትም አልችልም፡፡››

‹‹ቆይ በየጋዜጣው የታተሙላትን ልብወለዶች ሠብስቤ እንድታሳትም አግባባታለሁ ያልከውስ?››

‹‹እባክህ እምቢ አለች፡፡››

‹‹እንዴት .. ? ተው ይህቺ ልጅ መንፈስ ሳትሆን አትቀርም!››

‹‹ይሆናል .. !ማሳተም ከፈለግኩ ግን ሙሉ ውክልና እንደምትልክልኝ ነግራኛለች፡፡››

‹‹ያንተ ያለህ!›› የሠሎሞን መገረም ጨመረ፡፡

‹‹እሺ መፅሐፍ ታተመ እንበል፤የሚገኘው ገቢስ?

‹‹በእኔ ስም ባንክ ቤት እንዳስቀምጠው አሳስባኛለች፡፡››

‹‹በል በል ይሄንን የእብደት ወሬህን አቁምልኝ... ልዝናናበት፤ለራሴ በየውብዳር ጭቅጭቅ አዕምሮዬ ተወጥሮ ነው የመጣሁት፤ሌላ አዕምሮ የሚወጥር ነገር አትጨምርብኝ፤ይልቅ ትንግርትህን ጥራትና ዘና ታርገን፡፡››

ይቀጥላል

ቤተሰቦች #የዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ #እያደረጋቹ  ለማድረግ የሚጠይቀው ውስጣዊ ቅንነትን፣ለሰዎች መልካም ማሰብን፣ደግነትን ብቻ ነው።
አሁን #ዩቲዩቡ 128 subscribers አሉት ይሄ ቻናል ከ100,000 በላይ አባላት አሉት ከነዚህ ውስጥ 10 ሰው subscribe ያደርጋል ብዬ እጠብቃለው በጣም ትንሽ ነው ማድረግ ትችላላችሁ በቅድምያ
ስለመልካምነታችሁ ከልብ አመሰግናለሁ።
Sebscribe

YouTube link
https://www.youtube.com/@atronose
12.7K viewsአትሮኖስ, 18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-29 21:35:54 ‹‹እኔ ይሄኛው ትክክለኛ፤ ያኛው ደግሞ በስህተት የተሞላ ነው ልልህ አልችልም፡፡ ሀይማኖት የምርምር ሳይሆን የእምነት ጉዳይ ነው፡፡ መቼም ማስተርስህን የሠራኸው በፍልስፍና እንደመሆኑ መጠን የአብዛኞቹን ሃይማኖቶች ፍልስፍናዊ ፅንሰ ሀሳባቸውን የመመርመር ዕድሉ እንደነበረህ እገምታለሁ፤ ስለዚህ ከዛ በመነሳት አንዱን መምረጥ የሚያቅትህ አይመስለኝም፡፡››

ሁሴን ፊቱ የተቀመጠውን የውስኪ ብርጭቆ በማንሳት አንዴ ጠቀም አድርጎ ከተጎነጨለት በኃላ መልስ መስጠት ቀጠለ፡፡...

ይቀጥላል

እንደገና ጭቅጭቄን ልጀምር ነው እሱ ምንድነው  #የዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ #አድርጉ #የሚል #ነው ለማድረግ የሚጠይቀው ውስጣዊ ቅንነትን፣ለሰዎች መልካም ማሰብን፣ደግነትን ብቻ ነው።
አሁን #ዩቲዩቡ 119 subscribers አሉት ይሄ ቻናል ከ100,000 በላይ አባላት አሉት ከነዚህ ውስጥ 10 ሰው subscribe ያደርጋል ብዬ እጠብቃለው በጣም ትንሽ ነው ማድረግ ትችላላችሁ በቅድምያ
ስለመልካምነታችሁ ከልብ አመሰግናለሁ።
Sebscribe

