2022-09-24 18:52:01
. ◉●◦
አለሜ ነሽ ◦◉
ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ▣
አንብበው ሲጨርሱ ሼር ያርጉ ▣
#ክፍል_60
ደራሲ:- ቤዛዊት ፋንታዬ (የሸዋ ልጅ)
... ሄዋን፣አዳምና ቦስም ተኝተው ስለነበረ መልክቱን አላዩትም። ዲና በጠዋት
ውሀ እረጭታ ስታስነሳቸው እንጂ አስደንጋጭ መልክት
በስልካቸው ልካላቸው አንብበው አያውቁም....ሄዋን ከእንቅልፎ እንደነቃች የሌሊት ልብሷን ቀይራ
ወደ ሳሎን ሄደች።
ስልኳን ከእስማርት ቲቪው ጋራ አገናኝታ የዘወትር ልምዷን የሆነውን በጠዋት መዝሙር የመስማትና አብራ የመዘመር ፍቅሯን ልትወጣ መዝሙር ለመክፈት
ስልኳን ስትነካካ ቅድም ከቲቪው ጋር ለማገናኘት ስትሞክር ያላየችው አሁን ያስተዋለችው መልዕክት እንዳላት ምልክቱን አየች... ። የላኪው ማንነት ዲና ስለሆነች ግራ እየተገባች
"ምንድነው?" ብላ ከፍታ
ለማየት ወደ መልክት መፃፊያ እና መላኪያው ጋራ ሄደች። ሄዋን
አነበበችው አይኗን ማመን ተሳናት ህልም ቅዠት ቀልድ መሰላት
ሮጣ ወደ ዲና ክፍል ሄደች ዲና የለችም፤ ወደ በረንዳ ሄደች
አሁንም ዲና የለችም፤ መታጠቢያ ቤት ሄደች ዲ ና የለችም።
ሄዋን ዲናናናናናናናናናናናናናናናናናና ብላ ጮኸች። ቦስ ፣አዳም
ሰራተኖቹ እና ዘበኛው ተሯሩጠው ሄዋን ወዳለችበት መፀዳጃ ቤት
ሄዱ።
፨ አዳም "ምነው ምን ተፈጠረ?" አለ። ስልካችውን እዩት ዲና ዲና
ዲና መልክት ልካላችዋለች አለቻቸው። ቦስ እና አዳም
እየተሯሯጡ ወደ ክፍላቸው ሄዱ። ስራተኞቹ ሄዋንን ይዘው ሳሎን
ወስደው አስቀመጧት። አዳም እና ቦስ ስልካቸውን ካስቀመጡበት
አውጥተው መልክቱን አነበቡ። አዳም ከክፍሉ ወጥቶ ወደ ውጪ
ወጣ ቦስም ተከተለው። ሄዋን "የት ነው የምትሄዱት" አለችው....
"ዲና እንዲህ ሆና እንዴት አስችሎኝ እቀመጣለው ያን ምንም
እንዲያረገኝ አልፈቅድም በቃ" አለ።ቦስም "አዎ እኔም ዲናዬን
አጥቼ መኖር አልችልም" አለ። ሄዋን "አይ አትሂዱ የእናንተ መሄድ
ነገሩን ያብሰዋል እንጂ በጭራሽ አያቀለውም። ትንሽ እንታገስ እና
ከዛ መወሰን ያለብንን እንወስናለን" አለች። ሄዋን ንግግሯን
እንደጨረሰች የአዳም ስልክ ላይ መልዕክት ገባ። ወዲያው
አውጥቶ አየው። የማያውቀው ቁጥር ነበረ። መልክቱ እንዲህ
ይላል "ስላም ላንተ ይሁን አዳም ሰለ ዲና ሀሳብ አይግባክ" ።
ሄዋን ከተቀመጠችበት ሶፋ ብድግ ብላ ከአዳም እጅ ላይ ስልኩን
መንጭቃ ጮክ ብላ አነበበቸው።
፨ ቦስ "ማነው እንዲህ ያለው እየቀለዱብን ነው አውቀው ነው አ?"
