2023-03-23 19:23:48
ምኞት
ክፍል 43
ደራሲ ጥላሁን ተስፋዬ
.
.
.
አልጋ ውስጥ ከስር ገብታ ለመደበቅ ፍራሹ የሚያርፍበትን ችፑድ
ስታነሳው ....
እንኳን ውስጡ ገብታ ልትደበቅ ለመመልከት እንኳን ይከብዳል
ተጠርእጎ የማያውቅ አርቤርጎ ይመስላል።
እዚህ ውስጥማ አልደበቅም አለችና ወደ ሳሎኑ ተመልሳ መሀል
ላይ ቆመች ። ግራ ገባት ወደ ጀርባዋ መሬት ወደተነጠፈው
የመሳይ መኝታ ከጥግ እስከ ጥግ የተዘረጋውን ወፍራም መጋረጃ
ጠጋ ብላ ስትገልጠው ወደ ኮንደሚንየሙ ጀርባ ወዳለችው
ጠባብ በረንዳ የሚያስወጣው የተቆለፈው በር ቁልፉ በሩ ላይ
እንደተወተፈ ነው።
በሩን ከፈተችና ቁልፉን ኩውስጡ በማውጣት ወደ በረንዳው
ከመውጣቷ በፊት መጋረጃውን እንደነበረው አስተካክላ በመውጣት
ከውጪ ቆልፋው እበረንዳው ላይ ጥጓን ይዛ ተቀመጠች።
መሳይና ትንቢተ እነሱን ተከትለው በተሯሯጡት የኬንደሚንየሙ
ነዋሪዎች እየተሳሳቁ ወደ ውስጥ ገቡ።
የምኛት የልብ ትርታ ጨመረ። ቅድም በትግል አልከፈት ያላት
የእቃቤቱ በር አሁን ገፋ ስታረገው በቀላሉ በመከፈቱ የትንቢተ
ፍርሀትና ጥርጣሬ ልኩን አለፈ።
አንገቷን ብቅ አድርጋ ወደ እቃ ቤቱ በስሱ ከማየት ውጪ ወደ
ውስጥ ደፍራ መግባት አልቻለችም።
"ወንድሜ ተነስ ወደ ቤታችን እንሂድ እሄ ቤት ምኑም አልጣመኝም!
በጭራሽ እዚህ መቆየት የለብህም እንሂድ መስዬ ?" ስትለው •••
"ስሚ እህቴ የኔ ውድ እህት እኔን ከዚህ ቤት ይዛኝ የምትወጣው
ኖርዶስ ብቻ ነች ከዛ ከሷ ውጪ ንቅንቅ አልልም "ሲላት ደነገጠኝ።
" መስዬ እምልህን ሰምተኸኛል እሄ ቤት እንኳን አንተን እኔንም
ሊያሳብደኝ ነው ኖርዶስ እዚህ ምንም ልታደርግ አትመጣም
ሰይጣን ነች በናርዶስ ተመስላ የመጣችው መስዬ ሰይጣን ነች!
ና አሁኑኑ ቤቱን ለቀን መውጣት እጅ ለብን ብላ ግራ እጁን ያዝ
ስታደርገው።
ሳታስበው ግራ እጁን በሀይል መነጨቃትና በቀኝ እጁ በጥፊ
መረገባት። ተንገዳግዳ ግድግዳውን ተደግፋ ቆመች። ጥፊው
እንኳን ትንቢተን በረንዳው ላይ ያለችውን ምኛትንም
አስደንግጧታል።
ትንቢተ ክው እንዳለች ግድግዳውን ተደግፋ በአንድ እጇ ፊቷን
እንደያዘች።
"መታከኝ ወንድሜ እኔ ላይ እጅህን አነሳህ መስዬ እኔ እኮ የናትህ
ልጅ ትንቢተ ነኝ !" ስትለው
"ኖርዶሴን ሰይጣ ያስባለችሽ ሰይጣን አናትሽ ላይብስትጨፍር
አይቻት እሷን መታለሁ ብዬ ነው ይቅር በይኝ ልክ አንቺን በጥፊ
ስልሽ ቀድማሽ ከግድግዳ ጋር የተላተመችው እኮ ሰይጣና ነች
ከዛ እየተንገዳገደች ወደ ውጪ ወጣች ናርዶሴ ከመጣች
ታጣኛለች ብዬ ነው እንጂ ተከትያት ልሄድ ነበርኮ ክክክክክክክክ "
ሲል እብደቱ እየተነሳበት እንደሆነ አወቀች ቀስ ብላ ወደ
መውጫው በር ካቀናች ቡሀላ ወጥታ በሩን ከውጪ ከቆለፈችበት
ቡሀላ•••
መስ ሰማኽኝ አባቢን ይዤው መጣና ወደ ቤት ይዘንህ
እንመለሳለን ስትለው መሳይ ግን ለሱ ብቻ ከሚታየው ጓደኛው ጋር
ማውራት ጀምሮ ስለነበር አልሰደነገጠ
ሚኪ ወደ ማደሪያው ገብቶ እንደተረጋጋ ለብሩኬ ደወሎ ምኛትን
ድሬ ዳዋ እንዳላገኛትና ሊመለስ እንደሆነ ሲነግረው በጭራሽ ወደ
አዲስ አበባ እንዲመለስና ፅናትን እንዲያገኛት አይፈልግምና
በሚኪ ልመለስ ነው ማለት እጅግ በጣም ነበር የደነገጠው።
"አረ ባክህ ሚኪ ምንድን ነው እንደዚህ ያጣደፈህ እዚህ
ያስቀመጥከው ነገር አለ እንዴ ይልቅ ከድሬ ውጪ አትሆንም! ግዜ
ወስደህ በደንብ ብትፈልጋት ነው እሚሻለው ለማንኛውም መልሼ
እደውላለሁ ብሎት ስልኩን በመዝጋት ።
ትንሽ ቆይቶ በምኛት ስም በከፈተው የፌስ ቡክ አካውንት ወደ
ሚኪ የጓደኛ እንሁን ጥያቄ ላከለት ሚኪ ጓደኝነቱን ለመቀበል
ደቂቃዎች አልፈጁበትም ነበር።
ብሩክ " ካካካካ••• እየሳቀ ወድያው ሚኪዬ ነይ ብለህ እንደሰው
ጠርተከኝ እንደውሻ ብታባርረኝም አንተን የምጠላበት አንጀት
የለኝም እኔ መቀሌ ነው ያለሁት አንተ የት ነህ?
ብሎ በመላክ " ወይ ወደ አዲስ አበባ መመለስ ገና መች
ፈለካትና ቀጣይ ጎንደር እልክሀለሁ ካካካካካ......
..............ይቀጥላል............
170 ከገባ#ክፍል 44 ዛሬ ይለቀቃል
1.8K viewsflawoless , 16:23