YouTube link
https://www.youtube.com/@atronose
12.9K viewsአትሮኖስ, 18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-06 12:38:53 አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _12
አሮሯ ከመድረክ ወርዳ ወደውስጥ ስትገባ እሱ እዛው ወለሉ ላይ  እንደተንበረከከ ነበር። ከኃላዋ በአንድ ሜትር ርቀት ሶስቱም  የአሮሯ ሴት ጋርዶቾ እየተከተሏት ነው።ውስጧ የፈለገው ከመድረክ ወርዶ ወደውስጥ መግባት አልነበረም። የፈለገችው ወደፊት ለፊት ሄዳ ከመድረኩ ወርዳ ተንበርክኮ ዘፈኗን በፍቅርና በክብር ሲያዳምጥላት የነበረውን አፍቃሪዎን ከተንበረከከበት ማንሳትና ማቀፍ ነበር የተመኘችው። አዎ በእሷ ምክንያት ለሶስት አመት ምን ያህል እንደተሠቃየና ምንስ እንዳጣ እንዲነግራት ትፈልግ ነበር ።የሚሰማውን ጥልቅ የፍቅር ስሜት እንዲነግራት እና  ስሜቱን እንዲያጋባባት ትፈልጋለች።ግን  ያሰበችውን ማድረግ አልቻለችም።እንደዛ ብታደርግ እሱን ይበልጥ ማጋለጥና ዳግመኛ አደጋ ላይ መጣል  እንደሆነ ስላወቀች ቀጥታ ስሜቷን ጨቁና ወደ ውስጥ ገባች ።ጠባቂዎቾ ውጭ የበራፍን ግራና ቀኝ ይዘው ሲቆሙ እሷ አልፋ ወደውስጥ ገባችና በራፋን ከውስጥ ቆልፋ ቀጥታ ወደመቀመጫዋ ሄዳ ተቀመጠች።ከፊት ለፊት ያለው ግዙፍ መስታወት ላይ አፈጠጠች።ከተቀመጠችበት መልሳ ተነሳች...መስታወቱን በአፋንጨዋ የመንካት ያህል ተጠጋችው። ከመስታወቱ  ባሻገር  ያለው የገዛ ምስሏ  አፍጥጦባታል።"እኔ ግን የትኛው ነኝ ? ስትል አሰበች።"እኔ መስታወት ውስጥ ያለሁት ነኝ ወይስ እዚህ የቆምኩት?። የእኔ ምስል ከመስታወቱ ባሻገር  ያለው እኔ ደግሞ ከመስታወቱ ወዲ ያለውት  መሆኔን በምን ማረጋገጥ እችላለሁ ?ሁለቱም አሁን ፊት ለፊት የተፋጠጡት የማይዳሰሱ ብዠታዋች  ቢሆኑስ ..?" እያብሰለሠለች ባለችው ዝብርቅርቅ ሀሳብ ምክንያት እራሷን አመማት"የትኛው ነው  ግን የተመመው።ከውጭ ያለው እኔነቴ ወይስ መስታወት ውስጥ ያለው ? "መልሱን  ከውስጧ ለማግኘት  እያማጠች ባለችበት ቅፅበት ከፍተኛ የበራፍ መንኳኳት ድምፁ ተሠማ... ወደቀልቧ እንደመመለስ አለችና በጥድፊያ  ሄዳ ከፈተች።አባቷ ነው።ጡጦውን እንደቀሙት ህፃን ለንቦጩን ጥሎ  በንዴት ተገትሮል።
እጇን አፈፍ አደረጋትና እየጎተተ በጓሮ መውጫ በር ይዞት መሄድ ጀመረ..."ምን ነካህ?ቦርሳዬን እንኳን  ልያዝ እንጂ"
"ቀጥይ ...ልጆቹ ያመጡልሻል።"አለና ለአንደኛዋ  ጋርድ እንድታመጣላት ነገራት። ቀጥታ ወስዶ የጓሮ መውጫ በራፍ አካባቢ የቆመችው የገዛ መኪና ውስጥ ነው  ይዞት የገባው።
"የተፈጠረ ነገር አለ እንዴ?ይህ ሁሉ መዋከብና ግር ግር ምንድነው?"ጠየቀችው።
መልስ ሊመልስላት ሲዘጋጅ ጠባቂዋ በታዘዘችው መሠረት ቦርሳዋን ይዛ መጣችና  አቀበለቻት።እና ወደ አባቷ  ዞራ"ጌታዬ እንዴት እናርግ ..?ከኋላ እንከተላችሁ?"ስትል ጠየቀችው።
"ሽጉጥሽን ስጪኝ"አላት።ያለምንም ማቅማማት ከወገባ መዥርጣ አውጥታ አቀበለችው..
ተቀብሎ ፊት ለፊት አስቀመጠና"በቃ እዚሁ ሁኑ...እና  ቅድም የነገርኳችሁን ፈፅሙ"የሚል ትዕዛዝ አስተላለፈ።
"እሺ ጌታዬ ታዛዥ ነን" አለችና ወደኃላ ዞራ ቀሪ ሁለት ጓደኞችን አስከትላ ወደክለብ ተመለሱ።
አሮሯ ነፍስን የሚያቀዘቅዝ አይነት ጥርጣሬ ገባት"አባዬ ምንድነው ያዘዝካቸው?።"ለማረጋገጥ ጠየቀችው።
"አይመለከትሽም"
"ይመለከተኛል እንጂ...ነግሬሀለው... ልጅን ጫፉን እንዳትነኩት"
"እቤት ድረስ መጥቶ እጅሽን ይዞ እስኪወስድሽ ነው ዝም ምለው...?ይሄ  ልጅ ወይ እብድ ነው ወይም ደግሞ ደደብ ነው ።የሶስት አመት እስር ያላስተማረው ሌላ  ሞት ካልሆነ ምን ያስተምረዋል?"
"ሳፈቅርህ... ያልከኝን ሁሉ አደርጋለሁ... እንዳትነካው?"በመንሰፍሠፍ ተማፀነችው።
በማቅማማት ስሜት አይኖቹን አንዴ የሚነዳው መኪና መሪ ላይ ደግሞም እየሸረፈ እሷን መመልከት ጀመረ ተንጠራራችና ጉንጩን ሳመችውና "ስወድህ ... አሁኑኑ መኪናውን አቁምና ደውልላቸው...በፈጠረህ ምንም ነገር እንዳያደርጉት ንገራቸው"እንባ ባቀረሩ አይኖቾ እየተለማመጠች ለመነችው። እንደመርገብ አለና  መኪናውን መንዳቱን ሳያቆም  ስልኩን አወጣና ደወለ"ሄሎ ዝም ብላቹ ተከታተሉት... ሳላዛችሁ ምንም ነገር  አታድርጉት" ብሎ መልስ ሳይጠብቅ ስልኩን ዘጋው።
"መከታተሉስ ለምን አስፈለገ?"ስትል ጠየቀችው።
"አንቺ ደግሞ ሁሉ ነገር እኔ ያልኩት ብቻ ይሁን አትበያ"አለና ኮስተር አለባት ።ከዛ ስልኩን በድጋሚ ደወለ..ሲነሳ"ሄሎ ራሄል  አንመጣም.. ስራ ስለሚያስቆየን እዚሁ ነው የምናድረው"አለና እቤት ላለችው ሰራተኛ በመንገር ስልኩን ዘጋውና ወደቦታው መለሰው።
"እንዴ ወደቤት አንሄድም እንዴ?"በገረሜታ ጠየቀችው።
"አይ እንዲህ አናደሽኝማ ወደቤት አንሄድም ..ወደገነታችን ሄደን ለሊቱን ሙሉ ስትክሺኝ ታድሪያለሽ"
"ቆይ የልጅ መምጣት የእኔ ጥፋት ነው እንዴ?ደግሞ ቢመጣስ ምን አደረገ ?ለጠቅላላ ህዝብ ክፍት የሆነ ናይት ክለብ ነው የመጣው።ማንንም አልነካም። ማንንም አላስቀየመም.."
"ይሄ እኮ ነው የሚያበሳጨኝ...በጣም እያሰብሽው ነው ።እለት በእለት ስለእሱ ያለሽ መጨነቅ እያደገ ነው..ይሄ ደግሞ እሱን ለማጥፋትና ለመግደል ያለኝን ረሀብ እንዲጨምር እያደረገ ነው።በቅርብ ገዳይ ታደርጊኛለሽ"ሲል የሚሰማውን በግልፅ ነገራት።
"አባዬ ይሄ የእኔ እና ያንተ ነገር እኮ አንድ ቀን የሆነ ቦታ ማብቃቱ አይቀርም። "
"ለምንድነው የሚያበቃው?"በገረሜታ ጠየቃት።
ልታስረዳው ሞከረች"ባትወልደኝም እኳ ከልጅነቴ ጀምሮ ያሳደከኝ አባቴ ነህ...የሟች እናቴ ባል ነበርክ..የምወዳት ታናሽ እህቴ የስጋ አባት ነህ...እስከአሁን በጭለማ ውስጥ የዳከርነው ይበቃል..የሆነ ቦታ ላይ ይብቃ ማለት አለብን።እንደአለመታደል ሆኖ ታውቃለህ እኔም አፈቅርሀለው..ግን ምንም ማድረግ አንችልም.."
በዚህ ጊዜ እቤታቸው ደርሰው ነበር።ይሄ ቢላ ቤት በእሷ ስም የተገዛ ከሁለቱ በስተቀር ማንም የቤተሠብ አባል የማያውቀው  አልፎ አልፎ ሹልክ እያሉ በመምጣት የሚያድሩበትና የብቻቸውን ጊዜ የሚያሳልፉበት ነው።
ዘበኛው ከፈተላቸውና መኪናዋን ወደውስጥ አስገብ።ሳሎን እንደገብ ነበር ጎትቶ ወለል ላይ የጣላት። ከዛ የለበሰችውን ቀሚስ ከሰር ያዘና ተረተረው።በተለሳለሠ ድምፅ"ቀስ በል እንጂ..የእኔ ፍቅር"አለችው ።አልሰማትም ...ፓንቷን  በሁለት እጆቹ  ግራና ቀኝ ያዘና ጎትቶ በማውለቅ ወለሉ ላይ  ወረወረው እርቃኖን ቀረች።የራሱን ልብስ በችኮላ እያወለቀ መወርወር ጀመረ....


ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
2.9K viewsTsiyon Beyene, 09:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 21:00:26 አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _11
እለቱ እሁድ ነው። አሮራ  ናይት ክለብ በስራ ላይ ነው ያለችው።  ይሄ መድረክ ለእሷ የፀሎት ስፋራዋ ነው።ጭንቀቷን የምትረሳበት ከሀሳቧ እፎይ ምትልበት  ፍፁም የእረፍት ስፍራዋ ነው።ሙዚቃ ባይኖርና እሷም ሙዚቀኛ ባትሆን ይሄን ከባድና የተወሳሰበ ህይወቷን እንዴት አድርጋ መቋቋም እንደምትችል ስታስብ ይገርማታል።ሰዓቱ ከምሽቱ  አራት ሰዓት አካባቢ ነው።ለሁለተኛ ዙር ወደመድረክ  የወጣችው።አንድ በቅርብ የለቀቀችውን ነጠላ ሙዚቃ ከዘፈነች በኃላ በሁለተኛ ላይ የታዋቂና ተወዳጆን የአስቴር አወቀን" ጠይም ዘለግ ያለ..."እያለች መዝፈን ስትጀምር ከታዳሚው መካከል  ተነስቶ እሷ ወደምትዘፍንበት መድረክ አካባቢ ቀረበና  ያለምንም ይሉኝታ ወለሉ  ላይ ተንበርክኮ ሙዚቃውን በተመስጧ ማዳመጥ ጀመረ...የታዳሚው ቀልብ የእሷን ዘፈን በማዳመጥና የሠውዬውን ሁኔታ በመከታተል መሀል መበታተኑ ያስታውቃል...አይደለም ታዳሚው እራሷ አሮራ  መንፈሷ እየተሸራረፈባት ነው።ሠውዬውን አውቃዋለች።መንግስቱ ነው።በእሷ ጦስ አባቷ ለሶስት አመት ያሳሰረው እና ሰሞኑን መፈታቱን የሠማችው አፍቃሪዋ።

መንግስቱ በተንበረከከበት ሆኖ አይኖቹን ጨፍኖ በጆሮው የሚያፈቅራትን ልጅ    ጥዑም ሙዚቃ እያዳመጠ በምናብ ለመጀመሪያ ጊዜ የዛሬ አራት አመት  እዚሁ ቤት እሷን ያየበትንና በእሷ የተነደፈበትን ትዕይንት በምናብ በምስለት መቃኘት  ቀጠለ።