አለ። ሄዋን "አይ እኔ ግን የተለየ ሀሳብ ነው ያለኝ።ምን አልባት
የጊዲዮን ጠላት ሊሆን ይችላል" አለች። አዳም "ሲጀመር እኮ እሱ
ወዳጅ ሳይሆን አሽርጋጅ ነው ያለው" አላት። ቦስም "እና ምን
እናድርግ ቆይ ምን ይሻላል ኧረ መላ ፍጠሩ ዝም ብለን እጃችንን
አጣምረን እንቀመጥ ወይ እሺ ካልሆነ አስቀመጥኩት ያለችውን
ነገር እናንብበው" አለ። ሄዋን "አይ አይሆንም መታገስን መልመድ
አለብን ከእዚህ በኋላ ትግስት ያስፈልገናል እሺ አሁን ልሄድ ብላቹ
የት ነው የምትሄዱት?" አለች።ቦስ "የትም በቃ ምን እንደሚፈጠር
እስቲ እንናያለን ዲና ካለችው ሰዓት ካለፍ ግን ወደ ፓሊስ ጦቢያ
ነው የምንሄደው እሺ" አለ።አዳም "አይ ወዳጄ ሞኝ የዋህ ገራገር
ነክ ልበል እስካሁን ይህ ነገር የጠፍኝ መስሎክ ነው ግን
ስለማይሆን ነው የትኛውም ፓሊስ ጣቢያ የጌዲዮን ስዎች ነው
ያሉት። ለመክሰስ እንደምትፈልግ ነገረካቸው ከተስማሙ በኋላ
የምትከሰው ሰው እሱ መሆኑን ሲያውቁ ይሸሹካል መቼም
የማይሆን ነገር ነው። እንደምታስበው ቀላል አደለም እንጂ ቢሆን
ኖሮ እኔ ድሮ ነበረ የማሳስረው እንኳን መረጃ ሳይኖርክ ቢኖርክም
መቼም አይሰሙክም" አለ። ቦስ "ቆይ ታዲያ ምን ተሻለ?" አለና
የለበስውን ቲሽርት እስከሆዱ በብስጭት ገለፀው። አዳምም
"ምንም ምንም ማረግ አንችልም በቃ ቁጭ ብለን መጠበቅ ብቻ"
አለ።
፨ ቦስ ዲና ስልክ ላይ ደወለ። "የደወሉላቸውን ደንበኛ አሁን
ማግኘት አይችሉም እባኮ ትስሽ ቆይተው ይደውሉ" ይላል።
ደጋግሞ ሞከረ ግን የዲናን ድምፅን መስማት አልቻለም።አዳምም
ሄዋንም በተደጋጋሚ ሞከሩት ግን ስልኳ አይስራም። በጣም ተጨነቁ ፣ተንጎራደዱ፣ተቁነጠነጡ ፣አለቀሱ የማይደረስ ቀን
፤የማይነጋ ለሊት ፤የማይሄድ ወንዝ የለምና ስአትም ሰአት እየተካ
የሚጠብቁት ስአት ደረሰ።
፨ምሽት 1:00 አዳም "አሁን በጭራሽ መታገስ አልችልም"
አለና።ዲና መኝታ ቤት ገባና ቁም ሳጥኑን ከፍቶ ወረቀቱን ይዞ
ሳሎን መጣ። ሄዋን ቦስ እና ሰራተኞቹ በጉጉት ምን እንደሚል
ለመስማት ወደ አዳም
አፈጠጡ አዳምም ተስገብግቦ እና ቸኩሎ ከፈተው ጮክ ብሎ
ማንበብ ጀመረ።
፨ "ዛሬ ከእናንተ መለየቴን ሳስበው በጣም ከፍኝ ፤እጅክ አድረጌ