በወቅቱ መንግስቱ  ከወጣትና ሀብታም ጓደኞቹ ጋር ለመዝናናት ሲመጣ  እሷ ደግሞ መድረክ ላይ ሆና ስትዘፍን ነው የተመለከታት ።መጀመሪያ ድምፆ ነው በጆሮው ሰርስሮ የገባው። ያን ያህል የሙዚቃ አፍቃሪ አይደለም።ግን ድንዝዝ ነው ያለው ።ወደመድረኩ  ፊቱን አዞረና  ተመለከታት። ሸንቀጥ እና ዘለግ ያለች ወጣት ሴት ነች ..ደብዛዛውና ቀለም የበዛበት የቤቱ መብራት ፊቷ ላይ ቦግ ብልጭ ስለሚልባአት  በጥራት አልታየችውም። ዘፈኗን ጨርሳ ከመድረክ ወረደችና ወደጀርባ በሚወስደው በራፍ ገባችና ተሠወረች ...እሷ በወጣችበት በር ሌላ ወንድ ዘፋኝ መጥቶ ተካት።
"ማን ነች ልጅቷ?"ሲል ጓደኞቹን ጠየቀ...ማንም አያውቃትም"አንደኛው ጓደኛው ቤተኛ ስለነበረ የናይት ክለብን ስራ-አስኪያጅ አስጠራው።ሠውዬው እነሱ ጋር እንደደረሰ
መንግስቱም"አሁን ዘፍና የወረደችው ዘፋኛኝ  ማን ነች?"ሲል ጠየቀው።
"አሮሯ ትባላለች  ...ምነው ዘፈኗ አልተመቻችሁም እንዴ?"
"አይ በጣም ጥኡም ድምፅ አላት...ልተዋወቃትና አድናቆቴን ቀጥታ ልገልፅላት እፈልጋለሁ"አለው።
በንግግሩ  ጓደኞቹ  ግራ ተገብ..እንዲህ አይነት የመንሰፍሰፍ አመል አልነበረውም ...ስራ-አስካጅ አንገራገረ"ያው ልትዘፍን ስትመጣ ነው ማግኘት የሚቻለው"
ጓደኛው ጣልቃ ገባ"አረ ተው ...ውለታ ዋልልን እንጂ" በማለት ሲጫነው"
"በል እስኪ ና ከተቻለ እንሞክር" አለና  መንግስቱን እየመራ ወሰደው።ወደውስጥ ገብተው ከናይት ክለብ  ጋር የተያያዝ ከጀርባ ያለ ክፍል ሲደርሱ ቆሙና"ያ በራፉ ላይ ያለው ጠባቂዋ ነው..እኔ ቀርበውና በወሬ አዘናጋዋለሁ.. ከዛ አንተ ቀስ ብለህ ግባና አግኛት...ግን ችግር ከተፈጠረ አደራ ስሜን እንዳታነሳ..ቀጥታ ነው የምባረረው."ሲል ስጋቱን ነገረው።በዛ ተስማሙና ስራአስኪያጅ ጋርድን በወሬ ሲያዘናጋለት እሱ የጠቆመውን ክፍል ገፋ አድርጎ ገባና መልሶ ዘጋው።
...ደረቅ ወንበር ላይ ቁጭ ብላለች..ፊት ለፊቷ አነስተኛ ጠረጴዛ አለ...ጠረጴዛው ላይ በዛ ያሉ ኮስሞቲኮች ተኮልኩለዋል።ፊት ለፊት ደግሞ ትልቅ መስታወት አለ...እዛ መስታወት ላይ  አይኖቾን ሰክታ  በሀሳብ ጠፋታለች።  ከጉንጮቾ ላይ እንባ እየረገፈ ነው።
ኩሏ ለቆ ከእንባዋ ጋር ተደባልቆ ፊቷን የህፃናት የስዕል ደብተር አስመስሏታል።እንደዛም ሆኖ ግን ከድምፆ የሚስተካከል አስደንጋጭ ውበት ነበራት።
ቀስ ብሎ ወደውስጥ ዘለቀ ...አላስተዋለችውም ...ዝም ብሎ ከጎኗ ካለ ወንበር ላይ በፀጥታ ተቀመጠ...ለአሰር ደቂቃ ከነበረችበት ሀዘን ያጠቆረው ምስጠት ውስጥ ልትወጣ አልቻለችም..
ከዛ ግን ድንገት"በጣም ይሸተኛል..መጥፎ የሚሰነፍጥ ሽታ አንጀቴ ውስጥ ገብቶ ይረብሸኛል...አስታውኪ አስታውኪ ሁሉ ይለኛል"አለች።
ምን እንደሚመልስላት ግራ ገባው ።የንግግሯ መነሻና መዳረሻውም ሊጨበጥለት አልቻለም።
"የእኔ እመቤት ምንድነው ሚሸትሽ ?አመመሽ እንዴ?"
"ወንዶች እንዲህ በጣም ሲጠጉኝ ያመኛል ..በዚህ አለም ላይ ብቸኛ ችግሬ ወንዶች ናቸው...."
በንግግሯ በጣም ከመደንገጡ የተነሳ ድንገት በእጆቹ ኤሌክትሪክ እንደጨበጠ ሰው ሽምቅቅ አለ። ብዙ ቆይቶ ሊያበሳጫት አልፈለገም።ከተቀመጠበት ተነስቶ ቆመና ወደኃላው ሶስት እርምጃ ተራመደ "የእኔ እመቤት ምን አይነት ስሜት ውስጥ እንዳለሽና እንዴት አይነት ጭለማ ውስጥሽን እንዳጠቆረው አላውቅም ..እኔ አመጣጤ ድምፅሽ ምን ያህል ውብ እንደሆነና የተጫወትሻቸው ሁሉም ሙዚቃዎች እንከን አልባ እንደሆኑ ልነግርሽ ነበር "
"አውቃለሁ...ድምፄም ሆነ የተጫወትኳቸው ሙዚቃዎች እንከን አልባ እንደሆኑ በደንብ አውቃለሁ...ምክንያቱም ሀዘኔን ነበር የበተንኩት... ቁስሌን ነበር  በጣቴ የቆሰቆስኩት...ምሬቴን ነበር ለፈጣሪ ያሰማሁት ...እና ታዲያ እንዴት ላያምር ይችላል ብለህ ጠበቅክ...?ለማንኛውም ሲጋራ ይዘሀል...በጣም ጠማኝ".
"አይ አልያዝኩም ግን ባር ያሉት ጎደኞቼ ውስጥ የሚያጨሱ ስላሉ ልልክልሽ እችላለሁ..."
"እባክህ ...ከአድናቆትህ በላይ የሚጠቅመኝ እሱ ነው"
"እሺ ልክልሻለሁ ...ለማንኛውም መንግስቱ እባላለሁ...ያንቺ አሮራ እንደሚባል ነግረውኛል።ሌላስ...መጠጥ ትፈልጊ ይሆ?።"
"ደስ ያለህን ላክልኝ "አለችው ።ከክፍሉ ውስጥ ሲወጣ ጋርድ ግራ ተጋባ..ፈጠን ብሎ በሩን ከፈተና ወደውስጥ ተመለከተ ሁሉ ነገር ሰላም መሆኑን ሲያይ ተንፈስ አለ።
መንግስ ቀጥታ ወደ ናይትክለብ  ተመለሰ። ከአንድ ጓደኛው አንድ ባኮ ሲጋራ ከአንድ ጠርሙስ ጎርደን ጅን ጋር በ አንድ አስተናጋጅ በኩል ላከላትና ጓደኞቹ  ተሰናብቶ ወጥቶ ወደ ቤቱ ሄደ።በጣም ነበር የረበሸችው፤እንደዛ መንፈሷ የተሠበረች  ሴት  ለዛውም ገና ጮርቃ ወጣት በህይወቱ አጋጥሞት አያቅም። የትኛው የተረገመ ወንድ ይሆን  ገና ከህይወት መነሻዋ ጋር ያለችን ውብ ሴት እንደዚህ ወልቅልቅ እንድትል ያደረጋት ...?ደህና እንቅልፍ ሳይተኛ ስለእሷ ሲያስብ ምን ሆና ይሆን በማለት መላ ምት  ሲደረድር እንቅልፍ በአይኑ ሳይዞር እንዲሁ ሲገላበጥ ነጋበት።
በእንደዚህ አይነት ሁኔታና አጋጣሚ ነበር አሮሯ እና መንግስቱ ለመጀመሪያ ቀን የተገናኙትና የተዋወቁት


ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
4.3K viewsTsiyon Beyene, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-02 19:28:13 አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _10


ስለናይት ክለቡ የሆነ ነገር በማወቋ ደስ አለው‹‹በቅርብ ገብተሸ ተውቂያለሽ……?አይ አዲሱ ፍሬንዴ ብዙም እደዛ አይነት ነገር ስለማይመቸው ስድስት ወር አለፈኝ መሰለኝ፡፡››
‹‹ከሶስት አመት በፊት አዚህ እያለሁ እዛ ሚሰራ የሆነ ሰው አውቅ ነበር….አሁን ይኑር አይኑር ለማጣራት ፈልጌ ነው››
‹‹ምን ?ስልክ ቁጥሩን አታውቅም….?››
‹‹እንደዛም ቢሆን ቀላል ነበር….ምንም የማገኝበት መንገድ የለም››
‹‹ምንድነው የሚሰራው?››
‹‹ሴት ነች…ዘፋኝ ነች››
‹‹ዘፋኝ…ታዲያ ምን ችግር አለው ..ዘፋኝ ከሆነችማ በቀላሉ ማጣራት እንችላለን፡፡ማነች እኔ እራሴ አውቃት ይሆናል?››
‹‹አሮራ ትባላለች፡፡››
ከፊቶቷመቀያየር መደነቋ እያስታወቀባት‹‹ጥቁሯን አልማዝ ነው ምትፈልገው?››አለችው፡፡
‹‹አዎ ጥቁር አልማዝ አላችኋት?››

‹‹አዎ ….ከዋናው ስሟ እኩል በዚህ ሰም ትታወቃለች….የማትበላዋ ወፍም ይሏታል..ብቻ ስመ ቡዙ ነች…ምን ጓደኛህ ነበረች?››
‹‹አይ እንዲሁ ነበር የመውቃት…አሁን  ለሆነ ጉዳይ ፈልጌያት ነው ››
‹‹ታዲያ እሷ እኮ ምን አልባት ለስራ ወደውጭ ሀገረ ካልሄደች ትገኛለች…እቤቱ እኮ የአባቷ ነው..እሱን አታውቅም?››
‹‹አውቃለሁ….ያው እንዳልሽው ሀገር ውስጥ ካልሆነች ብዬ ነው፡፡››
እስን እናጣራለን……ግን ሀለቃ እየሰራች ቢሆን እንኳን ከእሷ  ተገናኝቶ ለመነጋገር ነገሮች ቀላል አይሆኑልህም..ዘወተር በሶስትና አራት አውሬ በሆኑ ጋርዶች እንደተጠበቀች ነው፡ኢትዬጳያ ውስጥ ከእሷ በላይ ጥበቃ የሚደረግለት ሌላ ሰው እኔ የማውቀው የለም ምን አልባት ጠቅላይ ሚኒስቴር ካሆነ በስተቀር››
‹‹አውቃለሁ… ብቻ እሷ እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥ ትኑር እንጂ የማግኘቱን ዘዴ  አስብበታለሁ››
‹‹ስለዚህ አሁን መኖር አለመኖሯን ብቻ ነው የምታጣራው፡፡››
‹‹አዎ፡፡››ደረሱን ናይት ክለቡ ፊት ለፊት መኪናዋን አቆመች …‹‹ሀለቃ ሴት ስለሆንኩ ከአንተ ይልቅ እኔ እሻላለሁ ዘበኞቹን አሳስቄ የሆነ መረጃ ነድፌያቸው መጣሁ ››ብላ እዛው መኪናው ውስጥ ጥላው ገቢናውን ከፍታ ወረደች…ከእስር ቤት ከዋጣ ሁለት ቀን ሆኖታል ፡፡በዚህ ሁለት ቀን ካገኛቻውና ከናገራቸው ሰዎች ሁሉ ቀልቡ ሙሉ በሙሉ የተቀበላት ይህቺን ልጅ ነው፡፡‹‹ግልፅ..የሰውን ስሜት በፍጥነት የምትረዳ ድርዬ መሳይ ግን ስርዓት ያላት ሴት ነች›› አለ፡፡ከ15 ደቂቃ በሃላ ተመልሳ መጣችና  ገቢናዋን ከፍታ ገብታ ቁጭ አለች፡፡
‹‹እሺ… ምን አገኘሽ?›› አላት ፡፡
‹‹አለች፡፡በሳምንት ሁለት ቀን ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ እና እሮብ ለሀሙስ አጥቢያ ነው የምትሰራው አሉ፡፡››
‹‹ዛሬ ምንድነው ቀኑ፡፡››
‹‹ሀሙስ››
‹‹በስመ አብ ….ገና ቅዳሜ ድረስ..››
ትእግስት  ተደነጋገራት…‹‹ይሄ ሰውዬ ለምን አይነት ለጉዳይ ነው የፈለጋት ?›› ስትል በውስጧ አሰበች፡፡
‹‹..ጉዳዩ በጣም አስቸኮይ ነው እንዴ?››
‹‹አይ ቅዳሜ አይደል…እስከዛ ቢቆይ አችግር የለውም››አለ፡፡
አይኗን ሳለይ ለሶስት አመት መጠበቅ የቻልኩ ሰውዬ ለሶስት ቀን መጠበቅ ትዕግስት እንዴት አጣለሁ..?››ሲል እራሱን ገሰፀ..እዛ እስር ቤት ሆኖ ቴሌቭዝን በማየት ሱስ እሱን የሚስተካከለው የለም ነበር….ሰው ሁሉ ከሚያወራው ወሬ ወይም ከሚተላለፈው ፕሮግራም ስለሚማርኩት ይመስለዋል..እሱ ግን ምን አልባት የዘፈን ምርጫቸውን እሷን ያደርጋሉ በሚል ጉግት ነው፡፡ስትዘፍን ለመመልከት… ድምፆን ለመስማት ነው፡፡ብዙ ጠብቆ በሳምንት አንድ ቀን እንኳን ቢሰካለት ለእሱ ፋሲካው ነው፡፡


ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
2.7K viewsTsiyon Beyene, 16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 19:48:15 አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _9

እንዴት አድርጎ የዘመናት ብስጭቱንና ቂሙን ሊበቀል እንደሚችል ግን የተሰበበትና የተጠና እቅድ የለውም….እንደዚህ ሎቶሪ በመሰለ ቅፅበታዊ አጋጣሚ ሰውዬው ጠቅላላ በህይወቱ ሙሉ የለፋበትንና የደከመበት ሀብት ሁሉ እጁ  እንደሚገባ  እንዴት ሊያስብ ችሎ ነው.እቅድ ሚኖረው..ግን ደግሞ በጣም በቂ ጊዜ አለው…አመታት ንብረቱም የሰውዬው ቤቱም ሆነ ሚስቱ በእጁ ይቆያል..እናም ዘና ብለ ምን ማድረግ እንዳለበት ያስብበታል፡፡
‹‹ምነው ተከዝክ?››
‹‹አይ ብቻ ይሄን ሁሉ ኃላፊነት ለእኔ መስጠትህ አልተዋጠልኝም….ሌላ አማራጭ ካለህ ብታስበበት ደስ ይለኛል?››አለው ..በውስጡ ስለሆነው ነገር በመደሰት ፡፡
‹‹አይ ይሄ ለአማራጭ የሚቀርብ አይደለም…ለንብረቶቼ አስተዳዳሪ የምቀጥር ቢሆን የብዙ ሰው ሲቪ ሰብስቤ
ልምዳቸውንን ፀባያቸውን በማጥተናት ከዚህ ያኛው ይሻላል ብዬ ማማረጥ እችል ነበር፡፡አሁን ግን እንደራሴ የማምነውን ስጋዬ እና እንደልጄ ለሆነ ሰው የእኔ ሆነውን ነገር ሁሉ በአደራ መስጠት ነው የምፈልገው፡ይሄ ደግሞ ውጭ ለምሄድባቸው አምስት አመታት ብቻ ሳይሆን እስከወዲያኛው እጣችን የተሳሰረ ነው፡፡የእኛንም ሆነ የመጪ ቤተሰቦቻችንን ዕጣ ፋንታ አብረን እንገነባለን፡፡የእኔ ልጆችም ሆኑ አንተ የምታፈቅራትን ልጅ አግብተህ የምትወልዳቸው ልጆች ነጋቸው ብሩህ እንዲሆን አብረን እንለፋለን፡፡ ደግሞም እናሳካዋለን ፡፡››
‹‹እሺ ካልክ…አሁን ግን የሆነ ቦታ ደርሼ ለመምጣት ፈልጌ ነበር››
ፈገግ ብሎ‹የት ልጅቷ ጋር?››
አቀረቀረ..
‹‹እሺ ጥሩ …ግን መጀመሪያ ትዕግስትን ልጥራና ገስት ሀውሱን አዙራ ታሳይህ..ከዛ የፈለክበት መሄድ ትችላለህ…ለመሆኑ መኪና መንዳት ትችላለህ?››
‹‹አዎ ግን መንጃ ፍቃዴ አልታደሰም››
‹‹እሺ ለጊዜው የምትፈልገው ቦታ ትዕግስት ይዛህ ትሂድ…እና እንዳሳደስክ የራስህ መኪና ተዘጋጅቷልሀል፡፡
‹‹አጎቴ በጣም ነው የማመሰግነው…..አሰቸገርኩህ››
‹‹አይ በቤተሰብ መካከል አስቸገርኩህ አስቸገርከኝ የሚሉ ቃላት ጥቅም ላይ አይውሉም››አለና መጥሪያውን አንጫረረ..ከ5 ደቅቃ በኃላ አንድ ልጅ እግር ወንዳወንድ አቋም ያላት ልጅ በራፉን አልፋ ገባች፡፡
‹‹እንዴት ናችሁ ጋሼ ፈለከኝ?››
‹‹አዎ ፈልጌሽ ነው..ተዋወቂ የነገርኩሽ ትልቁ ልጄ እሱ ነው፡፡››
ልክ ከዚህ በፊት እንደምተዋወቁና ለረጅም ጊዜ ሳይተያዩ እንደቆዩ ወዳጆች  እሮጣ ሄዳ ተጠመጠመችበት፡፡
‹‹በይ እንግዲህ ከዚህች ሰዓት ጀመሮ ሀለቃሽ እኔ ሳልሆን እሱ ነው….ለእኔ ትታዢ እንደነበረው ከቻልሽ ከዛም በላይ ለእሱ ታዘዢ ..እንደነገርኩሽ ለስራው አዲስ ስለሆነ ሁሉንም ነገር በትዕግስት አሳይው.. .እስከፈለገሽ ጊዜ ድረስ እረዳቱ ሆነሽ ትቀጥያለሽ..በይ አሁን ግቢውን በማስጎብኘት ጀመሩ..››
‹‹እሺ ጋሼ የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ..እንሂድ ሀለቃ›› አለች..
ያለ ምንም ንግግር  መቀመጫውን ለቀቀና በዝምታ ተከተላት፡፡
ምዕራፍ-
‹‹ክፍሎቹን ሆነ ግቢውን እንዲሁም ዋና ዋና ነገሮች ለመጎብኘት ከ40 ደቂቃ በላይ ነው የወሰደባቸው…፡፡በወቅቱ ስራ ላይ ካሉ ሰራተኞች ጋርም አስተዋቀችው..እንደጨረሱ››መንጃ ፍቃዴ  ስላልታደሰ መኪና መንዳት አልችልም…የሆነ ቦታ ትወስጂኛለሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹በደስታ ነዋ፡፡››አለችና ገስት ሀውሱ መኪና ማቆሚያ ወደ ቆመችውን የድርጅቱን መኪና ይዛው ሄደች… ገቢና ከጎና አስቀምጣ መኪናውን አስነሳችና  ግቢውን ለቀው ወጡ፡፡‹‹ወደየት ልንዳው?››
‹‹22-ቨክቶሪያ ናይት ክለብ….ታውቂዋለሽ?››


ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
4.7K viewsTsiyon Beyene, 16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-29 23:31:54 አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _8

‹‹የሚገርም ነው…ይህቺን ልጅንማ ከመሄዴ በፊት ታስተዋውቀኛለህ?››
‹‹የት ነው የምትሄደው….?››
‹‹ይሄውልህ እዚህ ሀገር ውስጥ የምቆው ግፋ ቢል ለ15 ቀን ብቻ ነው፡፡ከዛ ወደካናዳ እሄዳለሁ፡፡››
‹‹ምነው ለእረፍት ነው?››
‹‹አይ ለስራ ነው….ከአንድ አለማ አቀፍ የመአድን አምራች ካምፓኒ ጋር የተለየ አይነት የስራ እድል አግኝቼያለሁ…የዚህ ድርጅት ዋና መቀመጫው ከናዳ ነው፡፡ግን ደቡብ አሜሪካ ሀገሮች ውስጥ ብዙ የማዕድን ማውጫ ቦታዎች አሉት….እኔ ከዛ ድርጅት ጋር ቢያንስ ለቀጣዬቹ 5 አመታት አብሬ ለመስራት ነው የምሄደው…ምን አልባትም በአመት ሁለቴ ወይም አንዴ ብቻ ነው መጥቼ ላያችሁ የምችለው፡፡ይሄ ስራ የሁላችንንም ህይወት ነው ከመሰረቱ የሚቀይረው..እና በዚህ የስኬት መንገድ ከጎኔ እንድትሆን እፈልጋለሁ››…
‹‹ቤተሰቦችህን ይዘህ ነው የምትሄደው?››
‹‹አይ ማለቴ ልጆቹ የተሻለ ትምህርት እንዲማሩ ሰለምፈልግ ከሶስት ወር በኃላ ተመልሼ መጥቼ ወስዳቸዋለሁ… በተረፈ ሁሉም ነገር እንዳለ ነው የሚቀጥለው፡፡እዚህ ያለውን ንብረቴንም ሆነ ቤተሰቤን እንድትቆጣጠርልኝ ፈልጋለሁ..ይሄ ገስት ሀውስ በወር እስክ አንድ ሚሊዬን ብር የተጣራ ገቢ ያስገባል….በተጨማሪ ሌሎች ተያያዥ ቢዝነሶች አሉ..እነዛን ሁሉ በአንተ ስር ይሆናሉ…ከአምስት አመት በኃላ ደግሞ ጠቅልዬ ስመለስ በጥናት ላይ የተመሰረተ አንድ ግዙፍ ከምፓኒ እንከፍትና በጋራ እናስተዳድራለን፡፡አንተ የወንድሜ ልጅ ነህ …ያ ማለት ደግሞ ልጄ ነህ ማለት ነው፡፡››
‹‹አጎቴ ሀሳብ ደስ የሚል ነው..ግን እኔ በህይወቴ ተቀጥሮ ከመስራት ወጭ የራሴን አንድ የሰፈር ሱቅ እንኳና ከፍቼ አስተዳድሬ አላውቅም …ስለገስት ሀውስም ሆነ ስለሌላ ቢዝነስ ምነም የማውቀው ነገር የለኝም››
‹‹አውቃለሁ…ያ ብዙም ሊያስጨንቅህ አይገባም…ሁሉን ነገር ያሚያስረዱህና በደንብ እስክትለምድ ድረስ እንደረዳት ሆኖ የምታግዝህ አንድ ጥሩ ልጅ አለች….አንተ በቃኝ ብለህ እስክታሰናብታት ድረስ ረዳትህ ሆና ትሰራለች፡፡ይሄ ደግሞ የትርፍና የኪሳራ ጉዳይ አይደለም…ቤተሰበን የመሰብሰብ ጉዳይ ነው….ይሄ የራስህ ንብረት ነው..ከሰርክም አተረፍክም የራስህው ነው. ምርጫ ስለሌለህ ፈጣን ተማሪ ለመሆን መጣር ብቻ ነው የሚያዋጣህ፡እስከምሄድ ደግሞ እኔም አለው ዋና ዋና ነገሮችን አሳይሀለው››
‹‹ግን አጎቴ ባለቤትህ ከአንተ ጋር የማትሄድ ከሆነ ለምን ሀላፊነቱን ለእሷ አትሰጥም ነበር..እሷስ ብትሆን ንብረቷ በሌላ ሰው ቁጥጥር ስር ሲተዳደር ደስ ይላት ይመስልሀል››
ስለእሷ ምንም አታስብ፡፡ ንብረቷ በሌላ ሰው ቁጥጥር ስር ሳይሆነ በወንድሜ ልጅ ቁጥጥር ስር ነው የገባው…በዚህ መስማማት ግዴታዋ ነው፡፡በነገራችን ላይ ይሄንን ገስት ሀውስ ላይም ሆነ ጠቅላላ ንብረቴ ላይ በዚህ ይግባ በዚህ ይውጠ ብህ እንደምትወስን ሁሉ እሷ ላይም ያለህ ስልጣን እንደዛው ነው ሚሆነው….አንተ ያልፈቀድክበት ቦታ መሄድ አትችልም፤ አንተ ማታውቀውን ነገር ማድረግ አትችለም…ይሄንን ከመሄዴ በፊት ሁለታችሁም ባላችሁበት እንግራችኋላው፡፡
የሰውዬው ሁኔታና ጠቅላላ እቅዱ ሊጨበጥለት እልቻለም…፡፡‹‹ምን ያህል እንደምጠላው….ለአባቴ ሞት ለአባቴ የአመታት ስቃይና ህመም እሱን ተጠያቂ ሳደርግና ስረግመው እንደኖርኩ ቢያውቅ እንዲህ በድፍረት ንብረቱንም ሚስቱንም አሳልፎ አይሰጠኝም ነበር››ሲል አሰበ ፡፡