እወዳችዋለሁ። ቦስዬ አንተን ደሞ አፈቅረካለው አንዳንዴ
ከምንወዳቸው ጋራ ለዘላለም የምንኖረ ይመስለኛል። ብዙ
የአብሮነት ጊዜ እንደምናሳልፍ እኔም አስቤው ነበረ። ቦስዬ
የማልዋሽክ ነገረ ቢኖረ ገና አዳምዬ ፎቶክን ሲያሳየኝ ካንተ ጋራ
ጥሩ ፍቅር ውስጥ እንደምገባ ልቤ ነግሮኝ ነበር።እና ሆነ ቀለበት
አሰርክልኝ ያኔ በጣም ደስ ብሎኝ ነበረ ከዛ ደሞ እንዳገባክ
ስትጠይቀኝ ደስ አለኝ። በጣም ተመኝቼ ያልሆነው ነገር ቢኖር
ለዘላለም ሚስትክ የልጆክ እናት አለመሆሄ እና አንተን የማይዘልቅ
ፍቅር ውስጥ መክተቴ ነው። አዳም 'ትክክለኛ ፍቅር አንዴ
ይይዛል' ብሎኛል።ዝረዝሩን አዳምን ጠይቀው"። የሚለውን አዳም
ሲያነበው ሁሉም ፈገግ አሉ። አዳም ማንበቡን ቀጠለ "የኔ ውዶች
ሁሌም ፈገግ በሉልኝ ይህንን ቦታ ስታነብት ፈገግ እንደምትሉ
አውቃለው ። ቦስዬ ልብክ እንደሚሰበር አውቃለው ግን ቦስዬ በቃ
ምን ላድረግ።
፨ አምዳዬ አንተ አንተ ደሞ ከፈጣሪ የተሰጠከኝ ወንድሜ ስጦታዬ
ነክ።የህይወት መምህሬ ነክ ፍቅሬን እንዳውቅ ፈጣሪ የሰጠኝ
አንተንም መጀመሪያ ቀን ሳይክ ብዙ ነገር እንደምታስተምረኝ አውቄ
ነበረ። እና አልተሳሳትኩም አስተምረከኛል።
፨ሄዋንዬ የኔ ጩኸታም የኔ ሳቂታ ሳቂታዬ ሁሌም ሳቂልኝ እሺ
እንዲህ ስልሽ ፈገግ እንደምትይ አውቃለው" ይላል ሄዋን
እውነትም ፈገግ ብላለች አዳም ማንበብን ቀጠለ "ሄዋንዬ አንቺ
ማለት ደሞ ስለፍቅረ እንድማረ ር ምክንያት የሆንሽኝ ነሽ። ማለቴ
ያው ለማለት የፈለኩት ያው እንኳን ታመምሽ እያልኩሽ አደለም።
ከአንቺ ጋራ በጣም የተቀራረብንበትን እና የሳቅንበትን ቀን
ታስታውሽዋለሽ በጋራ ሻውር የወሰድንበትን ቀን እኔ ደስተኛ
ነበርኩ..
ይቀጥላል...
........... ••● ............
☛ በ 𝚈𝙾𝚄𝚃𝚄𝙱𝙴 ይከታተሉን
https://bit.ly/2XS2ecv
☛ በ 𝙵𝙰𝙲𝙴𝙱𝙾𝙾𝙺 ይከታተሉን
https://bit.ly/3ja9o3O
☛ በ 𝙸𝙽𝚂𝚃𝙰𝙶𝚁𝙰𝙼 ይከታተሉን
https://bit.ly/3rM2yop
◎◦#ሼር◦◎
◎◦#ሼር◦◎
@Yefiker_Gojo || @AbenaG
━━━━━✦ ✿ ✦━━━━━
2.3K views♕𝙰𝙱𝙴𝙽𝙸 𝙹𝙲❥̟, edited 15:52