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
5.0K viewsTsiyon Beyene, 20:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-28 05:36:00 አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _7
‹‹እንግዲህ ይሄ የእኛ ገስት ሀውስ ነው፡፡በኃላ ልጀቹ ሁሉንም ክፍልም ሆነ  አጠቃይ ግቢውን እያዞሩ ያሳዩሀል…አሁን ግን እናውራ፡፡››
በሰማው ነገር ስለተደነቀ‹‹አሀ ያንተ ገስትሀውስ ነው ማለት ነው?››ሲል መልሶ ጠየቀው፡፡
‹‹አዎ እኛ ነው፡፡››
‹‹ጥሩ ..ግን አንተ ስለምትፈልግው ነገር ከማውራታችን በፊት እኔ እንዲመለሱልኝ የምፈልጋቸው መአት ጥያቄዎች አሉኝ፡፡ እስከአሁንም በውስጤ አፍኜ የያዝኳቸው አመቺውን ጊዜ ስጠብቅ ነበር፡፡››
‹‹ጥሩ ብዙ ጥያቄዎች እንደሚኖሩህ እኔም እጠብቃለሁ…ሁሉንም ጥያቄዎች ለመመለስ እሞክራለሁ፡፡››
‹‹እሺ ከዚህ ሁሉ ጊዜ በኃላ ያለሁበት ቦታ እንዴት መጣህ? ለዛውም በመፈቻ ቀኔ ላይ?፡፡››
‹‹ምንመ መሰለህ የዛሬ ሰባት አመት በፊት ከአባትህ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ተለያየን …በወቅቱ ወንድሜ እናንተ አጠገብ እንድደርስ አይፈልገም ነበር፡፡ከዛ ከእናንተም ሆነ ከሌላው ቤተሰብ ተነጥዬ የራሴን ኑሮ መኖር ጀመርኩ፡፡››
‹‹እና ሲሞት ቀብሩ ላይ ሁሉ አልመጣህም…ምንም ብትቀያየሙ ብቸኛ ወንድምህ አይደል?››ሲል በጥንካሬ ሞገተው፡፡
‹‹አውቃለሁ..ግን በወቀቱ እኔ ሀገር ውስጥ አልነበርኩም፤፤ ወንድሜ ከሞተ ከሶስት አመት በኃላ ተመልሼ ስመጣ ነው መርዶውን የሰማሁት..በዛን ጊዜ  ስለአንተ እስርቤት መግባትህን ሰማሁ…ያው የነገሩኝ ደስ የማይል ነገር ስለበር ምንም ለማድረግ አልተደፋፈርኩም..››
‹‹ታዲያ አሁንስ ምን አዲስ ነገር ተገኘና ልታገኘኝ ወሰንክ?››
‹‹እንደአጋጣሚ ጠበቃህ ከነበረ ሰው ጋር የሆነ ቦታ ተገናኘንና ስለአንተ ተነሳ….የተፈጠረውን ነገር አስረዳኝ፡፡ በእውነት በጣም ነው ያዘንኩትም በራሴም ያፈርኩት….የሰው ወሬ ሰምቼ ችላ ከምልህ ቀርቤ አንተኑ ስለሁኔታው ብጠይቅህ ጥሩ ነበር…በጊዜው ልደርስልህና ልሟገትልህ ይገባ ነበር፡፡ከእድሜህ ላይ ሶስት አመት ሲባክን ዝም ብዬ በማየቴ በጣም ይቅርታ..››
‹‹አረ ነገሩ እንጂ ችግር የለውም..ደግሞ ምንም የባከነ ጊዜ የለኝም…ሶስት አመት በእስር በማሳለፌ ምንም የምቆጭበት ነገር የለም…ብዙ ነገር ተምሬበታለሁ፤ ከብዙ ድንቅ ሰዎች ጋር ተዋውቄ ብዙ የህይወት ተሞክሮ ከእነሱ አግኝቼለሁ..አዲስ ሞያ ተምሬለሁ፤ትእግስትን ….መረጋጋትንና …ጥሞናን ..አረ ብዙ ብዙ..ደግሞም በእሷ ምክንያት ሌላ 30 አመት ያህል ብታሰር እንኳን ቅንጣት ቅሬታ አይሰማኝም…››
‹‹ያን  ያህል ታፈቅራታለህ ማለት ነው?››
‹‹መጠንና ወሰን በሌለው ሁኔታ አፈቅራታለሁ…ደፈራት ብለው ሲከሱኝ በጣም ነው ያስገረሙኝ፡፡ እሷ እኮ የእኔው ነች፡፡ ልቤ ውስጥም ነፍሴ ላይም ያለችው እሷ ነች..እሷ ፊት ላይ ምታርፍ አንድ ጥፊ እንኳን ልቤ ላይ ጠባሳ ትተዋለች፡፡እንዴት ሰው የገዛ ልቡን በቢላዋ ወግቶ ያደማል…?እኔ እሷን እንኳን ልደፍራታ የለፍቃዷ  እጇን አልጨብጥም፡፡››
ፈዞ በተመስጦ ሲያዳምጠው የነበረው አጎቱ‹‹እሷስ ግን …?ማለቴ ያንተን ያህል ታፈቅርሀለች?››
‹‹እሱን ለማወቅ አልችልም…..እኔ እርግጠኛ ምሆነው በእኔ ማፈቅር ነው…ደግሞ የእኔ ፍቅር ጥልቅና ስምጥ ስለሆነ ለእኔም ለእሷም ይበቃል….ብቻዬንም ቢሆን ለሁለታችን የሚሆነውን ፍቅር ማመንጨት እችላለሁ፡፡››


ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
6.8K viewsTsiyon Beyene, 02:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-25 04:56:08 አሮራ
(ግማሽ ልቤን እና ግማሽ ነፍሴን ያመኛል)
ምዕራፍ _6
መንግስቱ አሁን የተሰጠው ክፍል አይደለም ሶስት አመት ከቆየበት የታፈገ የእስር ቤት ክፍል ይቅርና ቀድሞም በሰላሙ ጊዜ የራሱ የሆነ የተከበረ ስራ እያለው ከሚኖርበት ክፍል በጣም የተሻለና በውበትም በምቾትም የደመቀ ነው፡፡የአልጋው ጥራት፤ጠረጳዛው፤ ወንበሮቹ…ቁምሳጥኑ አንድ ዘመናዊ ወንደላጤ ቢኖሩት የሚመኛቸው ነገሮች ሁሉ የተሞሉለት ነው፡፡ከተቀመጠበት ተነሳና ወደ ሻወር ቤት አመራ፡፡ከፍቶ ገባ …ልዩ ነው፡፡ልብሱን አወላለቀና ወደመሀከል ተጠግቶ ውሀውን ከላይ ለቀቀው…..እስር ቤት ሻወር እንዴት እንደሚወስዱ ትዝ አለው…..መአት ወንዶች አንድ ላይ ይጠቀጠቁና ውሀው ከላይ ይለቀቃል… የአንዱ ጭቅቅት ተፈናጥሮ አንዱ ሰውነት ላይ እየተረጨ..አንዱ የሌላውን እርቃን ገላ እየጎበኛ ምቾት በሚነሳ መንገድ ይታጠባሉ፡፡
ያንንን እያሰበ ታጠበና  ፎጣ አገልድሞ ወደመኝታ ቤቱ ተመለሰ ፡፡ሰውነቱን አደራረቀና ልብስ ለመቀየር አሮጌ ሻንጣውን ከፈተ፡፡የተሻለ ያለውን ልብስ በመምረጥ ላይ ሳለ አጎቱ ቁም ሳጥኑ ውስጥ ልብስ አለልህ ያለው ትዝ አለው፡፡ሻንጣውን ባለበት ተወና እራቁቱን ወደ  ቁም ሳጥኑ አመራ፡ደረሰና ከፈተው፡፡መለስተኛ ቡቲክ ሊያስከፍት የሚችል ብዛትና ጥራት ያላቸው ልብሶች ተጠቅጥቀውበታል፡፡ሶስት የተለያየ ቀለም ያላቸው  ሙሉ ሱፎች ፤ከአምስት የሚበልጡ ጅንስ ሱሪዎች ሌሎች ሁለት ካኪ ሱሬዎች፤ ሸሚዞች፤ ፓክአውቶች ፤ፓንቶች እና ካልሲዎች ሳይቀሩ ተገዝተውለታል፡፡ቁም ሳጥኑ ጎን ያለው ወንበር ላይ ቁጭ አለ፡፡
‹‹ይሄ ሰውዬ ከእኔ ምንድነው የሚፈልገው…?››ሲል ጠየቀ፡፡አጎቱ ለእሱ ከፍተኛ እቅድ እንዳለው እርግጠኛ ነው፡፡ከለበለዚያ እንዲህ ድንገት ከተደበቀበትና ከተሸሸገበት ብቅ ብሎ ተወዳጅ አባት፤ ተናፋቂ ታላቅ ወንድም አይነት ገፀ ባህሪ ተላብሶ አይጫወትም ነበር…ዝም ብሎ አንድ ጅንስ ሱሪ አንድ ሸሚዝና አንድ ቀለል አያለ ጃኬት መረጠና ወደአልጋው ተመለሰ…፡፡ሁሉንም በየተራ ለበሰ፡፡ ወደሻወር ቤት ተመለሰና እራሱን በመስታወት ተመለከተ፡፡ የተወሰነ ቅባት እጅ ላይ አደረጋና ፀጉሩን እና ፊቱን  አባበሰ፡፡
‹‹አሁን እስኪ ወደ አዲሶቹ ተናፋቂ ዘመዶቼ ልሂድ ››አለና ወደውጭ መራመድ እንደጀመረ አጎቱ ለልጆቹ ምትሰጠው ስጦታ ነው ብሎ ጠረጴዛው ላይ ያስቀመጠለትን የስጦታ እቃ ትዝ አለው..ወደኃላ ተመለሰና አነሳቸው፡፡
‹‹አጎቴ አንተ እኔ ላይ ቆንጆ እቅድ ሊኖርህ እንደሚችል ጠንካራ ጥርጣሬ አለኝ..ግን እንዳትሸወድ እኔም በቅርብ ቀን አስበህ እራሱ የማታውቀውን እቅድ አወጣልሀለሁ፡፡ከአመታት በፊት ከአባቴ የወሰድከውን ሀብት ፤ ሰላም እና ጤና በጠቅላላ ከነወለዱ እረከብሀለው፡፡››ይሄንን በውስጡ እያሰላሰለ ሳሎን ሲደርስ የሳሎኑ ጠረጴዛ በምግብ ተሞልቶ ዙሪያውን በሰዎች ተከቦ  የእሱን መምጣት በናፍቆት ሲጠብቁ ደረሰ፡፡ከዛ ድግሱም ሆነ የአቀባበል ዝግጅቱ እስከምሽት የዘለቀና የተለየ ነበር፡፡
/////
በማግስቱ ጥዋት ከቁርስ በኃላ አጎቱ ይዞት ወጣ ፤ለሰላሳ ደቂቃ ዝምታ ያጠላበት ጉዞ ከተጓዙ በኃላ አንድ ግዙፍ ባለሶስት ወለል ገስትሀውስ ግቢ ውስጥ ይዞት ገባ፡፡መኪናዋን አቆሙና ግራውንድ ላይ ወዳለ አንድ ክፍል ይዞት ገባ….ለገስት ሀውሱ እንደቢሮ ሚያገለግል መሆኑን ክፍሉ ውስጥ ያሉትን እቃዎችን አይቶ መረዳት ይቻላል፡፡አጎትዬው የለበሰውን ጃኬት አወለቀና ማንጠልጠያው ላይ ሰቅሎ ጠረጴዛውን ዞሮ ግዙፉ ተሸከርካሪ ወንበር ላይ እየተቀመጠ እሱን ፊት ለፊት ያለ ወንበር ላይ እዲቀመጥ አዘዘው፡፡
‹‹እንግዲህ ይሄ የእኛ ገስት ሀውስ ነው፡፡በኃላ ልጀቹ ሁሉንም ክፍልም ሆነ  አጠቃላይ ግቢውን ያስጎበኙሀል....

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
9.4K viewsTsiyon Beyene, 01:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